ሀ ለ ሐ መ ሠ ረ ሰ ሸ ቀ በ ተ ቸ ኀ ነ ኘ አ ከ ኸ ወ ዐ ዘ ዠ የ ደ ጀ ገ ጠ ጨ ጰ ጸ ፀ ፈ ፐ
ጸልሞን ~ Zalmon:
‘ጽልመት፣ ጨለማ፣ ጥላ፣ ጠለላ’ ማለት ነው። ከዳዊት
ጠባቂዎች አንዱ፥
አሆሃዊው፥ “ጸልሞን፥ ነጦፋዊው
ኖኤሬ፥ የነጦፋዊው
የበዓና ልጅ
ሔሌብ፥ ከብንያም
ወገን”
(2 ሳሙ 23:29)
ጸዒር ~ Zair: ‘ትንሽ’ ማለት ነው። የቦታ ስም፥ “ኢዮራምም ከሰረገሎቹ ሁሉ ጋር ወደ ጸዒር አለፈ፤ በሌሊትም ተነሥቶ እርሱንና ...”
(2 ነገ 8:21)
ጸዕነኒም ~ Zaanannim: ‘መጻተኞች፣ ስደተኛ፣ ተጓዥ፣ መንገደኛ’ ማለት ነው። “ድንበራቸውም ከሔሌፍ፥ ከጸዕነኒም ዛፍ፥ ከአዳሚኔቄብ፥ ከየብኒኤል እስከ ለቁም ድረስ ነበረ ...” (ኢያ 19:33)
ጸፍናት ፐዕናህ ~ Zaphnath-paaneah: ‘አሳሽ፣ ዳሳሽ፣ መርማሪ፣ ፈላጊ’
ማለት ነው። “ፈርዖንም የዮሴፍን ስም ጸፍናት ፐዕናህ ብሎ ጠራው፤ የሄልዮቱ ከተማ ካህን የጶጥፌራ ልጅ የምትሆን አስናትን አጋባው። ዮሴፍም በግብፅ ምድር ሁሉ ወጣ” (ዘፍ 41:45)
ጹፍ ~ Zuph: ‘ሰፈፍ’ ማለት ነው። “ወደ ጹፍ ምድር በመጡ
ጊዜም ሳኦል
ከእርሱ ጋር
የነበረውን ብላቴና፦
አባቴ ስለ
አህዮች ማሰብ
ትቶ ስለ
እኛ እንዳይጨነቅ፥
ና፥ እንመለስ
አለው።” (1
ሳሙ 9:5)
ጺልታይ ~ Zilthai: ‘ጥላዬ፣ ሕያው ጥላ፣ ጠለላ’ ማለት ነው።
1. ብንያማዊ፥ “ኤሊዔናይ፥ ጺልታይ፥
ኤሊኤል፥ ዓዳያ፥ ብራያ፥ ሺምራት፥
የሰሜኢ ልጆች” (1 ዜና 8:20)
2. በጺቅላግ ከዳዊት ሠራዊት ጋር የተቀላቀለ፥ የምናሴ ሻለቆች ከነበሩ፥ “ወደ ጺቅላግም
ሲሄድ ከምናሴ
ወገን የምናሴ
ሻለቆች የነበሩ
ዓድና፥ ዮዛባት፥ ይዲኤል፥ ሚካኤል፥ ዮዛባት፥ ኤሊሁ፥ ጺልታይ ወደ እርሱ ከዱ።” (1 ዜና
12:20)
ጺቅላግ ~
Ziklag:
ጠመዝማዛ ማለት ነው። በይሁዳ ደቡባዊ ግዛት የነበረ ከተማ፥ “ኪሲል፥ ሔርማ፥ ጺቅላግ፥ ማድማና፥ ሳንሳና፥” (ኢያ 15:31)
ጺን ~ Zin: ‘ረባዳ፣ ጠፍጣፋ፣
ደልዳላ’
ማለት ነው።
“ወጡም ምድሪቱንም ከጺን ምድረ በዳ በሐማት ዳር እስካለችው እስከ ረአብ ድረስ ሰለሉ” (ዘኊ 13:21)
ጺዖር ~ Zior: ‘ብልጭታ፣ ትንሽ ብርሃን’
ማለት ነው።
በይሁዳ ተራራማ
ክፍል የሚገኝ
ከተማ፥ “አፌቃ፥ ሑምጣ፥
ኬብሮን የምትባል
ቂርያትአርባቅ፥ ጺዖር ዘጠኝ ከተሞችና መንደሮቻቸው።” (ኢያ 15:54)
ጺጽ ~
Ziz:
‘ትንበያ’ ማለት ነው። “ነገ በእነርሱ ላይ ውረዱ እነሆ፥ በጺጽ ዓቀበት
ይወጣሉ በሸለቆውም
መጨረሻ በይሩኤል
ምድረ በዳ
ፊት ለፊት
ታገኙአቸዋላችሁ።”
(2 ዜና 20:16)
ጻርታን ~
Zaretan: ‘መከራ፣ እንግልት’ ማለት ነው። ታቦቱን
የተሸከሙት የካህናቱ
እግሮች የዮርዳኖስን ውኃ ሲነኩ፥ ውኃው የቆመበት ቦታ፥ “ከላይ የሚወርደው ውኃ ቆመ
በጻርታን አጠገብ
ባለችው አዳም
በምትባል ከተማ
በሩቅ ቆሞ
... ሕዝቡም በኢያሪኮ
ፊት ለፊት
ተሻገሩ።”
(ኢያ 3:16፣17)
ጼላ ~ Zelah: ‘ዛለ፣ ደከመ’ ማለት
ነው። ለብንያም
ነገድ የተሰጠ
ቦታ፥ “ሬቄም፥ ይርጵኤል፥ ተርአላ፥ ጼላ፥ ኤሌፍ፥ ኢየሩሳሌም የምትባል የኢያቡስ ከተማ፥ ቂርያትጊብዓት
አሥራ ሦስት
ከተሞችና መንደሮቻቸው።
የብንያም ልጆች
ርስት በየወገኖቻቸው
ይህ ነበረ።” (ኢያ 18:28)
ጼሌቅ ~
Zelek:
ዘ ሊቅ፣ ጠሊቅ፣ ጥልቅ፣ ዘላቂ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ሊቅሕ፣ ሉቃስ]
Zelek-
‘ጥልቅ’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም
ነው። የኢዮአብ ጋሻ ጃግሬ፥ (2 ሳሙ 23:37) ፣ (1 ዜና 11:39)
ጼልጻህ ~
Zelzah:
‘ጥላ፣ ጠለላ’ ማለት ነው። የብንያም አዋሳኝ የሆነ የቦታ ስም፥
“ዛሬ ከእኔ በተለየህ
ጊዜ በብንያም
ዳርቻ በጼልጻህ አገር ባለው በራሔል
መቃብር አጠገብ ሁለት ሰዎች ታገኛለህ እርሱም፦ ...” (1 ሳሙ 10:2)
ጼር ~
Zer:
ጾር፣ ጣእር፣ ጦር፣ ፈተና፣ መከራ፣ አሳር... ማለት ነው። የንፍታሌም ልጆች ነገድ ርስት የሆነ የቦታ ስም፥ (ኢያ 19:35)
ጽሩዓ ~
Zeruah:
ዘርህ፣ ዘር፣ ወገን፣ ዘመድ፣ ረዳት፣ አጋዥ፣ ተባባሪ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ጽሩያ፣ ጽሩዓ፣ ጽሪ]
የናባጥ ልጅ
የኢዮርብ እናት፥
(1 ነገ 11:26)
ጽሩያ ~
Zeruiah:
ዘረያ፣ ዘረ ሕያው፣ የሕያው አምላክ ዘር፣ የጌታ ወገን፣ የእግዚአብሔር ልጅ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ጼር፣ ጽሩዓ፣ ጽሪ]
Zeruiah- ‘ዘር’
እና ‘ያሕ’ (ያሕዌ ፣ ሕያው) ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። የናባጥ
ልጅ የኢዮርብ
እናት፥ (1 ዜና 2:16)
ጽሪ ~
Zeri:
ዘሪ፣ ዘር የሚዘራ፣ የሚያመርት፣ የሚያበረክት... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ጼር፣ ጽሩያ፣ ጽሩዓ]
በንጉሥ ዳዊት ዘመን የነበረ፣ የኤዶታም ልጅ፥ (1 ዜና 25:3)
ጽሮር ~ Zeror: ‘እስር፣ ነዶ’ ማለት
ነው። ቂስ
የተባለ የብንያማዊ
ሰው፥ የብኮራት አባት፥ “ስሙ ቂስ የተባለ አንድ ብንያማዊ ሰው ነበረ እርሱም የአቢኤል ልጅ፥ የጽሮር ልጅ፥ የብኮራት ልጅ፥ የብንያማዊው የአፌቅ ልጅ፥ ጽኑዕ ኃያል ሰው ነበረ” (1 ሳሙ 9:1)
ጽናን ~
Zenan:
‘ጠማማ’
ማለት ነው። የይሁዳ አዋሳኝ የሆነ የቦታ ስም፥ “ጽናን፥ ሐዳሻ፥
ሚግዳልጋድ፥ ዲልዓን፥” (ኢያ 15:37)
ጽዮን ~
Zion:
ጽኑ፣ ጽኑዓን፣ ብርቱ፣ ጠንካራ፣ መከታ፣ አምባ፣ መመኪያ... ማለት ነው ። ኢየሩሳሌምም ጽዮን ትባላለች። [ተዛማጅ ስም- ሲዎን]
[ቃሉ አምባ
ማለት ነው
/ መቅቃ]
. የኢየሩሳሌም ሌላ ስም፥ “...ዳዊት ግን አምባይቱን ጽዮንን ያዘ እርሷም የዳዊት
ከተማ ናት:” (1 ዜና 11፡5-7)
. በአዲስ ኪዳን ጽዮን የሚለው ስም ለቤተ ክርስቲያን እና ለሰማያዊ የእግዚአብሔር መንግሥት፥
መጠሪያ ስም
ሁኖ ያገለግላል።
(ዕብ 12:22) ፣ (ራእ 14:1)
ጽዳድ ~ Zedad:
‘ገዳዳ፣ አቀበት’
ማለት ነው።
በሐማት አጠገብ፣
በሰሜን ፍልስጥኤም
የነበረ ከተማ፥
“ከሖርም ተራራ ወደ
ሐማት መግቢያ
ምልክት ታመለክታላችሁ የዳርቻውም መውጫ በጽዳድ ይሆናል” (ዘኊ 34:8፤ ሕዝ 47:15)
ጽፋት ~ Zephath: ‘ማማ’ ማለት ነው። የከነዓን ከተማ ጥንታዊ ስም፥ “ይሁዳም ከወንድሙ ከስምዖን ጋር ሄደ፥ በጽፋት የተቀመጡትንም ከነዓናውያንን መቱ፥ ፈጽመውም አጠፉአት። የከተማይቱንም ስም ሔርማ ...” (መሣ 1:17)
ጾርዓ ~
Zareah, Zorah: ጸራ፣ ጠራ፣ ጮራ፣ ጨረር... ማለት ነው።
ጾርዓ / Zareah: በደቡብ በኩል በምድራቸው ዳርቻ አጠገብ እስከ ኤዶምያስ ድንበር ያሉት የይሁዳ ልጆች ነገድ ከተሞች፥ (ነህ 11:29)
ጾርዓ / Zorah: የዳን ነገድ ርስት፥ “በቈላው ኤሽታኦል፥ ጾርዓ፥ አሽና፥ ዛኖዋ” (ኢያ 15:33)
ጾርዓ ~
Zorah:
‘ጢንዚዛ’ ማለት ነው። ለዳን ነገድ የተሰጠ ከተማ፥ “የርስታቸውም ዳርቻ ይህ ነበረ ጾርዓ፥ ኤሽታኦል፥ ዒርሼሜሽ፥”
(ኢያ 19:41)
ጾፊም ~ Zophim: ‘ጠባቂዎች’
ማለት ነው።
ባላቅ እስራኤላውያንን እንዲረግምለት ባላምን የወሰደበት ሜዳ፥ “ወደ ጾፊምም ሜዳ ወደ ፈስጋ ተራራ ራስ ላይ
ወሰደው ሰባትም
መሠዊያዎች ሠራ፥
በየመሠዊያውም ላይ
አንድ ወይፈን
አንድም አውራ
በግ አሳረገ” (ዘኊ 23:14)
ጾፋ ~ Zophah:
‘ሽንክላ፣ ዋርማ፣ ጽዋ’
ማለት ነው።
የኤላም ልጅ፥
“የወንድሙም የኤላም ልጆች ጾፋ፥ ይምና፥ ሰሌስ፥ ዓማል ነበሩ።” (1 ዜና 7:35፣36)
No comments:
Post a Comment