ሀ ለ ሐ መ ሠ ረ ሰ ሸ ቀ በ ተ ቸ ኀ ነ ኘ አ ከ ኸ ወ ዐ ዘ ዠ የ ደ ጀ ገ ጠ ጨ ጰ ጸ ፀ ፈ ፐ
ለሃይሮኢ ~ Lahairoi: ‘ያለ እና
የሚያየኝ’
ማለት ነው።
አጋር በምደረ በዳ ስትንከራተት ካለፈችባቸው
ቦታዎች፥ “ይስሐቅም ብኤርለሃይሮኢ በሚሉአት
ምንጭ መንገድ መጣ በአዜብ ምድር ተቀምጦ ነበርና።” (ዘፍ 24:62)
ለሕሚ ~ Lahmi: ‘ጦረኛ’
ማለት ነው።
የጎልያድ ወንድም፥
“ደግሞም ከፍልስጥኤማውያን ጋር ሰልፍ ነበረ የያዒርም ልጅ ኤልያናን የጦሩ የቦ እንደ ሸማኔ መጠቅለያ የነበረውን የጌት ሰው የጎልያድን ወንድም ለሕሚን ገደለ” (1 ዜና 20:5)
ለሕማስ ~
Lahmam:
‘መኖ፣ ቀለብ፣ ምግብ’ ማለት ነው። በይሁዳ በደልዳላው ክፍል የነበረ ከተማ፥
“ኦዶላም፥ ከቦን፥ ለሕማስ፥
ኪትሊሽ፥ ግዴሮት፥
ቤትዳጎን፥ ናዕማ፥
መቄዳ አሥራ
ስድስት ከተሞችና
መደሮቻቸው”
(ኢያ 15:40)
ለቁም ~ Lakum:
ለመቆም፣ ለመነሣት፣ ለመጽናት፣ ለመመከት… ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ቀሙኤል፣ ቁሚ፣ አኪቃም፣ አዶኒቃም፣ ኢዮአቄም፣ ዓዝሪቃም፣ ኤልያቄም፣ ያቂም፣ ዮቂም፣ ዮአቂም]
‘ቆመ’ ከሚለው ግስ የመጣ ስም ነው። ለንፍታሌም ልጆች ነገድ ርስት የተሰጠ፥ የቦታ
ስም፥ (ኢያ 19:33)
ለቦና ~
Lebonah:
ልቦና፣ ልባም፣ ደፋር፣ ጀግና፣ አስተዋይ… ማለት ነው።
[ተዛማጅ ስሞች- ልባዎት፣ ልብና፣ ልብድዮስ]
‘ልብ’ ከሚለው ቃል የመጣ ስም ነው። በሴሎ አጠገብ ከቤቴል በስተ ሰሜን የሚገኝ የከተማ
ስም፥ (መሣ 21:19)
ለአዳን ~
Laadan:
ለዳን፣ ለዳኛ፣ ለፍርድ፣ ለሥርዓት… ማለት ነው።
‘ዳኘ’
ከሚለው ግስ
የተገኘ ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
የኤፍሬም ልጅ፥
(1 ዜና 7:26)
2.
“ከጌድሶናውያን ለአዳንና
ሰሜኢ ነበሩ።” (1 ዜና
23:7፣ 8፣ 9፣ 26:21)
ለኡማውያን ~ Leummim: ‘ሕዝብ’
ማለት ነው።
የድዳን ልጅ፥
“ዮቅሳንም ሳባንና ድዳንን ወለደ። የድዳንም ልጆች አሦርያውያን፥ ለጡሳውያን፥ ለኡማውያን ናቸው።” (ዘፍ 25:3)
ለዓዳ ~ Laadah: ‘መመሪያ’
ማለት ነው።
የሴሎ ልጅ፥
“የይሁዳም ልጅ የሴሎም ልጆች የሌካ አባት ዔር፥ የመሪሳ አባት ለዓዳ፥ ከአሽቤዓ ቤት የሚሆኑ ጥሩ በፍታ
የሚሠሩ ወገኖች፥” (1 ዜና 4:21)
ለኪሶ ~ Lachish:
‘የማይበገር፣ የማይናወጥ፣
የማይሰበር፣ የማይታጠፍ፣
ጠንካራ’
ማለት ነው። የአሞራውያን ግዛት የሆነ፥ የስምዖን አዋሳኝ፥ በኢየሩሳሌም በስተደቡብ የሚገኝ ከተማ፥ “ስለዚህም የኢየሩሳሌም ንጉሥ ... ወደ ለኪሶ ንጉሥም ወደ ያፊዓ፥ ወደ
አዶላም ንጉሥም
ወደ ዳቤር
ልኮ። ወደ
እኔ ውጡ፥” (ኢያ
10:3፣ 5)
ለጡሳውያን ~ Letushim: ‘ውቅር፣ ቅጥቅጥ’ ማለት
ነው። የድዳን
ሁለተኛ ልጅ፥
“... የድዳንም ልጆች
አሦርያውያን፥ ለጡሳውያን፥
ለኡማውያን ናቸው” (ዘፍ 25:3)
ለፊዶት ~
Lapidoth:
‘ብርሃን፣ ስልጡን፣ ንቁ’
ማለት ነው። “በዚያ ጊዜም ነቢይቱ የለፊዶት ሚስት ዲቦራ በእስራኤል ላይ ትፈርድ ነበረች” (መሣ 4:4)
ሉሒት ~
Luhith:
‘ርብራብ’ ማለት ነው። በሞዓብ የነበረ የቦታ ስም፥ “ልቤ ስለ
ሞዓብ ጮኸ
ከእርስዋም የሚሸሹ
ወደ ዞዓር
ወደ ዔግላት
ሺሊሺያ ኰበለሉ በሉሒት ዓቀበት ላይ እያለቀሱ ይወጣሉ...” (ኢሳ 15:5)
ሉቃስ ~ Lucas, Luke: ሊቅ ዋስ፣ ሊቅ፣ ዐዋቂ፣ አስተዋይ፣ የተማረ፣ ቀዳሚ፣ መንገድ መሪ፣ አስተማሪ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ሉክዮስ፣ ሉቂዮስ፣ ሊቅሒ፣ ሌካ]
‘ሊቅ’ እና ’ዋስ’
ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
ሉቃስ / Lucas: የቅዱስ ጳውሎስ አገልጋይ የነበረ፥ ሉቃስ፥ (ፊል 1:24)
ሉቃስ / Luke:
ሐኪም የነበረ፣ ወንጌላዊው ሉቃስ፥ (ቆላ 4:14)
ሉክዮስ ~
Lucius:
ሊቅ ዋስ፣ ዐዋቂ፣ አስተዋይ፣ የተማረ፣ መንገድ መሪ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ሉቃስ፣ ሉቂዮስ፣ ሊቅሒ፣ ሌካ]
‘ሊቅ’ እና ‘ዋስ’
ከሚሉ ሁለት ቃላት የተገኘ ስም ነው።
. በአንጾኪያ ባለችው ቤተ ክርስቲያን ነቢይና መምህር የነበረ፥ ሉክዮስ፥ (ሥራ 13:1)
. ‘የጴጥሮስ መልእክት ወደ ሮሜ ሰዎች’ን የጻፈ፥ ጤርጥዮስ የጠቀሰው አገልጋይ፥
ሉክዮስ፥ (ሮማ 16:21)
ሉድ ~ Lud: ‘ግጭት፣ ብጥብጥ’ ማለት
ነው። ከሴም
ልጆች አራተኛው፥
“የሴምም ልጆች ኤላም፥ አሦር፥ አርፋክስድ፥ ሉድ፥ አራም ናቸው።” (ዘፍ 10:22)
ሊሳኒዮስ ~ Lysanias: ልሳነ
ዋስ፣ አጽናኝ
ንግግር፣ ሐዘንን
የሚያርቅ...
ማለት ነው። በሳቢላኒስ የአራተኛው ክፍል ገዥ የነበረ፥ “ጢባርዮስ ቄሣርም በነገሠ በአሥራ አምስተኛይቱ ዓመት ... ሊሳኒዮስም በሳቢላኒስ
የአራተኛው ክፍል
ገዥ ሆነው
ሳሉ።” (ሉቃ 3:1)
ሊቃኦንያ ~ Lycaonia: ‘የተኩላ አገር’ ማለት
ነው። በታንሿ
እስያ የሚገኝ
ደሴት፥ “ሕዝቡም ጳውሎስ
ያደረገውን ባዩ
ጊዜ ... በሊቃኦንያ ቋንቋ።
አማልክት ሰዎችን መስለው ወደ እኛ ወርደዋል አሉ” (ሐዋ 14:11)
ሊቅሒ ~
Likhi:
ሊቅ፣ ቀዳሚ፣ አስተዋይ፣ ዐዋቂ፣ ምሁር፣ መሪ፣ ተመራማሪ፣ በዕድሜ የበለጠ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ሉቃስ፣ ሉክዮስ፣ ሉቂዮስ፣ ሌካ]
‘ላቀ’
ከሚለው ግስ
የተገኘ ስም ነው። የምናሴ ወገን፣ የሸሚዳ ልጅ፣ ሊቅሒ፥ (1 ዜና 7:19)
ሊቢያ ~
Libya:
ልበያ፣ ልብ ያሕ፣ ልበ ሕያው፣ የአምላክ ልብ፣ እግዚአብሔር የወደደው... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ልባዎት፣ ልብና፣ ልብድዮስ]
‘ልብ’ እና ‘ያሕ’
ከሚሉ ቃላት የተገኘ ያገር ስም ነው።
በሰሜን ምሥራቅ
አፍሪቃ የሚግኝ
ግዛት (ግብፅን ሳይጨምር) ፥
(ሥራ 2:10)
ሊባኖስ ~ Lebanon: ‘ነጭ’
ማለት ነው።
ከፍተኛና ረጅሙ
የሶሪያ ተራራ፥
“እስከ ሴይርም ከሚያወጣው
ወና ከሆነው
ተራራ ጀምሮ
ከአርሞንዔም ተራራ በታች በሊባኖስም ሸለቆ ውስጥ እስካለው ...” (ኢያ 11:17)
[ፍችው፥ ቧሒት እንደማለት፤ ነጭ ነጮ ወይም ነጫም ማለት ነው። / ኪወክ / አ]
ሊኖስ ~
Linus:
በሮም የነበረ ክርስቲያን፥ “...ኤውግሎስና ጱዴስ ሊኖስም ቅላውዲያም
ወንድሞችም ሁሉ
ሰላምታ ያቀርቡልሃል።” (2 ጢሞ 4:21)
ላሃድ ~ Lahad: “ማመን፣ ማመስገን’ ማለት
ነው። የኢኤት
ልጅ፥ “የሦባልም ልጅ ራያ ኢኤትን ወለደ ኢኤትም አሑማይንና ላሃድን ወለደ...” (1 ዜና 4:2)
ላህቢም ~ Lehabim:
‘ነበልባል’ ማለት ነው። የአገር ስም፥ “ምጽራይምም ሉዲምን፥ ዐናሚምን፥ ላህቢምን፥ ነፍታሌምን፥ ፈትሩሲምን...” (ዘፍ 10:13)
ላልተማሩ ~ Barbarian:
በር በሪያን፣ የባሪያ ልጅ፣ ሕገ ኦሪትን ያላወቀ፣ ነጻ ያልወጣ፣ እንደተፈጠረ ያለ ሕዝብ፣ ለእግዚአብሔር መንግሥት እንግዳ... ማለት ነው። [ተለዋጭ ስሞች- አረማውያን፣ እንግዳ]
Barbarian- ‘በር’
፣ ‘በረ’ እና ‘ያሕ’
ከሚሉ ቃላት የተገኘ ስም ነው። ሕገ እግዚአብሔርን ያላወቁ፥ “ለግሪክ ሰዎችና ላልተማሩም፥ ለጥበበኞችና ለማያስተውሉም ዕዳ
አለብኝ፤”
(ሮሜ 1:14)
ላማ ~
Lama:
ለምን፣ ለምንድን ነው፣ ስለ ምን... ማለት ነው።
ጌታ በመስቀል ላይ ሆኖ ከተናገራቸው ቃላት፥ “በዘጠኝ ሰዓትም ኢየሱስ፦ ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ? ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህም። አምላኬ አምላኬ፥ ስለ ምን
ተውኸኝ?
ማለት ነው።” (ማቴ 27:46)
ላሜሕ ~
Lamech:
የሚመታ፣ ምች፣ መች፣ ብርቱ... ማለት ነው።
Lamech-
‘ለመች’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው።
. የቃየን አምስተኛ ትውልድ የሆነው፥ (ዘፍ 4:18-24)
. የማቱሳላ ልጅ ሁኖ የኖኅ አባት፥ (ዘፍ 5:25-31
፣ ሉቃ 3:36)
ላሲያ ~ Lasea:
‘ጠቢብ’ ማለት ነው። የከተማ
ስም፥ “በጭንቅም ጥግ
ጥጉን አልፈን ለላሲያ ከተማ ወደ ቀረበች ...ስፍራ መጣን።” (ሐዋ 27:8)
ላባ ~ Laban: ‘ነጭ፣ አንጸባራቂ’
ማለት ነው።
የይስሐቅ ሚስት፣
የርብቃ ወንድም፥ (ዘፍ 24:10፣29-60፥ 27:43፥ 29:5) “ለርብቃም ላባ የተባለ ወንድም ነበራት ላባም ወደ ውጪ ወደ ውኃው ምንጭ ወደ ሰውዮው ሮጠ።”
ሌሒ ~ Lehi: መንጋጋ፣ አገጭ...
ማለት ነው።
በይሁዳ የነበረ
የቦታ ስም፥
“ፍልስጥኤምማውያንም ወጡ፥ ... በሌሒ ላይም ተበታትነው ተቀመጡ” (መሣ
15:9፣14፣19)
ሌሳ ~ Laish: ‘አንበሳ’
ማለት ነው።
የፈልጢ አባት፥
የዳዊት ሚስት፥
የሚልካ የመጀመሪያ ባል፥ “ሳኦል ግን የዳዊትን ሚስት ልጁን ሜልኮልን አገሩ ጋሊም ለነበረው
ለሌሳ ልጅ
ለፈልጢ ሰጥቶ
ነበር።”
(1 ሳሙ 25:44፤ 2 ሳሙ 3:15)
ሌሼም ~ Leshem: ለሽም፣
ለስም፣ ለመጠሪያ፣
ለመታወቂያ... ማለት ነው።
‘ስም’ ከሚለው ቃል የመጣ ስም ነው። ዳን ተብላ የተጠራች፥ የቦታ ስም፥ “የዳንም ልጆች ዳርቻ አልበቃቸውም የዳንም ልጆች ከሌሼም ጋር ሊዋጉ ወጡ፥
...በአባታቸው በዳን ስም ዳን ብለው ጠሩአት።” (ኢያ 19:47)
ሌካ ~
Lecah:
ሊቅ፣ ቀዳሚ፣ ዐዋቂ፣ የተማረ፣ ንቁ፣ አስተዋይ... ማለት ነው።
[ተዛማጅ ስሞች- ሉቃስ፣ ሉክዮስ፣ ሉቂዮስ፣ ሊቅሒ]
‘ላቀ’
ከሚለው ግስ
የተገኘ ስም ነው። በይሁዳ የዘር ሐረግ የተጠቀሰው ሌካ፥ (1 ዜና 4:21)
ሌዊ ~
Levi:
ሊቬ፣ ልቤ፣ ልባዊ፣ ተወዳጅ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ሊቢያ፣ ልባዎት፣ ልብና፣ ልብድዮስ፣ ሌዋውያን]
‘ልብ’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች: -
1. የያዕቆብና የልያ ሦስተኛ ልጅ፥ “ደግሞም ፀነሰች፥ ወንድ ልጅንም ወለደች አሁንም ባሌ ወደ እኔ ይጠጋል፥ ሦስት ወንዶች ልጆችን ወልጄለታለሁና አለች ስለዚህም ስሙን ሌዊ ብላ ጠራችው።” (ዘፍ 29:34)
2. በጌታ የዘር ሐረግ የተጠቀሰ፥ የሚልኪ ልጅ፥ (ሉቃ 3:24፣ 29)
3. የእልፍዮስ ልጅ፣ ሐዋርያው ሌዊ፥ (ማር 2:14) ፣ (ሉቃ 5:27፣ 29)
[ስሙ “ይጠጋል”
ማለት ነው።
/ መቅቃ]
ሌዋውያን ~ Levites: ልባውያን፣ ልባዊ፣ የተወደዱ፣ የሌዊ ወገን፣ የሌዊ አገር ሰዎች... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም-
ሌዊ]
. የአሮን የልጅ ልጅ ፊንሐስ የሌዋውያን አባት ተብሎ ተጠራ፥ (ዘጸ 6:25)
. ለእግዚአብሔር በኩራት
ሆነው ስለተለዩ በእስራኤል ርስት አልነበራቸውም፥ (1 ነገ 8:4፣ ዕዝ 2:70)
ልሄኔሲፎሩ ~ Onesiphorus: “አትራፊ’
ማለት ነው።
በኤፌሶን የነበረ ክርስቲያን፥
ለጳውሎስ በሮም
በጎ ነገርን
ያደረገ፥ “ጌታ ልሄኔሲፎሩ ቤተ ሰዎች ምሕረትን
ይስጥ፥ ብዙ
ጊዜ አሳርፎኛልና፤” (2 ጢሞ
1:16-18፥4:19)
ልስጥራን ~ Lystra: ‘የተበተኑ’
ማለት ነው።
“ወደ ደርቤንና ወደ ልስጥራንም ደረሰ።
እነሆም፥ በዚያ
የአንዲት ያመነች
አይሁዳዊት ልጅ
ጢሞቴዎስ የሚባል
አንድ ደቀ
መዝሙር ነበረ፤
አባቱ ግን
የግሪክ ሰው
ነበረ”
(ሐዋ 14:1)
ልቅሶ ~ Baca: በፍልስጥኤም
አገር ያለ
ሸለቆ፥ ወደ
ሕያው ቤተ
መቅደስ የሚሸሹበት፥ እስራኤላውያን በዓይነ ኅሊናቸው ያዩት ቦታ፥ “በልቅሶ ሸለቆ ውስጥ በወሰነው ስፍራ የሕግ መምህር
በረከትን ይሰጣልና።” (መዝ 84:6)
ልባዎት ~
Lebaoth:
ልባት፣ ልባም፣ ደፋር፣ ጀግና፣ አስተዋይ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ሊቢያ፣ ሌዊ፣
ልብና፣ ልብድዮስ]
‘ልብ’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው። በነቢዩ ኢያሱ የተጠቀሰ የከተማ ስም፥ ልባዎት፥ (ኢያ 15:32)
ልብና ~ Libnah: ልቦና፣
ልቡና፣ ልባዊ፣
አስተዋይ... ማለት ነው። [ተዛማጅ
ስሞች-
ሊቢያ፣ ሌዊ፣ ልባዎት፣ ልብድዮስ]
‘ልብ’ ከሚለው ቃል የመጣ ስም ነው። ‘ሌበናን’
የሚለው የአገር ስም የተገኘው ከዚህ ነው።
እስራኤላውያን ከግብፅ ከወጡ በኋላ ካለፉባቸው ቦታዎች፥ ልብና፥ (ዘኁ 33:20፣ 21) ፣ (ኢያ 10:29-32፣ 12:15)
ልብድዮስ ~
Lebbaeus:
ልበ ዋስ፣ ልባዊ ዋስ፣ ደፋር፣ አስተዋይ፣ ጀግና... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ሊቢያ፣ ሌዊ፣ ልባዎት፣ ልብና]
Lebbaeus- ‘ልብ’
እና ‘ዋስ’ ከሚሉ ቃላት የተገኘ ስም ነው።
ከአሥራ ሁለቱ
ሐዋርያት አንዱ
የሆነው፣ የሐዋርያው
የታዴዎስ ሁለተኛ
ስም፥ “...ማቴዎስም፥ የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብም ታዴዎስም የተባለው ልብድዮስ፥” (ማቴ
10:3)
ልያ ~
Leah:
‘ጠውላጋ’ ማለት ነው። የላባ ትልቋ ልጅ፥ የያዕቆብ ሁለተኛ ሚስት፥ “ለላባም ሁለት ሴቶች ልጆች ነበሩት የታላቂቱ ስም ልያ የታናሺቱ ስም ራሔል
ነበረ።”
(ዘፍ 29:16)
ልዳ ~
Lydda:
‘ግጭት፣ ብጥብጥ’ ማለት ነው። “ጴጥሮስም በየስፍራው ሁሉ
ሲዞር በልዳ ወደሚኖሩ ቅዱሳን ደግሞ
ወረደ።”
(ሐዋ 9:32፣35፣38)
ሎሩሃማ ~ Lo-ruhamah: ‘ምሕረት ያጣ፣
ይቅርታ የሌለው፣ የተረገመ’ ማለት ነው። “ደግሞ ፀነሰች
ሴት ልጅንም ወለደች።
እግዚአብሔርም፦ ይቅር
እላቸው ዘንድ
የእስራኤልን ቤት
ከእንግዲህ ወዲህ
አልምርምና ስምዋን
ሎሩሃማ ብለህ
ጥራት”
(ሆሴ 1:6፥ 2:23)
ሎቤኒ ~ Libni: ‘ነጭ’
ማለት ነው።
የጌድሶን ልጅ፥
የሌዊ ወገን፥
“የጌድሶንም ልጆች እንደ ወገኖቻቸው ሎቤኒ፥ ሰሜኢ ናቸው” (ዘጸ 6:17፤ ዘኊ 3:18፣21)
ሎዓሚ ~
Lo-ammi:
‘ኢአማንያን፣ ያላመነ፣ ሕዝቤ ያልሆነ’ ማለት ነው። (ሆሴ 1:9፣ 10)
“እግዚአብሔርም፦ ሕዝቤ
አይደላችሁምና፥ እኔም
አምላክ አልሆናችሁምና
ስሙን ሎዓሚ ብለህ ጥራው አለው።”
ሎዛ ~
Luz:
ለውዛ፣ ለውዝ፣ የለውዝ ተክል... ማለት ነው።
.
ቤቴል ተብላ የተጠራች፥ ጥንታዊ የከነዓን ከተማ፥ “ያዕቆብም ያንን ስፍራ ቤቴል ብሎ ጠራው አስቀድሞ ግን የዚያች ከተማ ስም ሎዛ ነበረ።” (ዘፍ
28:19፣ 35:6)
.
በኬጢያውያን አገር የነበረ የቦታ ስም፥ “...
ስምዋንም ሎዛ ብሎ ጠራት...”
(መሣ 1:26)
[...ለውዝ፥ ለውዛም፥ የለውዝ ቦታ... / ኪወክ / አ]
ሎይድ ~
Lois:
‘ቅን፣ ተግባቢ’ ማለት ነው። የጢሞቴዎስ አያት፥ “በአንተ ያለውን ግብዝነት
የሌለበትን እምነትህን
... በአያትህ በሎይድ በእናትህም በኤውንቄ ነበረባቸው፥
በአንተም ደግሞ
እንዳለ ተረድቼአለሁ” (2 ጢሞ 1:5)
ሎድ ~
Lod:
ልድ፣ ልጅ፣ ውልድ፣ ትውልድ... ማለት ነው። ከግዞት ከተመለሱ፥ የሎድ ልጆች
ይገኙበታል፥ “የሎድና የሐዲድ
የኦኖም ልጆች፥
ሰባት መቶ
ሀያ አምስት።” (ዕዝ 2:33)
ሎዶቅያ ~ Laodicea: ‘ፍትሐዊ፣ እውነተኛ
ሕዝብ’
ማለት ነው።
“በሎዶቅያም ወዳለው ... አሜን የሆነው፥ የታመነውና እውነተኛው ምስክር፥ በእግዚአብሔርም ፍጥረት መጀመሪያ የነበረው እንዲህ ይላል።” (ራእይ 3:14)
ሎጥ ~
Lot:
‘ልጥ፣ ነጠላ፣ ሻሽ፣ የፊት መሸፈኛ’ ማለት ነው። የታራ ልጅ፣ የናኮር ልጅ፣ የሐራን ልጅ፥ “የታራም ትውልድ እነሆ ይህ ነው። ታራ አብራምንና ናኮርን ሐራንንም
ወለደ ሐራንም
ሎጥን ወለደ” (ዘፍ 11:27፣31)
No comments:
Post a Comment