ሀ ለ ሐ መ ሠ ረ ሰ ሸ ቀ በ ተ ቸ ኀ ነ ኘ አ ከ ኸ ወ ዐ ዘ ዠ የ ደ ጀ ገ ጠ ጨ ጰ ጸ ፀ ፈ ፐ
ሰለሚኤል ~
Shelumiel:
ሸላመ ኤል፣ ሰላመ ኤል፣ የአምላክ ሰላም፣ የጌታ ምሕረት... ማለት ነው።
‘ሰላመ’ እና ‘ኤል’
ከሚሉት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። ከእስራኤል ወደ ሰልፍ ከወጡ፥ (ዘኁ 1:6)
ሰለጰዓድ ~ Zelophehad:
‘የፍራቻ ድባብ’
ማለት ነው።
የምናሴ የልጅ
ልጅ፣ ለኦፌር
ልጅ፥ “ለምናሴ ልጅ፥
ለማኪር ልጅ፥
ለገለዓድ ልጅ፥
ለኦፌር ልጅ፥
ለሰለጰዓድ ግን
ሴቶች ልጆች
እንጂ ወንዶች
ልጆች አልነበሩትም፤ የሴቶች ልጆቹም
ስም ማህለህ፥ ኑዓ፥ ዔግላ፥ ሚልካ፥ ቲርጻ ነበረ” (ኢያ 17:3)
ሰሊሳ ~
Shelesh:
ሽለሽ፣ ስለሽ፣ ስለሺህ፣ ስለ ብዙ፣ ኃያል... ማለት ነው።
Shelesh- ‘ስለ’
እና ‘ሺህ’ ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። ከአሴር ነገድ የሆነ፣ የጾፋ ልጅ፥ ሰሊሳ፥ (1 ዜና 7:37)
ሰላሚኤል ~
Shemuel:
ስማ ኤል፣ አምላክ ሰማ፣ ጌታ አዳመጠ፣ ልመናን ተቀበለ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ሳሙኤል፣ ሽሙኤል]
Shemuel -‘ሰማ’
እና ‘ኤል’ ከሚሉ ሁለት ቃላት የተገኘ ስም ነው።
. ከስምዖን ልጆች ነገድ የሆነ፣ የዓሚሁድ ልጅ፥ “ከስምዖን ልጆች ነገድ የዓሚሁድ ልጅ
ሰላሚኤል”
(ዘኁ 34:20)
. የሕልቃና
አባት፥ ሳሙኤል- (1
ዜና 6:33፣34)
. የቶላ
ልጅ፥ ሽሙኤል- (1 ዜና 7:2)
ሰላትያል ~ Salathiel, Shealtiel:
ስእለተ ኤል፣ ከአምላክ የተጠየቀ፣ የጌታ ስእለት፣ የስእለት ልጅ... ማለት ነው።
Salathiel- ‘ስእለት’
እና ’ኤል’ ከሚሉ ቃላት የተገኘ ስም ነው።
ሰላትያል / Salathiel: የምርኮኛው የኢኮንያን ልጅ ሰላትያል፥
(1
ዜና 3:17)
ሰላትያል / Shealtiel:
በጌታ የዘር ሐረግ የተጠቀሰ፥ የኢኮንያን ልጅ፥ (ማቴ 1:12) ፣ የኔሪ ልጅ፥ (ሉቃ 3:7)
ሰሌምያ ~ Shelemiah: ሰላመ ያሕ፣ የአምላክ ሰላም፣ የሕያው ሰላም፣ የአምላክ እርቅ፣ የአምላክ አንድነት... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ሰሎሜ፣ ሰሎም፣ ሴሌሚ፣ ሴሌም፣ ሺሌም]
‘ሰላመ’ እና ‘ያሕ’(ያሕዌ ፣ ሕያው) ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
“በምሥራቅም በኩል ዕጣ ለሰሌምያ ወደቀ። ለልጁም ብልህ መካር ለሆነው ለዘካርያስ ዕጣ ጣሉ ዕጣውም በሰሜን በኩል ወጣ።” (1 ዜና 26:14)
2.
ከግዞት ተመልሰው ኢየሩሳሌምን ካደሱ፣ የሐናንያ አባት፥ ሰሌምያ፥ (ነህ 3:30)
3.
በመጽሐፈ ዕዝራ የተጠቀሰው የባኒ ልጅ ሰሌምያ፥ (ዕዝ 10:39)፣ (ዕዝ 10:30)
4.
በነህምያ ዘመን
የነበረ ካህኑ
ሰሌምያ፥ (ነህ 13:13)
5.
ንጉሡ ሴዴቅያስ፣ ወደ እግዚአብሔር ስለ እኛ ጸልይ ብሎ ወደ ኤርምያስ የላከው፥ ሰሌምያ፥ (ኤር 37:3፣ 38:1)
6.
የዘበኞች አለቃ፥ የሐናንያ ልጅ፣ የየሪያ አባት፥ ሰሌምያ፥ (ኤር 37:13)
7.
የኵሲ ልጅ፥
ሰሌምያ፥ (ኤር 36:14)
8.
የዓብድኤል ልጅ፥
ሰሌምያ፥ (ኤር 36:26)
ሰሌስ ~
Shelesh:
ስለሽ፣ ስለሺህ፣ የሺህ ሰው ያሕል፣ ኃይለኛ... ማለት ነው።
Shelesh-‘ስለ’ እና ‘ሺህ’
ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
የኤላም ልጅ፥
(1 ዜና 7:35)፥ “ሦጋል፥
ቤሪ፥ ይምራ፥
ቤጼር፥ ሆድ፥
ሳማ፥ ሰሊሳ፥ ይትራን፥
ብኤራ ነበሩ።“
(1 ዜና 7:37)
ሰልሙና ~
Salmone:
ሰላምነ፣ ሰላማዊ፣ ሰላማችን... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ሰልማን፣ ሰሎሞን]
‘ሰላም’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው።
ጳውሎስና ሌሎች ወደ ሮም ሲሄዱ ያለፉበት የወደብ ስም፥ ሰልሙና፥ (ሥራ 27:7)
ሰልማን ~
Shalman:
ስለ አማን፣ ሰለሞን፣ ሰላማዊ፣ አማናዊ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ሰልሞን፣ ሰሎሞን]
‘ስለ’
እና ‘አማን’
ከሚሉ ቃላት
የተመሠረተ ስም
ነው። በነቢዩ ሆሴዕ ትንቢት የተጠቀሰው፥ ሰልማን፥ (ሆሴ 10:14)
ሰልሞን ~ Zalmon, Salma: ስለአማን፣ ሰላማዊ፣ ደኅናነት፣ ርጋታ፣ ጸጥታ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ሰሎሜ፣ ሰሎም፣ ሴሌሚ፣ ሴሌም፣ ሺሌም] ‘ስለ’ እና ‘አማን’ ከሚሉ ቃላት የተገኘ ስም ነው።
በዚህ ስም የሚታወቁ አንድ ሰውና አንድ ቦታ አሉ።
.
የተራራ ስም፥
(መሣ 9:48)
.
በጌታ የዘር ሐረግ የተጠቀሰ፣ የነአሶን ልጅ፥ (ማቴ 1:4፣ 5) ፣ (ሩት 4:20)
ሰልሞን /
Salma: ሰላም፣ ጸጥታ ማለት ነው። የነአሶን ልጅ፥ የቦዔዝ አባት፥
“አሚናዳብም ነአሶንን ወለደ፥
ነአሶንም ሰልሞንን
ወለደ፥”
(ሩት 4:20፣ 21፤ 1 ዜና 2:11፣51፣ 54፤ ማቴ 1:4፣5፤ ሉቃ 3:32)
ሰልካ ~ Salcah: ‘ስደት’
ማለት ነው።
ለምናሴ ነገድ
የተሰጠ፥ የባሳን
ከተማ፥ “በሜዳውም ያሉትን
ከተሞች ሁሉ፥
ገለዓድንም ሁሉ፥
በባሳንም ያሉትን
የዐግን መንግሥት ከተሞች እስከ ሰልካና እስከ ኤድራይ ድረስ ባሳንን ሁሉ ወሰድን”
(ዘዳ 3:10፤ ኢያ 12:5፥
13:11)
ሰሎሚት ~ Shelomith, Shelomoth: ሰላሚት፣ ሰላማዊት፣ አማናዊት፣ ደኅንነት... ማለት ነው።
‘ሰላም’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ሰሎሚት / Shelomith:
1.
ከዳን ወገን የሆነች የደብራይ ልጅ፥ ሰሎሚት፥ (ዘሌ 24:11)
2.
የዘሩባቤል ልጅ፥
ሰሎሚት፥ (1 ዜና 3:19)
3.
የይስዓር ልጆች አለቃው፥ ሰሎሚት፥ (1 ዜና 23:18)
4.
በንጉሥ ዳዊት ዘመን ከሙሴ ልጅ ወገን፣ የአልዓዛር ልጅ፣ ሰሎሚት፥
(1
ዜና 26:25፣ 26፣ 28)
5.
የለአዳን አባቶች ቤቶች አለቃ፥ የሰሜኢ ልጅ፥ ሰሎሚት፥ (1 ዜና
23:9)
6.
ከዕዝራ ጋር
ከባቢሎን ከተመለሱ፥
የዮሲፍያ አባት፥
ሰሎሚት፥ (ዕዝ 8:10)
ሰሎሚት / Shelomoth: ይስዓራዊው፥ ሰሎሚት፥ (1
ዜና 24:22)
ሰሎሜ ~
Salome:
ሰላሜ፣ ሰላም፣ ደኅንነት... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ሰሎም፣ ሺሌም]
‘ሰላም’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው።
በሰንበት ወደ ጌታ መቃብር ከሄዱት፥ “…የዮሳም እናት ማርያም ሰሎሜም ነበሩ፥”
(ማር 15:40)
ሰሎም ~
Shallum:
ሰላም፣ ደኅንነት፣ ስምምነት፣ እርቅ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ሰሎሜ፣ ሰሎም፣ ሺሌም]
‘ሰላም’
ከሚለው ቃል
የመጣ ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
የንጉሥ ዳዊት ዘበኛ የነበረ፥ “በረኞችም ሰሎም፥ ዓቁብ፥ ጤልሞን ...” (1 ዜና 9:17)
2.
በሰማርያ አንድ ወር ያህል የነገሠ፣ የኢያቤስ ልጅ ሰሎም ፥ (2 ነገ 15:10፣ 13)
3.
የይሁዳ ልጆች ወገን የሆነ፥ የሲስማይ ልጅ፥ ሰሎም፥ (1 ዜና 2:40፣
41)
4.
የንጉሡ የኢዮስያስ ልጅ፥ ሰሎም” (1
ዜና 3:15፣ ኤር 22:11)
5.
የስምዖን ልጅ፥
ሰሎም፥ (1 ዜና 4:25)
6.
ከካህናቱ አንዱ፥ የሳዶቅ ልጅ ሰሎም፥ “አኪጦብም ሳዶቅን ወለደ ሳዶቅም ሰሎምን ወለደ” (1 ዜና 6:12፣ 13) ፣ (ዕዝ 7:2)
7.
የንፍታሌም ልጅ፥
ሰሎም፥ (1 ዜና 7:13)
8.
በንጉሥ ዳዊት
ዘመን አገልጋይ
የነበረ የቆሬ
ልጅ፥ ሰሎም፥
(1 ዜና
9:19፣ 31)
9.
ከኤፍሬም ልጆች
አለቆች፥ ሰሎም፥
(2 ዜና 28:12)
10.
በባቢሎን የምርኮ ዘመን ከነበሩት፥ ከመዘምራን አንዱ ሰሎም፥ (ዕዝ 10:24)
11.
በባቢሎን የምርኮ ዘመን ከነበሩት፥ (ዕዝ 10:41፣42)
12.
በኢየሩሳሌም እኩሌታ አለቃ የነበረ፥ የአሎኤስ ልጅ ሰሎም፥ (ነህ
3:12)
13.
የነቢዩ የኤርምያስ አጎት፥ የአናምኤል አባት ሰሎም፥ (ኤር 32:7)
14.
የበረኛው የመዕሤያ አባት፥ ሰሎም፥ (ኤር 35:4)
ሰሎሞን ~ Solomon: ስለ አማን፣ ስላማን፣ ሰለሞን፣ ሰላማዊ፣ ሰላም፣ ደኅንነት፣ ጸጥታ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ሰሎሜ፣ ሰሎም፣ ሴሌም፣ ሺሌም] ፤ [ሰላማዊ ማለት ነው / መቅቃ]
ሰሙኤል ~
Shammua:
ሰማ አምላክ፣ አዳመጠ፣ ታዘዘ... ማለት ነው። Shammua- ‘ሰማ’
ከሚለው ቃል
የመጣ ስም ነው።
ኢያሪኮ እንዲሰልሉ
በሙሴ ከተላኩት
አንዱ፥ ከሮቤል
ነገድ፥ (ዘኁ 13:4)
ሰሚራሞት ~
Shemiramoth:
ስመ ራማት፣ ታላቅ ስም፣ ከፍተኛ ዝና... ማለት ነው። (ሺህ መሪ መአት ተብሎም ይፈታል)
‘ስም’፣ ‘ራማ’ እና ‘መአት’
ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
በንጉሡ በኢዮሳፍጥ ትእዛዝ የእግዚአብሔርን የሕጉን መጽሐፍ ይዘው በይሁዳ
ያስተምሩ ከነበሩት፥
(2 ዜና 17:8)
2.
በሁለተኛው ተራ የዳዊት መዘምራን ከነበሩ፥ (1 ዜና 15:18፣ 20)
ሰማሪት ~ Shimrith: ሺህ
መሪት ማለት
ነው። የሞዓባዊቱ
የዮዛባት እናት፥
“የተማማሉበትም የአሞናዊቱ የሰምዓት
ልጅ ዛባድ፥
የሞዓባዊቱም የሰማሪት ልጅ
ዮዛባት ነበሩ።” (2 ዜና 24:26)
ሰማራያ ~ Shamariah, Shemariah:
ሺህ መሪ ያሕ፣ የሽዎች መሪ ጌታ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም-
ሳሜር፣ ሳምር፣ ሰማርያ]
‘ሺህ’ ፣ ‘መሪ’
እና ‘ያሕ’(ያሕዌ) ከሚሉ ቃላት የተገኘ ስም ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ሰማራያ / Shamariah: የሮብዓ ልጅ፥ ሰማራያ ፥ (1 ዜና 11:19)
ሰማራያ / Shemariah:
1.
በጺቅላግ ከቂስ ልጅ ከሳኦል በተሸሸገ ጊዜ ወደ ዳዊት ከመጡት፥ ሰማራያ፥ (2 ዜና 12:5)
2.
ከዕዝራ ጋር ከባቢሎን ከተመለሱት፥ ሰማራያ፥ (ዕዝ 10:`41)
3.
የካሪም ልጅ፥ ሰማራያ፥ “ሸማያ፥ ስምዖን፥ ብንያም፥ መሉክ፥ ሰማራያ”
(ዕዝ 10:32)
ሰማርያ ~ Samaria: ‘መሰማሪያ፣ የመጠበቂያ ተራራ’ ማለት
ነው። በኢየሩሳሌም
በስተሰሜን የነበረ ከተማ፥ “ከሳምርም በሁለት መክሊት ብር የሰማርያን ተራራ ገዛ ... በተራራው ባለቤት በሳምር ስም ሰማርያ ብሎ ጠራው።” (1 ነገ 16:24)
ሰማክያ ~ Semachiah:
‘አምላክ የጠበቀው’
ማለት ነው።
የሸማያ ልጅ፥ (1
ዜና 26:7) “ለሸማያ ልጆች ዖትኒ፥ ራፋኤል፥ ዖቤድ፥ ወንድሞቹም ኃያላን የነበሩ ኤልዛባድ፥
ኤልሁ፥ ሰማክያ።”
ሰማያስ ~
Ishmaiah:
ሰማ ዋስ፣ ሰማ ያሕ፣ ሕያው አዳመጠ፣ አምላክ ሰማ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ሳሙኤል፣ እስማኤል፣ ይሽማያ፣ ይሽማያ] Ishmaiah- ‘ሰማ’ እና ‘ያሕ’
(ያሕዌ) ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። ዳዊት በጺቅላግም ከቂስ ልጅ ከሳኦል በተሸሸገ ጊዜ ወደ ዳዊት ከመጡት፥ የአብድዩ ልጅ ይሽማያ፥ (1 ዜና 12፡4)
ሰማይ ~
Heaven:
ሒዋነ፣ የሕያው ቦታ፣ የዘላለማውያን ማረፊያ... ማለት ነው። [ተለዋጭ ስሞች- በቅዱስ ማደሪያው፣ መቅደሱ ከፍታ]
Heaven-
‘ሕያዋን’ ከሚለው ቃል የመጣ ስም ነው።
. መንፈሳዊ ዓለም፣ የሕያዋን መኖሪያ፥ “በመጀመሪያ እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን
ፈጠረ”
(ዘፍ 1፡1)
. ከመሬት በላይ ያለ፥ “ከላይ ሰደደ ወሰደኝም፥ ከብዙ ውኆችም አወጣኝ” (መዝ
18:16)፣ “የሰማይ መስኮቶች
ተከፍተዋልና፥ ...ከገደልም የወጣ
በወጥመድ ይያዛል።” (ኢሳ
24:18)፣ “ስለዚህ ይህን
ቃል ሁሉ
ትንቢት ትናገርባቸዋለህ፥ እንዲህም ትላቸዋለህ። እግዚአብሔር
በላይ ሆኖ
ይጮኻል፥ በቅዱስ ማደሪያውም ሆኖ ድምፁን ያሰማል በበረቱ ላይ እጅግ ... ይጮኻል።”
(ኤር 25:30)
. ሰማየ ሰማያት፥“እግዚአብሔር ከመቅደሱ ከፍታ ሆኖ ተመልክቶአልና፥ ከሰማይ ሆኖ ምድርን አይቶአልና
(መዝ 102:19)፥ ከፍ
ባለው በእስራኤል
ተራራ ላይ
እተክለዋለሁ፥ ቅርንጫፎችም
ያወጣል ፍሬም
ያፈራል ...በቅርንጫፎቹም ጥላ
በክንፍ የሚበርር ሁሉ ይጠጋል” (ሕዝ 17:23 ፥ 33:26)፣ “ዓይኖችህን ወደ ሰማይ አቅንተህ እይ፤ ከአንተም ከፍ ከፍ ያሉትን ደመናት ተመልከት።” (ኢዮ 35:5)
. ሰማየ ሰማያት፥ “... እንዲህ ያለው ሰው ከአሥራ አራት ዓመት በፊት እስከ ሦስተኛው ሰማይ ድረስ ተነጠቀ።” (2 ቆሮ 12:2)
ሰሜበር ~ Shemeber: ‘እልፍኝ’ ማለት ነው። የሰቦይ
ንጉሥ፥ “ከሰዶም ንጉሥ ከባላ፥ ከገሞራ ንጉሥ ከብርሳ፥ ከአዳማ ንጉሥ ከሰነአብ፥ ከሰቦይም
ንጉሥ ከሰሜበር፥ ዞዓር ከተባለች ከቤላ
ንጉሥም ጋር
ሰልፍ አደረጉ።” (ዘፍ 14:2)
ሰሜኢ ~ Shimei, Shimhi, Shimi:
ስሜ፣ ስም፣ ዝና፣ መጠሪያ፣ መታወቂያ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ሳሚ]
‘ሰመየ’ ከሚለው ግስ የተገኘ
ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ሰሜኢ /Shimei:
1.
የኢዮኤል ልጅ፥
ሰሜኢ፥ (1 ዜና 5:4፣5)
2.
ከሌዊ ልጆች፥ ጌድሶን ልጅ፥ ሰሜኢ፥ (ዘኁ:18)፣ (1 ዜና 6:17፣29)
3.
የፈዳያ ልጅ፥
(1 ዜና 3:19)
4.
የዘኩር ልጅ፥
(1 ዜና 4:26፣ 27)
5.
የሌዊያዊው የጌድሶን ልጅ፥ የኢኤት ልጅ፥ (1 ዜና 6:42፣ 43)
6.
የጎዶልያስ ልጅ፥
(1 ዜና 25:17)
7.
በዳዊት የወይን ቦታ የተሾመው፥ ሰሜኢ፥ (1 ዜና 27:27)
8.
የኤማን ልጅ፥
(2 ዜና 29:14)
9.
ካህኑ ሰሜኢ፥
(2 ዜና 31:12፣ 13)
10.
በዕዝራ ዘመን እንግዳ ሚስቶችን ካገቡ፥ የሐሱም ልጅ ሰሜኢ፥ (ዕዝ
10:33)
11.
ብንያማዊ የአስቴር አጎት የመርዶክዮስ ወገን፣ የቂስ ልጅ ሰሜኢ፥ (አስ 2:5)
. የኤላ ልጅ፥ “በብንያም የኤላ ልጅ ሳሚ” (1
ነገ 4:18)
. የጌራ
ልጅ-ሳሚ (1 ነገ 1:8)
ሰሜኢ / Shimhi: "ኤሊዔናይ፥ ...
ሺምራት፥ የሰሜኢ ልጆች” (1ዜና 8:21)
ሰሜኢ / Shimi: የሌዊ ልጅ ከጌድሶን ልጆች፥ “የጌድሶንም ልጆች እንደ ወገኖቻቸው ሎቤኒ፥ ሰሜኢ ናቸው።” (ዘጸ 6:17)
ሰሜጋር ~ Shamgar:
ስመ እግር፣ መንገደኛ፣ እንግዳ... ማለት
ነው። የእስራኤል
ፈራጅ የነበረ፥
የዓናት ልጅ፥
“ከእርሱም በኋላ የዓናት
ልጅ ሰሜጋር ተነሣ፥ ከፍልስጥኤማውያንም... ደግሞ
እስራኤልን አዳነ።” (መሣ 3:31)
ሰምላይ ~
Shalmai:
‘ሰላምታ፣ ምስጋና’ ማለት ነው። ከባቢሎን ምርኮ ከተመለሱ፥ የሰምላይ ልጆች ይገኙበታል፥ “የአጋባ ልጆች፥ የዓቁብ ልጆች፥ የአጋብ ልጆች፥ የሰምላይ ልጆች፥ የሐናን ልጆች፥” (ዕዝ 2:46፤ ነህ 7:48)
ሰምርኔስ ~ Smyrna: ‘እጣን’
ማለት ነው።
በታናሽቱ እስያ
ምዕራባዊ ወደብ፥
በኤፍራጠስ ወደብ
በስተሰሜን ከተማ፥
“በሰምርኔስም ወዳለው ወደ
ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ። ሞቶ የነበረው ሕያውም የሆነው ፊተኛውና መጨረሻው
እንዲህ ይላል።” (ራእይ 2:8-11)
ሰምዔ ~ Shuham: ‘ጉድጓድ ቆፋሪ’ ማለት
ነው። የዳን
ልጅ፥ “በየወገናቸው የዳን ልጆች እነዚህ ናቸው፥ ከሰምዔ የሰምዔያውያን...” (ዘኊ 26:42)
ሰሳብሳር ~ Sheshbazzar: ‘እሳተ መለኮት’ ማለት
ነው። ለዘሩባቤል
ፋርሳዊ ስም፥
“የፋርስ ንጉሥ ቂሮስም
በመዝገቡ ላይ
በነበረው በሚትሪዳጡ
እጅ አወጣቸው፥
ለይሁዳም መስፍን
ለሰሳብሳር ቈጠራቸው።” (ዕዝ
1:8፣11፥ 6:14፣ 18)
ሰራብያ ~
Sherebiah:
ሸር አብያ፣ ቸር አብ ያሕ፣ ቸር አምላክ፣ ሕያው አባት... ማለት ነው።
Sherebiah- ‘ቸር’
፣ ‘አብ’ እና ‘ያሕ’
(ሕያው) ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
ዕዝራ እና
ነህምያ በአደረጉት አገልግሎት
ስሙ አብሮ
የሚጠቀሰ ካህን፥
(ዕዝ 8:
18፣ 24-30፣ ነህ 9:4፣ 5፣ 10:12)
ሰራኩስ ~ Syracuse:
ሥራ ቀውስ፣ አፍራሽ፣ ተገንጣይ፣ በአመፅ የተለየ... ማለት
ነው። በሲሲሊ
በስተ ደቡባዊ ምሥራቅ የነበረ የወደብ ከተማ፥ ሐዋርያው ጳውሎስ ወደ ሮም ጉዞው ለሦስት
ቀናት ያረፈበት፥
“ወደ ሰራኩስም በገባን
ጊዜ ሦስት
ቀን ተቀመጥን” (ሐዋ
28:12)
ሰራፕታ ~ Sarepta, Zarephath: ‘የአንጠረኛ ሱቅ’
ማለት ነው። ነቢዩ ኤልያስ የገባበት መንደር ስም፥ “ኤልያስም በሲዶና አገር ወዳለች ወደ ሰራፕታ ወደ አንዲት መበለት እንጂ ከእነርሱ ወደ አንዲቱ አልተላከም” (ሉቃ 4:26)
ሰራፕታ / Zarephath: ‘ማቅለጫ’
ማለት ነው።
“ተነሥቶም ወደ ሰራፕታ ሄደ ወደ ከተማይቱም በር በደረሰ ጊዜ አንዲት ባልቴት በዚያ እንጨት ትለቅም
ነበር እርሱም
ጠርቶ። የምጠጣው
ጥቂት ውኃ
በጽዋ ታመጭልኝ ዘንድ
እለምንሻለሁ አላት።” (1 ነገ
17:10፤ ሉቃ 4:26)
ሰርዴስ ~
Sardis: ‘የደስታ ልዑል’ ማለት ነው። በዮሐንስ ራእይ የተጠቀሰ የቦታ
ስም፥ (ራእይ 3:1-6) “በሰርዴስም ወዳለው
ወደ ቤተ
ክርስቲያን መልአክ
እንዲህ ብለህ ጻፍ። ሰባቱ የእግዚአብሔር መናፍስትና ሰባቱ ከዋክብት ያሉት እንዲህ ይላል። ሥራህን አውቃለሁ ሕያው እንደ መሆንህ ስም አለህ ሞተህማል።”
ሰርግ ~ Feast: ፌስታ፣ ግብዣ፣ ድግስ፣ ዓመት በዓል፣ የደስታ ቀን፣ ዐውደ ዓመት... ማለት ነው። [ተለዋጭ ስሞች-
ማዕድ፣ በዓል፣ ግብዣ]
“ላባም የዚያን ስፍራ ሰዎች ሁሉ ሰበሰበ፥ ሰርግም አደረገ።” (ዘፍ 29:22)
ሰሮና ~
Saron:
በለምለም መስክነቱ የሚታወቅ ቦታ፥ “... በልዳና በሰሮናም የሚኖሩ ሁሉ እርሱን አይተው ወደ ጌታ ዘወር አሉ።” (ሐዋ 9:35)
ሰቅል~ Bekah, shekel: ሰቁል፣ ሰቀለ፣ ሚዛን ላይ አወጣ... ማለት ነው። ብር
ማለትም ነው። የእስራኤላውያን የመገበያያ
ገንዘብ፥ ከብር ቀልጦ የሚሠራ ሳንቲም፥ (ዘጸ 38:26) “እንደ መቅደሱ ሰቅል ሚዛን፥ የሰቅል ግማሽ ከተቈጠረው ከእያንዳንዱ ሰው የተሰጠ ነው ከሀያ ዓመት ጀምሮ ...” (ዘፍ 23:15)
ሰበንያ ~
Shebaniah:
ሰባነ ያሕ፣ ሰባነ ሕያው፣ ሳባውያን፣ የአምላክ ሰዎች፣ የጌታ ወገኖች፣ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም-
ሰብታ፣ ሰንበት፣ ሳባ፣ ሳባ ሰዎች፣ ሳባታይ፣ ሳባጥ፣ ሳቤህ፣ ሳቤዔ፣ ሴባ፣ ሤባ፣ ጸባዖት]
‘ሰበን’
እና ‘ያሕ’(ያሕዌ ፣ ሕያው)
ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
በእግዚአብሔር ታቦይ ፊት መለከት ይነፉ ከነበሩ አንዱ፥ ሰበንያ፥ (1ዜና 15:24)
2.
ሌዋዊው፥ ሰበንያ፥
(ነህ 9:4፣ 5)
3.
ካህኑ፥ ሰበንያ፥ “ዘኩር፥ ሰራብያ፥ ሰበንያ፥ ሆዲያ፥ ባኒ፥ ብኒኑ:” (ነህ
10:12)
4.
ሌላ ሌዋዊ፥
ሰበንያ፥ (ነህ 10:4)
ሰብታ ~
Sabtah:
ሰብ ቤት፣ ሰባት፣ ሳባት፣ ሳባ ቤት፣ የሰው ልጅ፣ ሰብአዊ፣ ቤተ ሰብ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም-
ሰበንያ፣ ሰንበት፣ ሳባ፣ ሳባ ሰዎች፣ ሳባታይ፣ ሳባጥ፣ ሳቤህ፣ ሳቤዔ፣ ሴባ፣ ሤባ፣ ጸባዖት]
‘ሰብ’ እና ‘ቤት’
ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
የኩሽ ሦስተኛ ልጅ፥ “የኩሽም ልጆች ሳባ፥ ኤውላጥ፥ ሰብታ፥ ራዕማ፥ ሰበቃታ ...”
(ዘፍ 10:7)
ሰተርቡዝናይ ~ Shethar-boznai: ‘ስውር ጠላት’ ማለት
ነው። ቤተመቅደሱ እንዳይታነጽ ጥረት ካደረጉ ሰዎች አንዱ፥ የፋርስ ወታደር፥ (ዕዝ 5:3፣ 6፥ 6:6፣ 13) “ዚያም ዘመን
በወንዝ ማዶ
የነበረው ገዥ
ተንትናይ፥ ደግሞ
ሰተርቡዝናይ፥ ተባባሪዎቻቸውም ወደ እነርሱ መጥተው፥ ይህን ቤት ትሠሩ ዘንድ፥ ይህንኑም ቅጥር ታድሱ ዘንድ ያዘዛችሁ ማን ነው? አሉአቸው።”
ሰቱር ~
Sethur:
ሰጡር፣ መሰጠር፣ መሰወር፣ መደበቅ፣ ምሥጢር ማድረግ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ምሥጢር]
‘ሰጠረ’
ከሚለው ግስ
የተገኘ ስም ነው።
ሙሴ የከነዓንን ምድር ይሰልሉ ዘንድ ከላካቸው፥ ከአሴር ነገድ የሆነ የሚካኤል ልጅ ሰቱር፥
(ዘኁ 13:13)
ሰነአብ ~ Shinab: ‘መልካም አባት’ ማለት ነው። በአብርሃም ዘመን የነበረ፥ የአዳማ
ንጉሥ፥ “ከሰዶም ንጉሥ
ከባላ፥ ከገሞራ
ንጉሥ ከብርሳ፥
ከአዳማ ንጉሥ
ከሰነአብ፥ ከሰቦይም
ንጉሥ ...ከቤላ
ንጉሥም ጋር
ሰልፍ አደረጉ።” (ዘፍ
14:2)
ሰናዖር ~
Shinar:
‘የሁለት ወንዞች አገር’ ማለት ነው። በባቢሎን አቅራቢያ የሚገኝ
የቦታ ስም፥
(ዘፍ 11:3)
“ከምሥራቅም ተነሥተው
በሄዱ ጊዜ
በሰናዖር ምድር አንድ ሜዳ አገኙ በዚያም ተቀመጡ።”
ሰናክሬም ~ Sennacherib: ‘ኃጢአት’ ማለት ነው። በንጉሥ ሕዝቅያስ
ዘመን፥ ይሁዳን
የወረረ የአሦር
ንጉሥ፣ “በንጉሡም በሕዝቅያስ
በአሥራ አራተኛው ዓመት የአሦር ንጉሥ ሰናክሬም ወደ ይሁዳ ወደ ...” (2 ነገ 18:13)
ሰንበት ~
Sabbath:
ሰብ ቤት፣ ሰባት፣ ሳባ ቤት፣ቤተ ሳባ፣ ቤተ ሰብ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ሰበንያ፣ ሰብታ፣ ሳባ፣ ሳባ ሰዎች፣ ሳባታይ፣ ሳባጥ፣ ሳቤህ፣ ሳቤዔ፣ ሴባ፣ ሤባ፣ ጸባዖት]
Sabbath- ‘ሰብ’
እና ‘ቤት’ ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
[ሰብኣት፥ ሰዎች፣ ወገኖች ፣የቅርብ ዘመዶች / ኪወክ /
አ]
[ሰብአ ቤት ፥ ቤተ ሰብ ዘመድ ፥ ወገን ነገድ፥ ሎሌ፥ ገረድ... / ደተወ / አ] [በዕብራይስጥ የቃሉ
ትርጉም ማቆም፡
መተው ማለት
ነው / መቅቃ]
፤ (ዕረፍት፣
የዕረፍት ቀን
... ተብሎም ይተረጎማል።)
ሰባተኛው ቀን፥
“እርሱም፦ እግዚአብሔር የተናገረው
ይህ ነው።
ነገ ዕረፍት፥ ለእግዚአብሔርም የተቀደሰ ሰንበት ነው
የምትጋግሩትን ጋግሩ፥ የምትቀቅሉትንም ቀቅሉ፥
የተረፈውን ሁሉ
ለነገ እንዲጠበቅ
አኑሩት አላቸው።” (ዘጸ
16:22-30)
ሰንባላጥ ~ Sanballat: ‘ብርታት’
ማለት ነው።
ነህምያ ኢየሩሳሌምን
ለመጠገን በተነሣሣበት ዘመን በሰማርያ ባለሥልጣን የነበረ፥ “ሖሮናዊውም ሰንባላጥና ባሪያው
አሞናዊ ጦብያ
ለእስራኤል ... ተበሳጩ።” (ነህ
2:10፣19፥ 4:1-12፣ 6)
ሰዓር ~ Zohar:
‘ጮራ፣ ብርሃናማ፣
ነጭ’
ማለት ነው።
1.
የኤፍሮን አባት፥
“...ሬሳዬን ከፊቴ እንድቀብር ከወደዳችሁስ ስሙኝ፥ ከሰዓር ልጅ ከኤፍሮንም ለምኑልኝ” (ዘፍ 23:8፥ 25:9)
2.
የስሞዖን ልጅ፥ “የስሞዖን ልጆች ይሙኤል፥ ያሚን፥ ኦሃድ፥ ያኪን፥ ጾሐር፥ የከነዓናዊት ልጅ ሳኡል።” (ዘፍ 46:10፤ ዘጸ 6:15)
ሰኰት፣ ሶኮ ~ Socoh: ‘ድንኳን’ ማለት ነው። በይሁዳ ነገድ የነበሩ ሁለት ከተሞች ስም፥
1. “ዓዶላም፥ ሰኰት፥ ዓዜቃ፥ ሽዓራይም፥ ዓዲታይም፥ ግዴራ፥ ግዴሮታይም አሥራ
አራት ከተሞችና
መንደሮቻቸው። (ኢያ
15:36፤ 1 ሳሙ17:1፤ 2 ዜና 11:7፥ 8:18)
2.
የይሁዳ ከተማ፥ ሶኮ፥“ሶኮ፥ ደና፥ ዳቤር የምትባለው ቂርያትሰና”
(ኢያ 15:49)
ሰኮት ~ Shochoh: [አደባባይ፣ መተላለፊያ
ማለት ነው። / ኪወክ] የቦታ ስም፥
“ፍልስጥኤማውያንም ጭፍሮቻቸውን በይሁዳ ባለው በሰኮት አከማቹ፤ በሰኮትና በዓዜቃ
መካከል በኤፌስደሚም
ሰፈሩ።”
(1 ሳሙ 17:1)
ሰይጣን~ Satan: ጠላት፣ተቃዋሚ... ማለት
ነው። ታላቁ ዘንዶ፣
የቀደመው እባብ፤
የዚህ ዓለም
ገዥ እና
በመሳሰሉት መጠሪያዎች
ይታወቃል፥ “ዓለሙንም ሁሉ የሚያስተው፥ ዲያብሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ተጣለ፤ ወደ ምድር ተጣለ መላእክቱም ከእርሱ ጋር ተጣሉ” (ራእይ
12:9፥20:2) ፣ (ዮሐ 12:31፥ 14:30)
ሰዱቃውያን ~ Sadducees: ጻድቃን፣
የሰዶቅ ተከታዮች
ማለት ነው።
“ዳሩ ግን ከፈሪሳውያንና
ከሰዱቃውያን ብዙዎች
ወደ ጥምቀቱ
ሲመጡ ባየ
ጊዜ፥ እንዲህ
አላቸው፦ እናንተ
የእፉኝት ልጆች
... ማን አመለከታችሁ?” (ማቴ
3:7)
ሰዲ ~ Sodi: ‘ውዴ፣ ወዳጄ፣
ጓደኛዬ’
ማለት ነው።
ከነዓንን እንዲሰልሉ
ከተላኩ፥ ከዜብሎን የሄደው፥ የጋዲኤል አባት፥ “ከብንያም ነገድ የራፉ ልጅ ፈልጢ ከዛብሎን ነገድ የሰዲ ልጅ ጉዲኤል” (ዘኊ 13:10)
ሰዲዮር ~ Shedeur:
‘ጨረር፣ ጮራ’
ማለት ነው።
የኤሊሱር አባት፥
“ከእናንተም ጋር የሚቆሙት
ሰዎች ስሞቻቸው
እነዚህ ናቸው
ከሮቤል የሰዲዮር ልጅ” (ዘኊ 1:5፥ 2:10፥7:30፣35፥ 10:18)
ሰዶም ~
Sodom:
በክፉ ሥራቸው ከሰማይ በወረደ እሳት ከጠፋት ከተሞች አንዱ፥ “ሎጥም ዓይኑን አነሣ፥ በዮርዳኖስ ዙሪያ ያለውንም አገር ሁሉ ውኃ የሞላበት መሆኑን አየ፤ እግዚአብሔር ሰዶምንና ገሞራን ከማጥፋቱ አስቀድሞ እስከ ዞዓር ድረስ እንደ
እግዚአብሔር ገነት
በግብፅ ምድር
አምሳል ነበረ።” (ዘፍ
13:10፤14:1-16)
ሰጢም ~ Shittim: ሰጢም፣
ሸለቆ...
ማለት ነው።
የቦታ ስም፥
“የነዌም ልጅ ኢያሱ፥ ሄዳችሁ
ምድሪቱንና ኢያሪኮን
እዩ ብሎ
ከሰጢም ሁለት
ሰላዮች በስውር
ላከ። ሄዱም
ረዓብም ወደሚሉአት
ጋለሞታ ቤት
ገቡ ...” (ኢያ 2:1)
ሰጲራ ~
Sapphira:
‘ዕንቁ፣ ልዑል፣ ቆንጆ፣ ውብ’ ማለት ነው። “ሐናንያም የተባለ አንድ ሰው ሰጲራ ከተባለች ከሚስቱ ጋር መሬት ሸጠ፥” (ሐዋ 5:1)
ሰፈጥ ~
Shaphat:
ስፍነት፣ መስፈን፣ መግዛት፣ መፍረድ፣ መዳኘት... ማለት ነው።
[ተዛማጅ ስሞች- ሳፋጥ፣ ሻፋጥ፣ ሻፍጥ]
‘ስፍነት’ ከሚለው ቃል የተገኘ ስም ነው። በዚህ ስም የሚታወቁ አራት ሰዎች አሉ።
.
ከስምዖን ነገድ የሱሬ ልጅ፥ ሰፈጥ፥ (ዘኁ 13:5)
.
የኤልሳዕ አባት፥
ሳፋጥ፥ (1 ነገ 19:16-19)
.
የሸማያ ልጅ፥
ሻፋጥ፥ (1 ዜና 3:22)
.
የዳዊት እረኞች አለቃ፣ የዓድላይ ልጅ፣ ሻፍጥ፥ (1
ዜና 27:29)
ሰፉፋም ~ Shephuphan:
‘ሰፋፋ፣ ጨመረ፣ ደመረ’ ማለት ነው። የባላ ልጅ፥ “... አቢሱ፥ ናዕማን፥ አሖዋ፥ ጌራ፥ ሰፉፋም፥ ሑራም።” (1 ዜና 8:4)
ሰፋጥያስ፣ ስፋጥያስ ~ Shephatiah:
ሕያው ገዥ፣ ሕያው ዳኛ... ማለት ነው።
1.
ንጉሥ ዳዊት ከአቢጣል የወለደው፥ “አራተኛውም የአጊት ልጅ አዶንያስ፥ አምስተኛውም የአቢጣል ልጅ ሰፋጥያስ ነበረ” (2 ሳሙ 3:4)
2.
በጺቅላግ ከዳዊት
ሠራዊት ጋር ከተቀላቀሉ፥ “ገድሮታዊው ዮዛባት፥ ኤሉዛይ፥ ኢያሪሙት ... ሀሩፋዊው ሰፋጥያስ፥” (1 ዜና 12:5)
3.
በእስራኤልም ነገዶች
ላይ አለቃ
ከነበሩ፥ የመዓካ
ልጅ፥ “..
ልጅ አልዓዛር አለቃ ነበረ በስምዖናውያን የመዓካ ልጅ ሰፋጥያስ” (1 ዜና 27:16)
4.
የይሁዳ ንጉሥ የኢዮሣፍጥ ልጅ፥ “ለእርሱም የኢዮሣፍጥ ልጆች ዓዛርያስ፥ ይሒኤል፥
ዘካርያስ፥ ዔዛርያስ፥
ሚካኤል፥ ሰፋጥያስ ...”
(2 ዜና 21:2)
5.
ከባቢሎን ምርኮ ከተመለሱ የሰፋጥያስ ልጆች፥ “የሰፋጥያስ ልጆች፥ ሦስት
መቶ ሰባ
ሁለት።”
(ዕዝ 2:4)
6.
ከባቢሎን ምርኮ
ከተመለሱ፥ “የሰፋጥያስ ልጆች፥ የሐጢል ልጆች፥ የፈክራት ልጆች፥ የሐፂቦይም ...” (ዕዝ 2:57፤ ነህ 7:59)
7.
የማታን ልጅ፥
“ኤርምያስም ለሕዝቡ ሁሉ የተናገረውን ቃል የማታን ልጅ ስፋጥያስ፥ የጳስኮርም ልጅ ጎዶልያስ ...” (ኤር 38:1-4)
ሱሔ ~
Shoa:
ሽዋ፣ ሺህ፣ የሺ፣ ብዙ፣ ሀብታም፣ ባለጸጋ... ማለት ነው።
[ተዛማጅ ስሞች- ሱሳ፣ ሱዋ፣ ሱሔ፣ ሴዋ]
Shoa- ‘ሺዋ’ ሺህ፣ ከሚለው ቁጥር የመጣ ስም ነው።
ስለ ኦሖሊባ ትንቢት ሲነገር ተያይዞ የተጠቀሰ፥ (ሕዝ 23:23)
ሱሲ ~
Susi:
ከአሥራ ሁለቱ ሰላዮች የአንዱ፣ የጋዲ አባት፥ “ከዮሴፍ ነገድ እርሱም የምናሴ ነገድ የሱሲ ልጅ ጋዲ” (ዘኊ 13:11)
ሱሲጳጥሮስ ~ Sopater: ‘ጋሻ ጃግሬ፣ አርበኛ’ ማለት
ነው። ጳውሎስ
ከግሪክ ወደ እስያ ባደረገው ጉዞ ከሸኙት፥ “የሸኙትም የቤርያው ሱሲጳጥሮስ ከተሰሎንቄ ሰዎችም አርስጥሮኮስና ሲኮንዱስ የደርቤኑም ጋይዮስና ...ነበሩ” (ሐዋ 20:4)
ሱሳ ~ Sheva: ሸቫ፣ ሳባ፣ ሰብዓ፣ ሰብ፣ ሰው... ማለት ነው። (ሸባ፣ ሺህ አባ፣ የብዙዎች አባት ተብሎም ይተረጎማል።) [ተዛማጅ ስሞች-
ሱሔ፣ ሱዋ፣ ሱሔ፣ ሴዋ]
Sheva-
‘ሰብ’ ከሚለው ቃል የመጣ
ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:
-
1.
የዳዊት ጸሐፊ፥
ሱሳ፥ (2 ሳሙ 20:26)
2.
የጊብዓ አባት
ሱሳ፥ (1 ዜና 2:49)
ሱሳ ~
Shushan:
‘አበባ’
ማለት ነው። ዳንኤል ራእዩን ያየበት ቦታ፥ “በራእዩም አየሁ ባየሁም ጊዜ በኤላም አውራጃ ባለው በሱሳ ግንብ ...” (ዳን 8:2)
ሱሪሰዳይ ~ Zurishaddai: የአምላክ ወገን፣ አምላክ የረዳው... ማለት ነው። የሰለሚኤል አባት፥ “ኤሊሱር፥ ከስምዖን የሱሪሰዳይ ልጅ ሰለሚኤል፥” (ዘኊ 1:6፥ 2:12)
ሱሪኤል ~
Zuriel:
ዘረ ኤል፣ የጌታ ወገን፣ ረዳት፣ መመኪያ... ማለት ነው።
Zuriel- ‘ዘር’
እና ‘ኤል’ ከሚሉ ሁለት ቃላት የተገኘ ስም ነው።
የሜራሪ ወገኖች
አባቶች ቤት
አለቃ፥ የአቢካኢል
ልጅ ሱሪኤል፥
(ዘኁ 3፡35)
ሱራፌል ~ Seraphim:
‘ነበልባል’ ማለት ነው። ኢሳይያስ
በአየው ራእይ፥
በጌታ ዙፋን
ላይ የቆሙ
መላእክት፥ “ሱራፌልም ከእርሱ
በላይ ቆመው
ነበር፥ ለእያንዳንዱም
ስድስት ክንፍ
ነበረው፥ በሁለት ክንፍ
ፊቱን ይሸፍን
ነበር፥ በሁለቱም
ክንፍ እግሮቹን ይሸፍን ነበር፥ በሁለቱም ክንፍ ይበር ነበር” (ኢሳ 6:2)
ሱር ~
Shur, Zur: ዙር፣ ዙሪያ፣ አጥር... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም-
ዱር] በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ: -
ሱር / Shur: የቦታ ስም፥ “አብርሃምም ከዚያ ተነሥቶ ወደ አዜብ ምድር ሄደ፥ በቃዴስና በሱር መካከልም ተቀመጠ በጌራራም በእንግድነት ተቀመጠ”
(ዘፍ 20:1) ፥ (ዘጸ 15:22)
ሱር / Zur:
. የንጉሥ ስም፥ “የተገደለችውም ምድያማዊት ስምዋ ከስቢ ነበረ እርስዋም የሱር ልጅ ነበረች...” (ዘኁ 25፡15)፣ (ዘኁ 31:8)
. ብንያማዊው፥ ዱር- (1
ዜና 8:30)
ሱባ ~ Zobah: ዘብ፣
ጠባቂ፣ ወታደር... ማለት
ነው። የአሦርያ
ክፍለ ግዛት
የነበረ፥ ሳኦል
እና ዳዊት
ከሱባ ንጉሥ
ጋር ጦርነት
አካሂደዋል፥ “ሳኦልም ... ከኤዶምያስም፥
ከሱባም ነገሥታት፥
ከፍልስጥኤማውያንም ጋር
ይዋጋ ነበር፤ በየሄደበትም
ሁሉ ድል
ይነሣ ነበር።” (1 ሳሙ
14:47፤ 2
ሳሙ 8:3፥ 10:6)
ሱባኤ ~
Shebuel:
ሰባ ኤል፣ የአምላክ ሰው፣ የሰንበት ጌታ፣ የእግዚአብሔር ሰው... ማለት
ነው። [ተዛማጅ ስም-
ሱባኤል]
Shebuel- ‘ሰብ’
እና ‘ኤል’ ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። የኤማን
ልጅ፥ (1 ዜና 25:4፣ 5)
ሱባኤል ~ Shebuel, Shubael:
ሰባ ኤል፣ የሳባ አምላክ፣ የሰንበት ጌታ፣ የእግዚአብሔር... ሰው ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም-
ሱባኤ]
‘ሰብ’ እና ‘ኤል’
ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
. ሱባኤል / Shebuel: የጌርሳም ልጆች አለቃ ሱባኤል፥ (1 ዜና 23:16)
. ሱባኤል / Shubael: “አሥራ ሦስተኛው ለሱባኤል ለልጆቹም ለወንድሞቹም ለአሥራ ሁለቱ፥” (1 ዜና 25:20)
ሱቱላ ~
Shuthelah:
የኤፍሬም ልጅ፥ “እነዚህ የሱቱላ ልጆች ናቸው፤ ከዔዴን የዔዴናውያን ወገን።”
(ዘኊ 26:35)
ሱነማይቱ ~ Shunammite:
ሰላማዊት፣ አማናዊት፣ ተባባሪ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ሱነማዊት]
‘ሰላም’
ከሚለው ቃል
የመጣ ስም ነው።
. ንጉሡ ዳዊት በሸመገለ ጊዜ ያገባት፥ “በእስራኤልም አገር ሁሉ የተዋበች ቈንጆ ፈለጉ፥ ሱነማይቱን
አቢሳንም
አገኙ፥ ወደ
ንጉሡም ይዘዋት
መጡ።”
(1 ነገ 1:3)
. ሱነማዊት-
[2 ነገ 4:12]
ሱነም ~ Shunem: ‘እጥፍ ማረፊያ’
ማለት ነው።
ለይሳኮር የተሰጠ
ከተማ፥ “ወደ ከስሎት፥ ወደ ሱነም፥ ወደ ሐፍራይም፥ ወደ ሺኦን፥ ወደ አናሐራት፥”
(ኢያ 19:19)
ሱኮት ~ Succoth: ‘ድንኳን፣ መቅደስ፣ ማደሪያ፣ መጸለያ’ ማለት ነው።
1. ከጥንታዊ ከተሞች አንዱ፥ “ያዕቆብ ግን ወደ ሱኮት ሄደ፤ በዚያም ለእርሱ ቤትን ሠራ፥
ለከብቶችም ዳሶችን
አደረገ፥ ስለዚህም የዚያን
ቦታ ስም
ሱኮት ብሎ
ጠራው።”
(ዘፍ 35:17)
2. እስራኤል ልጆች ከግብፅ ሲሔዱ ካረፋባቸው፥ “እስራኤልም ልጆች ከራምሴ ተነሥተው
ወደ ሱኮት ሄዱ፤
ከሕፃናቱም ሌላ
ስድስት መቶ
ሺህ ሰው
የሚያሕል እግረኛ
ነበረ።”
(ዘጸ 12:37፥ 13:20፤ ዘኁ33:5፣6)
ሱኮትበኖት ~ Succoth-benoth:
‘የልጆች ድንኳን’ ማለት
ነው።
የባቢሎናውያን ጣዖት ስም፥ “የባቢሎንም ሰዎች ሱኮትበኖትን ሠሩ፤ የኩታም ሰዎች ኤርጌልን
ሠሩ”
(2 ነገ 17:30)
ሱዋ ~ Shua, Suah: ሺው፣ ሺህ፣ የብዙ ቁጥር... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ሱሔ፣ ሴዋ]
Shua-
‘ሺዋ’ ከሚለው ቃል የተገኘ
ስም ነው።
. የአሴር
ልጅ፥ (1 ዜና 7:30፣ 32)
. ከነዓናዊቱ
ሴዋ-
(1 ዜና 2:3)
ሱዋ /
Suah: የጾፋ ልጅ፥ (1 ዜና 7:36) “የጾፋም ልጆች ሱዋ፥ ሐርኔፍር፥”
ሲሐ ~ Ziha: ‘ድርቅ’ ማለት ነው።
1.
ከባቢሎን ምርኮ ከተመለሱ፥ የናታኒም ልጅ፥ “ናታኒም የሲሐ ልጆች፥ የሐሡፋ ልጆች፥” (ዕዝ 2:43፤ ነህ 7:46)
2.
“ናታኒምም በዖፌል ተቀምጠው ነበር፤ ሲሐና ጊሽጳ በናታኒም ላይ ነበሩ።”
(ነህ 11:21)
ሲላ ~
Silla:
‘ሰላ፣ ተስተካከለ፣ ቀና፣ ተመቻቸ’ ማለት ነው። “ባሪያዎቹም ተነሥተው ዐመፁበት፥ ወደ ሲላ በሚወርደውም መንገድ በሚሎ ቤት ገደሉት።” (2 ነገ 12:21)
ሲላስ ~ Silas: ሥልስ፣ ሠላሽ፣ ሦስተኛ ማለት ነው። “ያን ጊዜ ሐዋርያትና ሽማግሌዎች ... ሆነው በርስያን የተባለው ይሁዳና ሲላስ ነበሩ።” (ሐዋ 15:22)
ሲምሳይ ~
Shimshai:
‘ፀሓያማ’ ማለት ነው።
Shimshai- ‘ስም’ እና ‘ሺህ’ ከሚሉ ቃላት የተገኘ ስም ነው።
ከግዞት ሲመለሱ የቤተ መቅደሱን እንደገና መታነጽ ከተቃወሙ፥ ጸሐፊው ሲምሳይ፥ (ዕዝ 4:8፣ 13፣ 17 ፣ 23...)፣ (ዕዝ 4:7)
ሲሞን ~ Simon: ስማን፣ ሰማ፣ አዳመጠ፣ ተረዳ፣ ታዘዘ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ስምዖን፣ ሲሞን፣ ሺሞን]
‘ስማ’
ከሚለው ቃል
የመጣ ስም ነው። [ሰማ ከሚለው ግስ የተገኘ ነው / መቅቃ]
ሐሰተኛ ነቢይ የነበረ፥ በኋላ ግን አምኖ በሐዋርያት የተጠመቀ፥ “ሲሞን የሚሉት አንድ ሰው ግን። እኔ ታላቅ ነኝ ብሎ...” (ሥራ 8:9)
ሲሣራ ~ Sisera: ‘የጦርነት ሰልፍ’ ማለት ነው።
1.
የከነዓን ንጉሥ፣ የኢያቢስ ሠራዊት አለቃ፥ “እግዚአብሔርም ... የሠራዊቱም አለቃ በአሕዛብ አሪሶት የተቀመጠው ሲሣራ ነበረ” (መሣ 4:2)
2.
ከባቢሎን ምርኮ ከተመለሱ የሲሣራ ልጆች፥ “የሲሣራ ልጆች፥ የቴማ
ልጆች፥ የንስያ
ልጆች፥ የሐጢፋ
ልጆች።”
(ዕዝ 2:54፤ ነህ
7:55)
ሲስማይ ~
Sisamai: የኤልዓሣ ልጅ፥
“ኤልዓሣም ሲስማይን ወለደ” (1 ዜና 2:40)
ሲባ ~ Ziba:
ዘብ፣ ዘበኛ፣ ጠባቂ ማለት ነው።
በሳዖል ቤት
አገልጋይ የነበረ፥
(2 ሳሙ 9:2-18)
ሲኒም ~ Sinim: ‘ሲናውያን፣ የደቡብ
አገር’
ማለትነው። (ኢሳ 49:12) “እነሆ፥ እነዚህ
ከሩቅ፥ እነሆም፥ እነዚህ ከሰሜንንና ከምዕራብ፥ እነዚህም ከሲኒም አገር ይመጣሉ”
ሲና ~ Sinai: ‘ቁጥቋጦ፣ እሾሃማ’ ማለት ነው። የእስራኤልም
ልጆች ማኅበር
ሁሉ ከግብፅ አገር ከወጡ በኋላ ካለፉባቸው ቦታዎች አንዱ፥ “...በኤሊምና በሲና መካከል ወዳለችው ወደ ሲን ምድረ በዳ መጡ” (ዘጽ 17:8-13)
ሲን ~ Sin: ‘ቋጥኝ’
ማለት ነው።
የግብፅ ከተማ
ስም፥ “በግብፅም ምሽግ
በሲን ላይ
መዓቴን አፈስሳለሁ፥
የኖእንም ብዛት
አጠፋለሁ።”
(ሕዝ 30:15፣16)
ሲንጤኪን ~ Syntyche:
‘እድለኛ፣ ተግባቢ’
ማለት ነው።
የፊሊፒን ቤተ ክርስቲያን አባል
የነበረች፥ ጳውሎስ
ወደ ፊሊጵስዮስ
በላከው ደብዳቤ
የጠቀሳት፥ “በአንድ አሳብ
በጌታ እንዲስማሙ
ኤዎድያንን እመክራለሁ
ሲንጤኪንንም እመክራለሁ።” (ፊሊ 4:2፣3)
ሲአራ ~
Sherah:
‘ዘር፣ ዘመድ’ ማለት ነው። የኤፍሬም ሴት ልጅ። “ሴት ልጁም
ታችኛውንና ላይኛውን
ቤትሖሮንንና ኡዜንሼራን
የሠራች ሲአራ ነበረች።” (1 ዜና 7:24)
ሲዓ ~
Sia:
‘ሃጅ’
ማለት ነው። ከምርኮ ከተመለሱ የሲዓ ልጆች ይገኙበታል፥ “የጠብዖት ልጆች፥ የኬራስ ልጆች፥ የሲዓ ልጆች፥” (ነህ 7:47)
ሲካር ~ Sychar: ‘ፍጻሜ’
ማለት ነው።
ያዕቆብ ለልጁ
ለዮሴፍ በሰጠው
ስፍራ አጠገብ የነበረ፥ የቦታ ስም፥ “ስለዚህ ያዕቆብ ለልጁ ለዮሴፍ በሰጠው ስፍራ አጠገብ
ወደምትሆን ሲካር ወደምትባል የሰማርያ ከተማ
መጣ፤”
(ዮሐ 4:5)
ሲኮንዱስ ~ Secundus: ሰከንድ፣
ቅጽበት፣ ደቃቅ... ማለት
ነው። በተሰሎንቄ
የጳውሎስ ተከታይ
የነበረ ክርስቲያን፥
“ሸኙትም የቤርያው ሱሲጳጥሮስ ከተሰሎንቄ
ሰዎችም አርስጥሮኮስና
ሲኮንዱስ የደርቤኑም
... ነበሩ፤”
(ሐዋ 20:4)
ሲዎን ~ Sion: ጽዮን፣
ጽኑዓን፣ ብርቱ፣
ኃያል፣ መከታ፣
አምባ... ማለት ነው።
[ተዛማጅ ስም- ጽዮን]
‘ጽኑ’
ከሚለው ቃል
የመጣ ስም ነው።
የተራራ ስም፥ “... ሲዎን ተራራ እስከ አርሞንዔም ድረስ” (ዘዳ 4:48)
ሲዲም ~ Siddim: ‘መስክ፣ ደልዳላ
ሥፍራ’
ማለት ነው።
የሸለቆ ስም፥
“እነዚህ ሁሉ በሲዲም ሸለቆ ተሰብስበው ተባበሩ፤ ይኸውም የጨው ባሕር ነው።”
(ዘፍ 14:3፣8፣10)
ሲድራቅ ~ Shadrach:
‘ግርማዊ’ ማለት ነው። ከሦስቱ
ጻድቃን አንዱ
በጃንደረቦቹም አለቃ
የተጠራበት ስም፥
አናንያ፥ “የጃንደረቦቹም አለቃ
ስም አወጣላቸው፤ ዳንኤልን
ብልጣሶር፥ አናንያንም
ሲድራቅ፥ ሚሳኤልንም
ሚሳቅ፥ አዛርያንም
አብደናጎ ብሎ
ጠራቸው።”
(ዳን 1:7)
ሲዶን ~
Sidon, Zidon: ‘ማደን’ ማለት ነው። ከነዓን የበኵር ልጁ፥ (ዜና 10:15) “ከነዓንም የበኵር ልጁን ሲዶንን፥ ኬጢያውያንንም፥”
ሲዶን / Zidon:
‘አዳኝ፣ አሳ አስጋሪ’ ማለት
ነው። የከነዓን የበኲር
ልጅ፥ ከተማውም
በስሙ ተጠራ፥
“ከነዓንም የበኵር ልጁን
ሲዶንን፥ ኬጢያውያንንም” (ዘፍ 10:15፣19)
ሲፋይ~
Sippai: የራፋይም ወገን፥ “ከዚህም በኋላ በጌዝር ... ሰልፍ ሆነ፤ ኩሳታዊውም ሴቦካይ ከራፋይም ወገን የነበረውን ሲፋይን ገደለ።” (1 ዜና 20:4)
ሲፓራ ~ Zipporah: ‘የመስቀል ወፍ’
ማለት ነው። ኪወክ / አ
ሲጶራ-
ሲፎራ (የሙሴ ሚስት-
ኢትዮጵያዊት)
የኢትዮጵያዊው ካህን
የራጉኤል ልጅ፣
የሙሴ ሚስት፥
“ሙሴም ከዚያ ሰው
ጋር ሊቀመጥ ወደደ፤ ልጁንም ሲፓራን ለሙሴ ሚስት ትሆነው ዘንድ ሰጠው።” (ዘጸ 2፡
21) ፣ “ሙሴም ኢትዮጵያይቱን አግብቶአልና
ባገባት በኢትዮጵያይቱ
ምክንያት ማርያምና አሮን በእርሱ ላይ ተናገሩ።” (ዘኁ 12:1)
ሳላይ ~ Sallai: ‘ቅርጫት ሠሪ’ ማለት ነው።
1.
የብንያም ወገን፥ “ከእርሱም በኋላ ጌቤና ሳላይ ዘጠኝ መቶም ሀያ ስምንት።”
(ነህ 11:8)
2.
“ከሳላይ ቃላይ፥
ከዓሞቅ ዔቤር፥”
(ነህ 12:20)
ሳሌም ~Salem, Salim:
ሳሌም፣ ሰላም፣ መረጋጋት፣ ጸጥታ፣ ደኅንነት... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ሰሎሜ፣ ሰሎም፣ ሴሌሚ፣ ሴሌም፣ ሺሌም]
‘ሰለመ’ ከሚለው ግስ የመጣ ስም ነው።
በዚህ ስም የሚታወቁ ሁለት ቦታዎች አሉ።
ሳሌም / Salem:
ካህኑ ንጉሥ
መልከጻድቅ ያስተዳድረው የነበር አገር፥ “የሳሌም ንጉሥ መልከ ጼዴቅም እንጀራንና የወይን ጠጅን አወጣ ...” (ዘፍ
14:18)
ሳሌም / Salim: ነብዮ ዮሐንስ ያጠምቅበት የነበረ አካባቢ የቦታ ስም፥ (ዮሐ 3:23)
ሳሙስ ~ Shammua, Shimea:
ሽሚ፣ ሰሚ፣ ሰማ፣ አዳመጠ፣ ተረዳ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ሰሙኤል፣ ሳምዓ ፣ ሰሙኤ]
Shammua, Shimea-
‘ሰማ’
ከሚለው ቃል የተገኘ ስም ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ሳሙስ / Shammua:
1.
በጸሎት ጊዜ ምስጋናን የሚያቀነቅን የነበር፣ የአብድያ አባት ሳሙስ፥ (ነህ
11:17)
2.
ከቢልጋ ነገድ የሆነ ካህን፥ ሳሙስ፥ (2 ሳሙ 5:14)
ሳሙስ /
Shimea:
. ንጉሥ ዳዊት ከቤርሳቤህ የወለደው፥ (1 ዜና 3:5)
. የዳዊት
ወንድም፥ ሳምዓ - (1 ዜና 20:7)
ሳሙስ ~ Shammuah: ‘ሰማ፣ አዳመጠ፣ ታዘዘ’
ማለት ነው። የዳዊት ልጅ፥ “በኢየሩሳሌምም የተወለዱለት ስማቸው ይህ ነው ሳሙስ፥” (2 ሳሙ 5:14)
ሳሙኤል ~ Samuel: ሰማ ኤል፣ ሰማ አምላክ፣ ጌታ ሰማ፣ እግዚአብሔር አዳመጠ፣ ጸሎትን ተቀበለ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም-
ሽሙኤል]
‘ሰማ’ እና ‘ኤል’
ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
[ሳሙ ኤል
ማለት የእግዚአብሔር
ስም፣ አምላካዊ ስም
ማለት ነው
/ መቅቃ] የሕልቃና
እና የሐና
ልጅ፣ ነቢዩ
ሳሙኤል፥ “የመፅነስዋም ወራት
ካለፈ በኋላ
ሐና ወንድ ልጅ ወለደች፤ እርስዋም፦ ከእግዚአብሔር ለምኜዋለሁ ስትል ስሙን ሳሙኤል ብላ
ጠራችው:”
(1 ሳሙ 1:20)
ሳሚ ~
Shimei:
ስሜ፣ ስም፣ ዝና፣ መጠሪያ፣ መታወቂያ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ሰሜኢ፣ ሣማ፣ ሳምአ ፣ ሳምዓ]
‘ስመ’
ከሚለው ግስ
የተገኘ ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
ንጉሥ ዳዊትን ይራገም የነበር ከሳኦል ቤት የሆነ የጌራ ልጅ፥ (2 ሳሙ
16:5-13)
2.
ንጉሡ ሰሎሞን በእስራኤል ሁሉ ላይ ነግሦ በነበር ጊዜ ከነበሩት አለቆች አንዱ፥ “በብንያም የኤላ ልጅ ሳሚ” (1 ነገ 4:18)
ሳማ ~ Shamma, Shammah, Shimea:
ስምዓ፣ ሰማ፣ አዳመጠ፣ ተረዳት... ማለት ነው።
‘ሰመዐ’
ከሚለው ግስ
የመጣ ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ሳማ / Shamma:
ሻማ ማለት ነው። የጾፋ ልጅ፥ (1 ዜና 7:37)
ሣማ / Shammah: ሻማ ማለት ነው።
1.
የዔሳው ልጅ የራጉኤል ልጅ፥ (ዘፍ 36:13 ፣ 17)
2.
የእሴይ ልጅ፣ የዳዊት ወንድም፥ “እሴይም ሣማን አሳለፈው ...”
(1 ሳሙ 16:9 ፣ 17:13)
3.
የአጌ ልጅ፥
(2 ሳሙ 23:11-17)
4.
“ልጅ ኤልያናን፥ አሮዳዊው ሣማ፥ ሒሮዳዊው ኤሊቃ፥” (2 ሳሙ
23:25)
5.
“የአሳን ልጆች፥ ዮናታን፥ አሮዳዊው ሣማ” (2 ሳሙ 23:33)
ሣማ / Shimea: የዳዊት
ወንድም፥ “እስራኤልንም በተገዳደረ ጊዜ የዳዊት ወንድም የሣማ ልጅ ዮናታን ገደለው።” (2 ሳሙ 21:21)
ሳማያ ~
Shemaiah:
ሰማ ያሕ፣ ሰማ አምላክ፣ ሕያው ሰማ፣ እግዚአብሔር አዳመጠ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ሰሜኢ፣ ሸማያ]
‘ሰማ’ እና ‘ያሕ’(ያሕዌ ፣ ሕያው) ከሚሉ ሁለት ቃላት የተገኘ ስም ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
. ነቢዩ ሳማያ፥ “የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እግዚአብሔር ሰው ወደ ሳማያ...”
(1 ነገ 12:22-24)
. ከባቢሎን ከተመለሱ የሴኬንያ ልጅ፥ ሸማያ፥ (ነህ 3:28 ፣ 29)
.
ከስምዖን ወገን የሆነ፥ ሰሜኢ፥ (1 ዜና 4:27)
ሳሜር ~
Shamer, Shomer: ሺህ መሪ፣ የሺህ መሪ፣ የሺህዎች አለቃ፣ የብዙዎች ጠባቂ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- (ሳሜንር) ፣ ሳምር፣ ሾሜር]
Shamer, Shomer- ‘ሺህ’ እና ‘መሪ’ ከሚሉ ቃላት የተገኘ ስም ነው።
ሳሜር / Shamer: አሴራዊው፥ “የሳሜርም ልጆች አኪ፥ ሮኦጋ፥ ይሑባ፥ አራም ነበሩ።” (1 ዜና 7:34)
ሳሜንር / Shomer: የሔቤር ልጅ፥ ሳሜንር (ሳሜርን) ፥ (1
ዜና
7:32)
. ሾሜር -
(2 ነገ 12:21)
ሳምር ~
Shemer:
ሺህ መሪ፣ የሺህ መሪ፣ የሺህዎች አለቃ፣ የብዙዎች ጠባቂ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ሳሜር፣ ሰማርያ]
በይሁዳ ንጉሥ በአሳ በሠላሳ አንደኛው ዓመት ዘንበሪ በእስራኤል ላይ አሥራ ሁለት ዓመት
ሲነግሥ በገንዘብ
የገዛው የተራራ
ስም፥ “ከሳምርም በሁለት
መክሊት ብር
የሰማርያን ተራራ
ገዛ...
በሳምር ስም
ሰማርያ ብሎ
ጠራው”
(1 ነገ 16:24)
ሳምር፣ ሻሚር ~ Shamir:
‘እሾህ፣ ሹል፣ ጫፍ’ ማለት ነው።
1.
በይሁዳ ተራራማ ክፍል የነበረ ከተማ፥ “በተራራማውም አገር ሳምር፥ የቲር፥” (ኢያ 15:48)
2.
በተራራማው የኤፍሬም አገር የነበረ፥ የእስራኤል ዳኛ፥ “ከአቤሜሌክም በኋላ ከይሳኮር ነገድ የሆነ የዱዲ ልጅ የፎሖ ልጅ ቶላ እስራኤልን
...በኤፍሬም አገር ባለችው በሳምር ተቀምጦ ነበር።” (መሣ 10:1፣2)
3.
የሚካ ልጅ፥ “የሚካ ልጅ ሻሚር የሚካ ወንድም ይሺያ” (1 ዜና
24:25)
ሳምናስ ~ Shebna:
‘ሽብና፣ ሰብእና፣ ሰውነት፣ ህልውና፣ ብርታት’ ማለት ነው። በሕዝቅኤል መንግሥት፥ ከፍተኛ ባለሥልጣን የነበረ፥ “የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በቤቱ ውስጥ ወደ ተሾመው ወደዚህ አዛዥ ወደ ሳምናስ ሂድ እንዲህም በለው” (ኢሳ 22:15)
ሳምአ ~ Shimea, Shimeah, Shimeam:
የቃሉ ትርጉም ሁለት ነው:- ስም እና ሰማ። [ተዛማጅ ስሞች-
ሳምዓ፣ ሳሙስ]
‘ሰመዐ’ ከሚለው ግስ የመጣ: ሲሆን-
ሰምዓ፣ ሰማ፣ አዳመጠ፣ ተረዳ ማለት ነው። ‘ሰየመ’ ከሚለው ግስ የመጣ
ሲሆን:-
ስምዓ፣ ሴማዊ፣
ስማዊ፣ ዝና፣
መለያ፣ መታወቂያ
ማለት ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ሳምዓ / Shimea:
1.
የዳዊት ወንድም፥ “እስራኤልንም በተገዳደረ ጊዜ የዳዊት ወንድም የሳምዓ ልጅ
ዮናታን ገደለው” (1 ዜና 20:7)
2.
የሜራሪ ልጅ፥
(1 ዜና 6:30)
3.
የሚካኤል ልጅ፥
(1 ዜና 6:39፣40)
ሳምአ /
Shimeah:
1.
የሚቅሎት ልጅ፥ “ሚቅሎት ሳምአን ወለደ ...” (1 ዜና 8:32)
2.
የዳዊት ወንድም፥ “ለአምኖንም የዳዊት ወንድም የሳምዓ ልጅ ...” (2 ሳሙ13:3)
ሳምአ / Shimeam: “ሚቅሎትም ሳምአን ወለደ ...” (1 ዜና 9:38)
ሳሞት ~ Shammoth:
ሽማት፣ ስማት፣ ስሞች ማለት ነው።
‘ስም’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው።
ከዳዊት የዘበኞቹ
አለቃ አንዱ፥
ሃሮራዊው ሳሞት፥
(1 ዜና
11:27)
ሳሞትራቄ ~ Samothracia: ‘ሰማርያውያንና ተርሴሳውያን
የሚኖሩበት’ ማለት ነው። ጳውሎስ በሐዋርያዊ ጉዞው ካለፈባቸው ቦታዎች፥ “ከጢሮአዳም ተነሥተን በቀጥታ ወደ ሳሞትራቄ በነገውም ወደ ናጱሌ በመርከብ ሄድን፤” (ሐዋ 16:11)
ሳሞን ~ Samos: ‘ኮረኮንች’
ማለት ነው።
ጳውሎስ በሐዋርያዊ
ጉዞው ካለፈባቸው ቦታዎች፥ “በማግሥቱም ... ወደ ሳሞን ተሻገርን በትሮጊሊዮም አድረን በማግሥቱ
ወደ ሚሊጢን
መጣን”
(ሐዋ 20:15)
ሳራሳር ~ Sharezer, Sherezer:
ቸር ዘር፣ ምስጉን፣ አምላካዊ፣ መልካም ወገን፣ የንጉሥ ወገን፣ መለኮታዊ... ማለት ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ሳራሳር / Sharezer: የአሦር ንጉሥ የሰናክሬ ልጅ፥ በአምላኩም በናሳራክ ቤት ሲሰግድ ልጆቹ አደራሜሌክና ሳራሳር በሰይፍ ገደሉት (2 ነገ 19:37)
ሳራሳር / Sherezer: ከቤቴል ሰዎች ወደ አምላክ የተላከ፥ (ዘካ 7:2)
ሳርጎ ~ Sargon: ‘ሰርጎ፣ ሰርጓጅ፣ ጠላቂ፣ የባሕር ልዑል’
ማለት ነው።
ከታዋቂ የአሦር
ነገሥታት አንዱ፥ “የአሦር ንጉሥ ሳርጎን ተርታንን በሰደደ ጊዜ እርሱም ወደ አዛጦን በመጣ ጊዜ አዛጦንም ወግቶ በያዛት ጊዜ፥” (ኢሳ 20:1)
ሳሮን ~ Sharon: ደልዳላ፣
ረባዳ፥ የለመለመ
መስክ... ማለት ነው። የቅድስት አገር
ክፍለ ግዛት፥
የቦታ ስም፥
“በገለዓድም ምድር በባሳን
በመንደሮቹም በሳሮንም መሰምርያዎች ሁሉ እስከ ዳርቻቸው ድረስ ተቀምጠው ነበር።” (1 ዜና 5:16፤ ኢሳ 33:9)
ሳቢላኒስ ~ Abilene: ‘ሜዳማ አገር’ ማለት ነው። በጌታ የልደት ዘመን፥ ሊሳኒዮስ ገዥ የነበረበት ከተማ፥ “ጢባርዮስ ቄሣርም በነገሠ በአሥራ አምስተኛይቱ ዓመት ... ሊሳኒዮስም በሳቢላኒስ የአራተኛው ክፍል ገዥ ሆነው ሳሉ”
(ሉቃ 3:1)
ሳባ ~ Seba, Sheba: ሰባ፣ ሰብዓ፣ ሰብ፣ ሰው... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ሰበንያ፣ ሰብታ፣ ሰንበት፣ ሳባ ሰዎች፣ ሳባታይ፣ ሳባጥ፣ ሳቤህ ፣ ሳቤዔ፣ ሴባ፣ ሤባ፣ ጸባዖት]
‘ሰብዓ’
ከሚለው ግስ
የመጣ ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ሳባ / Seba:
1.
የኩሽ ልጅ ሳባ፥ “የኩሽም ልጆች ሳባ፥ ኤውላጥ ...” (ዘፍ 10:7)
2.
ሳባውያን፥ (ኢሳ 43:3)
ሳባ /
Sheba:
1.
የራዕማ ልጅ፥ “... የራዕማ ልጆችም ሳባ፥ ድዳን ናቸው” (ዘፍ 10:7)
2.
የዮቅጣ ልጅ፥
(ዘፍ 10:28፣29)
3.
የአብርሃም ልጅ፥ የዮቅሳን ልጅ፥ “ዮቅሳንም ሳባንና ድዳንን ወለደ። ...”
(ዘፍ 25:3)
4.
“እግዚአብሔርም እንዲህ
ይላል። የግብፅ
ድካምና የኢትዮጵያ
ንግድ ቁመተ ረጅሞችም የሳባ ሰዎች ወደ አንተ ያልፋሉ ለአንተም ይሆናሉ እጆቻቸውም ታስረው
ይከተሉሃል...”
(ኢሳ 45:14)
5.
“… የዓረብና የሳባ ነገሥታት እጅ መንሻን ያቀርባሉ።” (መዝ 72:10)
. የብንያማዊ የቢክሪ ልጅ፥ ሳቤዔ - (2 ሳሙ 20:1)
. ሤባ- (ኢያ 19:2)
ሳባ ሰዎች (የሳባ ሰዎች) ~ Sabeans: ሰባያን፣ ሳባውያን፣ ሳባቤት፣ የሰው ልጅ፣ የሳባ አገር ሰዎች... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም-
ሰበንያ፣ ሰብታ፣ ሰንበት፣ ሳባ፣ ሳባታይ፣ ሳባጥ፣ ሳቤህ፣ ሳቤዔ፣ ሴባ፣ ሤባ፣ ጸባዖት]
ሳባውያን፥ “እግዚአብሔርም እንዲህ
ይላል። የግብፅ ድካምና የኢትዮጵያ ንግድ ቁመተ ረጅሞችም የሳባ ሰዎች ወደ አንተ ያልፋሉ ...” (ኢሳ
45:14)
. የሳባ ሰዎች፥ “...ኢትዮጵያንና ሳባንም ለአንተ ፋንታ ሰጥቻለሁ” (ኢሳ 43:3)
. ሰው፥ “ሰዎችና እንስሶችም በማቅ ይከደኑ...” (ኢዮ 3:8)
. ሰው፥ “የደስተኞችም ድምፅ በእርስዋ ዘንድ ነበረ ከብዙም ሰዎች ጉባኤ ...” (ሕዝ 23:42)
. ሳባውያን፥ “የሳባም ሰዎች አደጋ ጣሉ፥ ወሰዱአቸውም፥ ...” (ኢዮ 1:15)
ሳባታይ ~
Shabbethai:
ሳባተያ፣ ሳባዊያት፣ የሳባ ወገን፣ የሳባ አገር ሰዎች... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ሰበንያ፣ ሰብታ፣ ሰንበት፣ ሳባ፣ ሳባ ሰዎች፣ ሳባጥ፣ ሳቤህ፣ ሳቤዔ፣ ሴባ፣ ሤባ፣ ጸባዖት]
ከእግዚአብሔርም ቤት በሜዳ በነበረው ሥራ ላይ ከነበሩ የሌዋውያን አለቆች፥ “ደግሞ ኢያሱና ባኒ፥ ሰራብያ፥ ያሚን፥ ዓቁብ፥ ሳባታይ፥ ... ሕዝቡን ያስተምሩ ነበር።” (ነህ 8:7) ፣ (ዕዝ 10:15)፣ (ነህ 11:16)
ሳባጥ ~
Sebat:
ሰባት፣ ሳባ ቤት፣ የሳባ ልጅ፣ የሰው ልጅ፣ ቤተ ሳብ፣ ቤተ ሰብ፣ የሳባ ወገን... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም-
ሰበንያ፣ ሰብታ፣ ሰንበት፣ ሳባ፣ ሳባ ሰዎች፣ ሳባታይ፣ ሳቤህ፣ ሳቤዔ፣ ሴባ፣ ሤባ፣ ጸባዖት]
Sebat- ‘ሰብዓ’
እና ‘ቤት’ ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። የወር
ስም፥ (ዘካ 1:7)
ሳቤህ ~ Shebah: ሰብዓ፣ ሳባ፣ ሰብ፣ ሰው፣ የሰው ልጅ ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ሰበንያ፣ ሰብታ፣ ሰንበት፣ ሳባ፣ ሳባ ሰዎች፣ ሳባታይ፣ ሳባጥ፣ ሳቤዔ፣ ጸባዖት]
የቦታ ስም፥ የቤርሳቤህ የማሳጠር ስም፥ “ስምዋንም ሳቤህ ብሎ ጠራት ስለዚህም የከተማይቱ ስም እስከ ዛሬ ድረስ ቤርሳቤህ ነው” (ዘፍ 26:33)
ሳቤዔ ~
Sheba:
ሰብዓ፣ ሳባ ፣ ሰብ፣ ሰው... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ሰበንያ፣ ሰብታ፣ ሰንበት፣ ሳባ፣ ሳባ ሰዎች፣ ሳባታይ፣ ሳባጥ፣ ሳቤህ፣ ሴባ፣ ሤባ፣ ጸባዖት]
‘ሰብዐ’
ከሚለው ግስ
የመጣ ስም ነው።
የቢክሪ ልጅ ሳቤዔ፥ (2 ሳሙ 20:1) ፣ (ዘፍ 10:7)
ሳብያ ~
Zibiah:
ዘብ ያሕ፣ የተጠበቀ፣ ታላቅ፣ የተከበረ ማለት ነው።
Zibiah-
‘ዘብ’ እና ‘ያሕ’
(ያሕዌ)
ከሚሉ ቃላት
የተመሠረተ ስም
ነው። የንጉሡ የኢዮአስ
እናት፥ (2 ነገ 12:1)
ሳኔር ~
Senir, Shenir: “ሲዶናውያን አርሞንዔምን ሢርዮን ብለው ይጠሩታል፥ አሞራውያንም ሳኔር ብለው ይጠሩታል።” (ዘዳ 3:9)
ሳኔር / Shenir:
‘ማሾ፣ ፋኖስ’
ማለት ነው
። የኤርሞን
ተራራ የሶደናውያን መጥሪያ፥ “ሲዶናውያን አርሞንዔምን ሢርዮን ብለው ይጠሩታል፥ አሞራውያንም ሳኔር ብለው ይጠሩታል።” (ዘዳ 3:9፤ መኃ 4:8)
ሳንሳና ~ Sansannah: ‘የዘንባባ ቅርንጫፎች’ ማለት ነው። በይሁዳ ደቡባዊ ክፍል የነበረ ከተማ፥ “ኪሲል፥ ሔርማ፥ ጺቅላግ፥ ማድማና፥ ሳንሳና፥”
(ኢያ 15:31)
ሳኡል፣ ሳኦል ~ Shaul: ሺህ አውል፣ ኃይለኛ፣ ጀግና... ማለትነው።
1.
የስምዖን ልጅ፥ “የስሞዖን ልጆች ይሙኤል፥ ያሚን፥ ኦሃድ፥ ያኪን፥
ጾሐር፥ የከነዓናዊት
ልጅ ሳኡል።” (ዘፍ
48:10፤ ዘጸ 6:15፤ ዘኊ
26:13፤ 1
ዜና 4:24)
2.
“ሠምላም ሞተ፥
በስፍራውም በወንዝ አጠገብ ካለችው ከርሆቦት ሳኦል ነገሠ።” (ዘፍ 36:37)
ሳኦል፣ ሳውል ~ Saul: ሺህ አውል፣ ብርቱ፣ ጀግና... ማለት ነው።
1.
ከቀደሙ የኤዶም
ነገሥታት አንዱ፥ “በስፍራውም በወንዝ አጠገብ ካለችው ከርሆቦት ሳኦል ነገሠ።” (ዘፍ 36:37፣38፤1 ዜና 1:48)
2.
የመጀመሪያው የእስራኤላውያን ንጉሥ፥ (2
ሳሙ 1:25)
3.
የሐዋርያው ጳውሎስ
የቀድሞ ስም፥ ሳውል
ሳዶቅ ~ Sadoc, Zadok:
ሳዲቅ፣ ዛዲቅ፣ ጻድቅ፣ እውነተኛ፣ ሕያው ማለት ነው።
‘ጸደቀ’
ከሚለው ግስ
የተገኘ ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ሳዶቅ / Sadoc:
በጌታ የዘር ሐረግ የተጠቀሰ፥ የአኪም ልጅ፥ (ማቴ 1:14)
ሳዶቅ / Zadok:
1.
የእግዚአብሔርን ቃል ኪዳን ታቦት ተሸክመው ከመጡ፣ የአኪጦብ ልጅ፥ ሳዶቅ፥
(1 ዜና 24:3)
2.
የንጉሥ ዖዝያ አያት፣ የኢየሩሳ አባት፥ (2 ነገ 15:33፣ 2 ዜና 27:1)
3.
የኢየሩሳሌምን አጥር ከጠገኑት፣ የበዓና ልጅ፥ ሳዶቅ፥ (ነህ 3:4፣ 29)
4.
የመራዮት ልጅ፥ ሳዶቅ ፥ (1 ዜና 9:11)
ሳፋጥ ~ Shaphat: ሽፍት፣ ስፍነት፣ መስፈን፣ መፍረድ፣ መዳኘት... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ሣፋጥ፥ ሻፋጥ፣ ሰፈጥ]
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ሳፋጥ / Shaphat:
. የነቢዩ
የኤልሳዕ አባት፥
(1 ዜና 5:12)
. የሱሬ ልጅ፥ “ከስምዖን ነገድ የሱሬ ልጅ ሰፈጥ” (ዘኁ 13:5)
. የሸማያ ልጅ፥ “... የሸማያም ልጆች ሐጡስ፥ ይግኣል፥ ባርያሕ፥ ነዓርያ፥ ሻፋጥ ስድስት ነበሩ።”
(1 ዜና 3:22)
ሣፋጥ / Shaphat: የነቢዩ የኤልሳዕ አባት፥ (1
ነገ 19:18፣19)
ሴሊድ ~ Seled: ‘ደስታ፣ ፈንጠዝያ’ ማለትነው። የናዳብ ልጅ፥ (1
ዜና 2:30)
“የናዳብም ልጆች ሴሊድና አፋይም ነበሩ ሴሌድም ያለ ልጆች ሞተ”
ሴላ ~ Zillah: ‘ጥላ፣ ጠለላ፣ ግርዶሽ’ ማለት ነው። ከላሜሕም
ሚስቶች አንዷ፥
“ላሜሕም ለራሱ ሁለት ሚስቶችን አገባ የአንዲቱ ስም ዓዳ፥ የሁለተኛይቱ ስም ሴላ ነበረ።” (ዘፍ 4:19፣22)
ሴሌሚ ~
Shelomi:
ሰሎሜ፣ ሰላሜ፣ ደኅንነቴ፣ አማኔ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ሰሎሜ፣ ሰሎም፣ ሴሌም፣ ሺሌም]
‘ሰላም’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው።
ከአሴር ልጆች ነገድ አንድ አለቃ የአሒሁድ አባት፥ ሴሌሚ ፥ (ዘኁ 34:27)
ሴሌም ~
Shallum:
ሰላም፣ ስምምነት፣ እርቅ፣ አንድነት... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ሰሎሜ፣ ሰሎም፣ ሴሌሚ፣ ሺሌም]
‘ሰለመ’
ከሚለው ግስ
የመጣ ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
የቲቁዋ ልጅ፣ የነቢያቱ የሕልዳና ባል፥ (2 ነገ 22:14፣ 2
ዜና 34:23)
2.
የንፍታሌም ልጅ፥
(1 ዜና 7:13)
ሴሌስ ~ Helez: ‘ጉልበት’ ማለት ነው።
1.
ከሠላሳ የዳዊት
ዘበኞች አንዱ፥ “ፈልጣዊው፣ፈሎናዊው፣ፍሎናዊው (the
Paltite) ሴሌስ፥ የቴቁሐዊው” (2 ሳሙ
23:26፤ 1
ዜና 11:27)
2.
ኬሌስ፥ “ዓዛርያስም ኬሌስን ወለደ ኬሌስም ኤልዓሣን ወለደ”
(1 ዜና 2:39)
ሴሌውቅያ ~ Seleucia: ‘ነውጥ፣ ሞገደኛ’ ማለት
ነው። የአንጾኪያ
የባሕር ወደብ፥
“እነርሱም በመንፈስ ቅዱስ ተልከው ወደ ሴሌውቅያ ወረዱ፤ ከዚያም በመርከብ ወደ ቆጵሮስ ሄዱ።” (ሐዋ 13:4)
ሴሌፍ ~ Zalaph: ‘ቁስል’
ማለት ነው።
የኢየሩሳሌምን ቅጥር
በመጠገን የተባበረ፥ “ከእርሱ በኋላ የሰሌምያ ልጅ ሐናንያና የሴሌፍ ስድስተኛው ልጁ ሐኖን ሌላውን
ክፍል አደሱ።
ከዚያም በኋላ
የበራክያ ልጅ
ሜሱላም ...” (ነህ 3:30)
ሴሎ ~ Shiloh: ‘ስለ’
ማለት ነው።
የቦታ ስም፥
“የእስራኤል ልጆች ማኅበር
ሁሉ በሴሎ ተሰበሰቡ፥ በዚያም የመገናኛውን
ድንኳን ...” (ኢያ 18:1)
ሴሎም ~ Shelah: ‘መፍታት፣ ማላቀቅ’ ማለት ነው።
1. የይሁዳ ትንሹ ልጅ፥
“እንደ ገና ደግሞ
ወንድ ልጅን ወለደች፥ ስሙንም
ሴሎም ብላ
ጠራችው እርሱንም
በወለደች ጊዜ
ክዚብ በሚባል
አገር ነበረች።” (ዘፍ
38:5፣11፣14፣26፥ 46:10፥ ዘኊ
26:20፥ 1
ዜና 2:3፥ 4:21)
2. ሳላን፥ “አርፋክስድም ቃይንምን ወለደ ቃይንምም ሳላን ወለደ ሳላም
ዔቦርን ወለደ።” (1 ዜና 1:18፣24)
ሴሜር ~ Shamer: ሽሕ መር፥
ሌዋዊው የሞሖሊ ልጅ፥ (1
ዜና 6:46፣ 47)
ሴሜይ ~
Semei:
ሴሚ፣ ሰሚ፣ አዳማጭ፣ ታዛዥ... ማለት ነው።
‘ሰማ’
ከሚለው ቃል
የመጣ ስም ነው።
በጌታ የዘር ሐረግ የተጠቀሰ፥ የዮሴፍ ልጅ፥” (ሉቃ 3:26)
በጌታ የዘር ሐረግ፥ የማታትዩ ልጅ። “የናጌ ልጅ፥ ... ልጅ የሴሜይ ልጅ፥ የዮሴፍ ልጅ፥” (ሉቃ 3:26)
ሴም ~
Sem, Shem: ሴም፣ ስም፣ ዝና፣ እውቅና ማለት ነው።
‘ስም’
ከሚለው ቃል
የመጣ ስም ነው።
ሴም / Sem:
ከሦስቱ የኖኅ ልጆች የአንዱ ስም፥ (ሉቃ 3:36)
ሴም / Shem:
የኖኅ ልጅ፥ (ዘፍ 5:32)
ሴሲ ~
Sheshai:
‘ክቡር’ ማለት ነው። በኬብሮን የሚኖረው፣ የዔናቅ ልጅ፥ “በደቡብም በኩል
ወጡ፥ ወደ
ኬብሮንም ደረሱ
በዚያም የዔናቅ
ልጆች አኪመን፥
ሴሲ፥ ተላሚ
ነበሩ። ኬብሮንም
በግብፅ ካለችው
ከጣኔዎስ ...ነበር።” (ዘኊ
13:22)
ሴሴይ ~
Shashai:
‘ሲሳይ’
ማለት ነው። በዕዝራ ዘመን የነበረ፥ ከባኒ ልጆች አንዱ፥
“ሴሴይ፥ ሸራይ፥
ኤዝርኤል፥ ሰሌምያ፥
ሰማራያ፥ ሰሎም፥
...” (ዕዝ 10:41)
ሴሬድ ~ Sered: ‘ፍርሀት’
ማለት ነው።
የዛብሎን ልጅ፥
“የዛብሎንም ልጆች ሴሬድ፥ ኤሎን፥ ያሕልኤል።” (ዘፍ 46:14፤ ዘኊ 26:26)
ሴሮህ ~ Saruch: ሥሮች፣ ቅርንጫፍ...
ማለት። በጌታ
የዘር ሐረግ
የተጠቀሰ፥ የራጋው
ልጅ፥ “የናኮር ልጅ፥
የሴሮህ ልጅ፥
የራጋው ልጅ፥
የፋሌቅ ልጅ፥
የአቤር ልጅ፥
የሳላ ልጅ” (ሉቃ 3:35)
ሴሮሕ ~ Serug: ‘ቅርንጫፍ’
ማለት ነው።
የአብርሃም ቅድመ
አያት፥ የራግው
ልጅ፥ “ራግውም መቶ
ሠላሳ ሁለት
ዓመት ኖረ፥
ሴሮሕንም ወለደ”
(ዘፍ 11:20-23)
ሴባ ~ Shisha: ‘ተፎካከረ፣ ተገዳደረ’
ማለት ነው።
የኤልያፍና አኪያ አባት፥ “ጸሐፊዎቹም የሴባ ልጆች ኤልያፍና አኪያ፥ ታሪክ ጸሐፊም የአሒሉድ ልጅ
ኢዮሣፍጥ”
(1 ነገ 4:3)
ሴባማ ~ Shebam: ‘ሽቶ’
ማለት ነው።
ለጋድ እና
ለሮቤል ልጆች፥
ለከብቶቻቸው መሰማሪያ እንዲሆን የተሰጠ፥ የቦታ ስም፥ “እግዚአብሔር በእስራኤል ማኅበር ፊት የመታው ምድር፥ አጣሮት፥ ዲቦን፥ ኢያዜር፥ ነምራ፥ ሐሴቦን፥ ኤልያሊ፥ ሴባማ፥ ናባው፥ ባያን፥ ለእንስሶች የተመቸ ምድር ነው ...” (ዘኊ 32:3)
ሴባማ ~ Shibmah: ‘ሽቶ’
ማለት ነው።
በዮርዳኖስ በስተምሥራቅ
የሮቤል ከተማ፥
“ቂርያታይምን፥ ስማቸውም የተለወጠውን
ናባውን፥ በኣልሜዎንን፥
ሴባማን ሠሩ
እነዚህንም የሠሩአቸውን
ከተሞች ...” (ዘኊ 32:38)
ሴባማ ~ Sibmah: ‘ምርኮ’
ማለት ነው።
በዮርዳኖስ በስተ
ምሥራቅ፥ የሞዓባውያን ግዛት፥ የሮቤል ከተማ፥ “ሜፍዓት፥ ቂርያታይም፥ ሴባማ፥ በሸለቆውም ተራራ
ያለችው ጼሬትሻሐር፥” (ኢያ 13:19)
ሴቦካይ ~ Sibbechai: ‘ዘዋሪ፣ ሸማኔ’
ማለት ነው። የዳዊት ዘበኛ፥ የስምንተኛው ወር ስምንተኛ አለቃ፥ “ከዚህም በኋላ ...ሰልፍ ሆነ፥ ኩሳታዊውም ሴቦካይ ከራፋይም ወገን የነበረውን ሳፍን ገደለ።”
(2 ሳሙ 21:18፤ 1
ዜና 20:4)
ሴት ~
Seth, Sheth: ሴተ፣ ሰጠ፣ ተካ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም-
ሤት] ‘ሰጠ’ ከሚለው ግስ የመጣ ስም ነው።
ሴት / Seth: የአዳምና የሔዋን ሦስተኛ ልጅ፥ “አዳም ደግሞ ሚስቱን አወቀ ወንድ
ልጅንም ወለደች።
ስሙንም፦ ቃየን
በገደለው በአቤል
ፋንታ እግዚአብሔር
ሌላ ዘር
ተክቶልኛል ስትል
ሴት አለችው” (ዘፍ
4:25) ፥ (ዘፍ 4:25፣ 6:3) ፣ (1 ዜና 1:1)
ሤት / Sheth:
(ዘኁ 24:17)
ሴናዓ ~ Senaah: ‘እሾሐማ፣ የሾለ፣
የሰላ’
ማለት ነው።
ከባቢሎን ምርኮ
ከተመለሱ፥ “የሴናዓ ልጆች፥ ሦስት ሺህ ስድስት መቶ ሠላሳ”(ዕዝ 2:35፤ ነህ 7:38)
ሴኔ ~ Seneh: ‘ግራር’
ማለት ነው።
“ዮናታንም ... ሊሻገርበት በወደደው
መተላለፊያ መካከል
በወዲህ አንድ
ሾጣጣ በወዲህ
አንድ ሾጣጣ
ድንጋዮች ነበሩ
የአንዱም ስም ቦጼጽ የሁለተኛውም ስም ሴኔ ነበረ” (1 ሳሙ 14:4፣5)
ሴኬም ~ Shechem: ሸክም፣ ጭነት... ማለት ነው።
1.
አብርሃም የመቃብር ቦታ የገዛበት፥ የኤሞር ልጅ፥ ... የእርሻውን ክፍል ከሴኬም አባት ከኤሞር ልጆች በመቶ በጎች ገዛው።” (ዘፍ 33:19፥ 34)
2.
የምንናሴ ወገን፥
“ከሴኬም የሴኬማውያን ወገን፥ ከሸሚዳ የሸሚዳውያን ወገን፥ ከኦፌር የኦፌራውያን ወገን።” (ዘኊ26:31፤ ኢያ 17:2)
3.
በሰማርያ የነበረ ከተማ፥ “ያዕቆብም ... ወደ ሴኬም ከተማ በደኅንነት መጣ በከተማይቱም ፊት ሰፈረ።”
(ዘፍ 33:18)
ሴኬም ~
Sichem:
ሸክም፣ ጭነት፣ ትክሻ ላይ የሚያዝ... ማለት ነው። “አብራምም እስከ ሴኬም ስፍራ እስከ ሞሬ የአድባር ዛፍ ድረስ በምድር አለፈ የከነዓን ... ነበሩ።” (ዘፍ 12:6)
ሴኬንያ ~ Shecaniah: ሺህ ቅነ ያሕ፣ የሕያው ወዳጅ፣ ለአምላክ የቀረበ... ማለት ነው።
1.
ከዳዊት የካህናት ምድብ፥ አሥረኛ እጣ የወጣለት፥ ካህን፥ “አሥረኛው ለሴኬንያ፥ አሥራ
አንደኛው ለኤልያሴብ፥
አሥራ ...” (1
ዜና 24:12)
2. በሌዋዊው የይምና ልጅ የምሥራቁ ደጅ በረኛ በቆሬ ሥር ሆነው የእግዚአብሔርን መባና የተቀደሱትን ነገሮች እንዲያካፍል ከተመደቡ ካህናት አንዱ፥ “በካህናቱም ከተሞች
... በየሰሞናቸው ክፍላቸውን
በእምነት ይሰጡ
ዘንድ ዔድን፥
ሚንያሚን፥ ኢያሱ፥ ሸማያ፥ አማርያ፥ ሴኬንያ ከእጁ በታች ነበሩ።” (2 ዜና 31:15)
ሴዊ ~ Shaveh: ‘ደልዳላ’
ማለት ነው።
የሸለቆ ስም፥
“ኮሎዶጎምርንና ከእርሱ ጋር
የነበሩትን ነገሥታት
ወግቶ ከተመለሰ
በኋላም የሰዶም
ንጉሥ የንጉሥ
ሸለቆ በሆነ በሴዊ ሸለቆ ሊቀበለው ወጣ።” (ዘፍ 14:17)
ሴዋ ~
Shua, Shuah: ሽዋ፣ ሺህ፣ ብዙ ቁጥር... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ሱሔ፣ ሱዋ፣ ስዌሕ]
Shua,
Shuah- ‘ሽዋ’ ከሚለው ቃል የተገኘ ስም ነው።
ሴዋ / Shua: የነከዓናዊቱ የይሁዳ ሚስት፣ አባት፥ (1 ዜና 2:3)
ሴዋ / Shuah: “የይሁዳ ሚስት የሴዋ ልጅ ሞተች ይሁዳም ተጽናና፥ የበጎቹን ጠጕር ወደሚሸልቱት ሰዎችም ወደ ተምና ወጣ...” (ዘፍ 38:
12)
ሴዌኔ ~ Syene: ‘ክፍተት’
ማለት ነው።
በኢትዮጵያና በግብፅ
ድንበር ላይ
የነበረ የግብፅ ከተማ፥ “… የግብፅንም ምድር ከሚግዶል ጀምሮ እስከ ሴዌኔና እስከ ኢትዮጵያ
ዳርቻ ድረስ
ውድማና ባድማ
አደርጋታለሁ።”
(ሕዝ 29:10፥ 30:6)
ሴዎን ~
Sihon:
‘ጦረኛ’ ማለት ነው። እስራኤላውያን ወደ ቃል ኪዳን አገር በቀረቡ ጊዜ የነበረ፥ የአሞራውያን ንጉሥ፥ “እስራኤልም። በምድርህ ላይ እንለፍ … ወደ አሞራውያን ንጉሥ ወደ ሴዎን መልእክተኞችን ላኩ።” (ዘኊ 21:21)
ሴይር ~
Seir:
ሥር፣ ሳር፣ ሥራ ሥር... ማለት ነው። በዚህ ስም የሚታወቁ አንድ ሰውና አንድ ተራራ አሉ።
. የሰው ስም፥ “በዚያች አገር የተቀመጡ የሖሪው የሴይር ልጆች ...”
(ዘፍ 36:20-30)
. የተራራ ስም፥ የኤዶም አገር፥ “የሖር ሰዎችንም በሴይር ተራራቸው በበረሐ አጠገብ እስካለች እስከ …” (ዘፍ 14:6)
ሴዴቅያስ ~ Zedekiah, Zidkijah:
ጸደቀ ያሕ፣ ፣ ጽድቀ ዋስ፣ ሕያው ጻድቅ፣ እውነተኛ አምላክ፣ የጽድቅ አምላክ... ማለት ነው።
Zedekiah,
Zidkijah- ‘ጽድቅ’ እና ‘ሕያው’ (ዋስ) ከሚሉ ቃላት የመጣ ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ
ውስጥ ሴዴቅያስ ተብለው የተጠሩ ሦስት
አሉ። ለማገናዘብ እንዲረዳ
ቀጥሎ የቀረቡትን
ጥቅሶች ማነጻጸር ይበጃል።
ሴዴቅያስ / Zedekiah:
1.
የባቢሎን ንጉሥ የዮአኪን አጎት ማታንያን፥ ሴዴቅያስ ብሎ ጠራው፥
(2
ነገ 24:18)
2.
የክንዓና ልጅ፥
(1 ነገ 22:11)
ሴዴቅያስ / Zidkijah: ቃልኪዳኑን አትመው ከሰጡ አለቆች አንዱ፥ ካህኑ ሴዴቅያስ፥ (ነህ 10:1)
ሴድራክ ~ Hadrach: ‘ማደሪ፣ መኖሪያ’
ማለት ነው።
በነቢዩ ዘካሪያስ
የተጠቀሰ፥ የሲሪያ
አገር፥ “የእግዚአብሔር ቃል
ሸክም በሴድራክ ምድር ላይ ነው፥
በደማስቆም ላይ ያርፋል የእግዚአብሔር ዓይን ወደ ሰውና ወደ እስራኤል …” (ዘካ 9:1)
ሴጎር ~
So:
‘የእህል ሚዛን’ ማለት ነው። የግብፅ ንጉሥ፥ “የአሦርም ንጉሥ በሆሴዕ ላይ ዓመፅ አገኘ መልእክተኞችን ወደ ግብፅ ንጉሥ ወደ ሴጎር ልኮ ነበርና እንደ ልማዱም በየዓመቱ ለአሦር ንጉሥ ግብር አልሰጠምና ስለዚህ የአሦር ንጉሥ ይዞ
በወህኒ ቤት
አሰረው።”
(2 ነገ 17:4)
ሴፈርዋይም ~ Sepharvaim:
ሰፋሪያም ማለት ነው። ሰናክሬም ለሕዝቅያስ በላከው ደብዳቤ የተጠቀሰ፥ የአገር ስም፥ “የሐማት ንጉሥ፥ የአርፋድ ንጉሥ፥ የሴፈርዋይም ከተማ ንጉሥ፥ የሄናና የዒዋ ንጉሥ ወዴት አሉ?” (2 ነገ 19:13፤ ኢሳ 37:13)
ሴፎር ~
Zippor:
‘የመስቀል ወፍ፣ ብርቅዬ፣ ትንሽ ወፍ’ ማለት ነው። የሞዓብ ንጉሥ፥ “የሴፎር ልጅ ባላቅ
እስራኤል በአሞራውያን
ላይ ያደረገውን
ሁሉ አየ።”
(ዘኊ 22:2፣4)
ስልማና ~ Salamis: በቆጵሮስ
ደቡባዊ ምሥራቅ
የነበረ ከተማ፥
“በስልማናም በነበሩ ጊዜ
በአይሁድ ምኵራቦች
የእግዚአብሔርን ቃል
ሰበኩ፤ አገልጋይም
ዮሐንስ ነበራቸው” (ሐዋ 13:5)
ስልማና ~ Zalmunna: ‘ግርዶሽ፣ ጥላ’ ማለት
ነው። “ሱኮትንም ሰዎች።
የምድያምን ነገሥታት ዛብሄልንና ስልማናን ሳሳድድ፥ ደክመዋልና እኔን ለተከተሉ ሕዝብ እንጀራ፥ እባካችሁ፥ ስጡ አላቸው” (መሣ 8:5-21)
ስልምናሶር ~ Shalmaneser: ‘እሳት አምላኪ’ ማለት ነው። የአሦር ንጉሥ፥ “የአሦርም ንጉሥ ስልምናሶር በእርሱ ላይ ወጣ ሆሴዕም ተገዛለት፥ ግብርም አመጣለት።” (2 ነገ 17:3)
ስልዋኖስ ~ Silvanus: ‘ዱረኛ፣ ጫካ
የሚወድ’
ማለት ነው።
“በእኛ ማለት በእኔና በስልዋኖስ በጢሞቴዎስም በመካከላችሁ የተሰበከ የእግዚአብሔር ልጅ
ኢየሱስ ክርስቶስ
አዎንና አይደለም
አልነበረም፥ ነገር
ግን በእርሱ
አዎን ሆኖአል።” (2 ቆሮ 1:19)
ስምንት ~ Sheminith:
ሽምንት፣ ስምንት (8)
፣ ሳምንት፥ ከሰባት በመቀጠል ከዘጠኝ በፊት የሚመጣ ቁጥር... ማለት ነው።
Sheminith- ሳምንት ከሚለው ቃል የተገኘ ስም ነው።
የበገና አውታር
(ቅኝት) ቁጥር ለመግለጽ የተጠቀሰ፥
“መቲትያ፥ ኤልፍሌሁ፥ ሚቅኒያ፥ ዖቤድኤዶም፥ ይዒኤል፥ ዓዛዝያ ስምንት አውታር ባለው በገና ይዘምሩ ነበር” (1 ዜና 15:21)
ስምዖን ~ Shimeon, Simeon, Simon:
ሰማነ ፣ ሰማ፣ አዳመጠ፣ ተረዳ፣ ተገነዘበ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም-
ሲሞን]
‘ስማን’
ከሚለው ቃል
የመጣ ስም ነው።
[ሰማ ከሚለው ግስ የተገኘ ነው / መቅቃ]
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ስምዖን / Shimeon: በነቢዩ ዕዝራ ዘመን፥ በባቢሎን በምርኮ፥ እንግዶቹን ሚስቶች አግብተው፥ አያሌ ልጆችን ከወለዱ ካህናት፥ (ዕዝ 10:31)
ስምዖን / Simeon:
ልያ ለያዕቆብ
የወለደችለት ልጅ፥ “ደግሞም
ፀነሰች፥ ወንድ ልጅንም ወለደች፤ እኔ እንደ ተጠላሁ እግዚአብሔር ስለ ሰማ ይህን ደገመኝ አለች፤ ስሙንም ስምዖን ብላ ጠራችው።” (ዘፍ 29:33)
ስምዖን / Simon:
1.
ቀነናዊው ስምዖን ፥ (ማቴ 10:4)
2.
የጌታ ወንድም ተብሎ የተጠቀሰው የያቆብና የዮሳ ወንድም፥ “ይህ የጸራቢ ልጅ አይደለምን? እናቱስ ማርያም ትባል የለምን? ወንድሞቹስ ያዕቆብና ዮሳ ስምዖንም ይሁዳም አይደሉምን?” (ማቴ 13:55) ፣ “ይህስ ጸራቢው የማርያም ልጅ የያቆብም የዮሳም የይሁዳም የስምዖንም ወንድም አይደለምን? እኅቶቹስ በዚህ በእኛ ዘንድ
አይደሉምን?
አሉ …” (ማር 6:3)
3.
ጌታን ተቀብሎ ያስተናገደ ፥ ለምጻሙ ስምዖን፥ (ማቴ 26:6)
4.
የአስቆሮቱ ይሁዳ አባት፥ ስምዖን፥ (ዮሐ 6:71፣ 13:2፣ 26)
፣ (ሥራ 2:10)
5.
ቆርበት ፋቂው
ስምዖን፥ (ሥራ 9:43)
ስንጣክን ~ Stachys: ስንጣር፣ ስንጣቂ... ማለት ነው። በሮም የነበረ
ክርስቲያን፥ ጳውሎስ
በሰላምታ ደብዳቤው የጠቀሰው፥ “በክርስቶስ አብሮን ለሚሠራ ለኢሩባኖን ለምወደውም ለስንጣክን ሰላምታ
አቅርቡልኝ።”
(ሮሜ 16:9)
ስካካ ~ Secacah: ‘አጥር’ ማለት ነው። በይሁዳ ምድረ በዳ ከነበሩ ስድስት ከተሞች አንዱ፥ “በምድረ በዳ ቤትዓረባ፥ ሚዲን፥ ስካካ፥” (ኢያ 15:61)
ስዌሕ ~
Shuah:
ሽዋህ፣ ሽዋ፣ ሺህ፣ ብዙ ቁጥር... ማለት ነው።
‘ሺህ’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው።
አብርሃም ከኬጡራ
የወለደው፥ “እርስዋም ዘምራንን፥
ዮቅሳንን፥ ሜዳንን፥
ምድያምን፥ የስቦቅን፥
ስዌሕን ወለደችለት” (ዘፍ
25:2) ፥ (1 ዜና 1:32)
ስጥና ~ Sitnah:
ሰይጣናዊ፣ ጠብ፣ ጥላቻ... ማለት
ነው። ይስሐቅ
ካስቆፈራቸው የውኃ
ጉድጓዶች፥ ሁለተኛው፥
“ሌላ ጕድጓድም ማሱ፥
ስለ እርስዋም
ደግሞ ተጣሉ ስምዋንም
ስጥና ብሎ
ጠራት።”
(ዘፍ 26:21)
ስፋራድ ~ Sepharad:
‘የተለየ፣ የተከፈለ’
ማለት ነው።
“ይህም … ሰራጵታ ድረስ ይወርሳል፤ በስፋራድም የሚኖሩ የኢየሩሳሌም ምርኮኞች የደቡብን ከተሞች
ይወርሳሉ።”(አብ 1:20)
ስፋር ~Sephar: ስፍር፣ ልክ፣ መጠን፣ ቁጠር... ማለት ነው።
‘ሰፈረ’
ከሚለው ግስ
የመጣ ስም ነው።
የዮቅጣን ልጆች ከኖኅ የጥፋት ውኃ በኋላ የኖሩበት የቦታ ስም፥ (ዘፍ 10:30)
ስፎ ~ Shephi, Shepho, Zepho: ‘እራቁት’ ማለት ነው። “የሦባል ልጆች ዓልዋን፥ ማኔሐት፥ ዔባል፥ ስፎ፥ አውናም … ዓና።” (1 ዜና 1:40)
ስፎ /
Shepho: ‘ደቦ’ ማለት ነው። “የሦባል ልጆችም እነዚህ ናቸው፥ ዓልዋን፥ ማኔሐት፥ ዔባል፥ ስፎ፥ አውናም።” (ዘፍ 36:23)
ስፎ /
Zepho: ‘ማማ’ ማለት ነው። የዔሳው የልጅ ልጅ፥ የኤልፋዝ ልጅ፥ “የኤልፋዝም ልጆች እነዚህ ናቸው …
ስፎ፥ ጎቶም፥ ቄኔዝ።” (ዘፍ 36:11)
ሶምሶን ~
Samson:
‘ፀሓያማ፣ ፀሓይ የመሰለ’ ማለት ነው። ናዝራዊው፥ የማኑሄ
ልጅ፥ “ሴቲቱም ወንድ
ልጅ ወለደች፥
ስሙንም ሶምሶን
ብላ ጠራችው
ልጁም አደገ
እግዚአብሔርም ባረከው።” (መሣ 13:3-5)
ሶሳን ~ Sheshan: ‘ክቡር’
ማለት ነው።
“የአፋይምም ልጅ ይሽዒ፥
የይሽዒም ልጅ
ሶሳን፥ የሶሳንም ልጅ አሕላይ ነበረ።” (1 ዜና
2:31፣34፣35)
ሶስቴንስ ~ Sosthenes: ‘አዳኝ፣ መከታ’ ማለት
ነው። በቆሮንጦስ
የምኩራብ አለቃ
የነበረ፣ ጳውሎስን
ባለመቃወሙ በአድመኞች
የተደበደበ፥ “የግሪክ ሰዎችም
ሁሉ የምኩራብ
አለቃ ሶስቴንስን
ይዘው በወንበሩ
…” (ሐዋ 18:12-17)
ሶስና ~ Susanna: ‘አበባ፣ ጽጌሬዳ’
ማለት ነው።
የጌታን ትምህርት
ይከታተሉ ከነበሩ፥
“የሄሮድስ አዛዥ የኩዛ
ሚስት ዮሐናም
ሶስናም ብዙዎች
ሌሎችም ሆነው በገንዘባቸው ያገለግሉት ነበር” (ሉቃ 8:3)
ሶሬቅ ~
Sorek:
‘ወይን ጠጅ ቀለም’ ማለት ነው። ደሊላ የነበረችበት አገር፣ የሸለቆ
ስም፥ “ከዚህም በኋላ
በሶሬቅ ሸለቆ
የነበረች ደሊላ
የተባለች አንዲት
ሴትን ወደደ።” (መሣ 16:4)
ሶርያ፣ ሶሪያ ~ Syria: ሥራ ያሕ፣ የሕያው ሥራ፣ ያምላክ ሰራተኛ፣ የጌታ ሠራዊት... ማለት ነው። “ይስሐቅም አርባ
ዓመት ሲሆነው
ርብቃን አገባ፤
እርስዋም በሁለት
ወንዞች መካከል
ያለ የሶርያዊው የባቱኤል
ልጅና የሶርያዊው
የላባ እኅት
ናት።” (ኦሪት ዘፍጥረት
25: 20)
“ያዕቆብም የሶርያውን ሰው
ላባን ከድቶ
ኮበለለ፥ መኮብለሉንም፥
አልነገረውም።” (ኦሪት ዘፍጥረት
31
20)
ሶሪያ / syria: “የክንዓና
ልጅ ሰዴቅያስም
የብረት ቀንዶች
ሠርቶ፦ እግዚአብሔር
እንዲህ ይላል፦
ሶሪያውያንን እስኪጠፉ
ድረስ በእነዚህ
ትወጋለህ አለ።” (“2ኛ ዜና 18: 10)
ሶባብ ~
Shobab:
ሺህ አባብ፣ ሽባብ፣ የሚያባባ፣ አስፈሪ... ማለት ነው።
‘ሺህ’ እና ‘አባብ’
ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
ዳዊት ከኬብሮን ከመጣ በኋላ የተወለደ፥ ሶባብ፥ (2 ሳሙ 5:14)
2.
የኤስሮም ልጅ ካሌብ ከሚስቱ ከዓዙባ የወለደው፥ (1 ዜና 2:18)
ሶባክ ~ Shobach: ‘መስፋፋት’
ማለት ነው።
የሶርያ ንጉሥ
የወታደሮቹ አዛዥ፥ “አድርአዛርም ልኮ በወንዝ ማዶ የነበሩትን ሶርያውያን፥ አመጣ ወደ ኤላምም መጡ፥
የአድርአዛርም ሠራዊት
አለቃ ሶባክ በፊታቸው ነበረ።”
(2 ሳሙ 10:16)
ሶባይ ~
Shobai:
ሺህ አባይ፣ የሺህ አባ፣ የብዙዎች አለቃ፣ መሪ... ማለት ነው። የባቢሎን
ንጉሥ ናቡከደነፆር
ከማረካቸው ምርኮኞች
ወደ ኢየሩሳሌምና
ወደ ይሁዳ
ወደ እየከተማቸው
ከተመለሱት የአገር
ልጆች፥ የሶባይ ልጆች ይገኙበታል፥ (ነህ 7:45) ፣ (ዕዝ 2:42)
ሶቤቅ ~
Shobek:
‘መተው፣ መልቀቅ’ ማለት ነው። የቃል ኪዳኑን ደብዳቤ ከፈረሙት አንዱ፥ “አሎኤስ፥ ፈልሃ፥ ሶቤቅ፥ ሬሁም፥ ሐሰብና፥” (ነህ 10:24)
ሶገር ~
Zuar:
‘ትንሽነት’ ማለት ነው። የናትናኤል አባት፥ “ከይሳኮር የሶገር ልጅ
ናትናኤል፥”
(ዘኊ 1:8፥ 2:5፥7:18፣23፥ 10:15)
ሶጣይ ~
Sotai:
‘ተለዋዋጭ’ ማለት ነው።’ ከምርኮ ከተመለሱ፥ የሰሎሞን አገልጋዮች፥ የሶጣይ ልጆች ይገኙበታል፥
“የሰሎሞንም ባሪያዎች ልጆች
የሶጣይ ልጆች፥
የሶፌሬት ልጆች፥
የፍሩዳ ልጆች” (ዕዝ
2:55፤ ነህ 7:57)
ሶፋር ~ Zophar: ‘ድምቢጥ’ ማለትነው። ከሦስቱ የኢዮብ
ወዳጆች አንዱ፥
“...ቴማናዊው ኤልፋዝ፥ ሹሐዊው በልዳዶስ፥ ነዕማታዊው ሶፋር ነበሩ። እነርሱም ሊያዝኑለትና ሊያጽናኑት በአንድነት ወደ እርሱ ለመምጣት ተስማሙ።” (ኢዮ 2:11፥ 11:1፥
20:1፥ 42:9)
ሶፌሬት ~ Sophereth: ስፍረት፣ ሰፋሪያት፣ ቆጣሪያት፣
ጸሐፍት... ማለት ነው።
ከባቢሎን ምርኮ ከተመለሱ፥ የሶፌሬት ልጆች ይገኙበታል፥ “የሰሎሞንም ባሪያዎች ልጆች የሶጣይ ልጆች፥ የሶፌሬት ልጆች፥ የፍሩዳ ልጆች፥” (ዕዝ 2:55፤ ነህ 7:57)
ሶፎንያስ ~ Zephaniah: ጸፋነ
ዋስ፣ ጭፈነ ያሕ፣ ጠፋነ ያሕ፣
በሕያው የጠፋ፣
አምላክ የጋረደው፣
ጌታ የሸሸገው... ማለት ነው።
1.
የኵሲ ልጅ፥
ነቢዩ፥ “በይሁዳ ንጉሥ
በአሞጽ ልጅ በኢዮስያስ ዘመን ወደ ሕዝቅያስ ልጅ ወደ አማርያ ልጅ ወደ ጎዶልያስ ልጅ ወደ ኵሲ ልጅ ወደ ሶፎንያስ የመጣ የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው።” (ሶፎ 1:1)
2. የኢዮስያስ
አባት፥ “ከባቢሎን ከመጡት
ምርኮኞች ከሔልዳይና ከጦብያ
ከዮዳኤም ውሰድ፤
በዚያም ቀን መጥተህ
ወደ ሶፎንያስ ልጅ
ወደ ኢዮስያስ ቤት
ግባ።” (ዘካ 6:10)
No comments:
Post a Comment