ሀ ለ ሐ መ ሠ ረ ሰ ሸ ቀ በ ተ ቸ ኀ ነ ኘ አ ከ ኸ ወ ዐ ዘ ዠ የ ደ ጀ ገ ጠ ጨ ጰ ጸ ፀ ፈ ፐ
ዓብዳ ~ Abda: አገልጋይ፣ ተላላኪ፣ ታዛዥ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- አብዲ፣ አቤድ]
‘አብዴ’
ከሚለው ቃል
የመጣ ስም ነው።
. የአዶኒራም
አባት፥ (1 ነገ 4:6)
. የሳሙስ ልጅ፥ አብድያ- (ነህ 11:17)
ዐናሚም ~ Anamim: ‘ፏፏቴ’
ማለት ነው።
የግብጻውያን ወገን፥
የምጽራይም ልጅ፥ “ምጽራይምም ሉዲምን፥ ዐናሚምን፥ ላህቢምን፥ ነፍታሌምን፥ ፈትሩሲምን፥” (ዘፍ
10:13፤ 1
ዜና 1:11)
ዓዛርያስ ~
Azariah: ዘረ ሕያው፣ ዘረ ዋስ፣ የጌታ ወገን፣ የአምላክ ቤተሰብ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ዓዛሪያስ፣ ዔዛርያስ]
Azariah- ‘ዘር’
እና ‘ያሕ’ (ያሕዌ ፣ ሕያው) ከሚሉት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
ንጉሡ ሰሎሞን በእስራኤል ሁሉ ላይ በነገሠበት ዘመን አለቃ የነበረ፥ የሳዶቅ ልጅ ፥ ካህኑ ዓዛርያስ፥ (1 ነገ 4:2)
2.
የኬልቅያስ ልጅ፥ (ዕዝ7:1 ፣ 2)
፣ “የእግዚአብሔርም ቤት አለቃ …
ዓዛርያስ” (1 ዜና 9:11፣ ነህ 3:23)፣ (1 ዜና 6:36)
3.
የዖዴድ ልጅ፥
(2 ዜና 15:1)
4.
የአኪማአስ ልጅ፥ (1 ዜና 6:9
፣ 1 ነገ 4:2)
5.
የዮሐናን ልጅ፥
(1 ዜና 6:10
፣ 11)
6.
የአሜስያስ ልጅ፥ (2 ነገ 14:21 ፣ 2
ዜና 26:17-20)
ዐግ ~ Og: ‘ትልቅ’
ማለት ነው።
ግዛቱ በስድሳ
ከተሞች የተስፋፋ፥ የአሞራውያን
ንጉሥ፥ “ባሳንንም ሁሉ
እስከ ሰልካ
ድረስ፥ በባሳን
የነበረውን በአስታሮትና በኤድራይ የነገሠውን የዐግን መንግሥት ሁሉ እርሱም ከራፋይም የቀረ ነበረ
እነዚህንም ሙሴ
መታቸው አወጣቸውም።” (ኢያ 13:12)
ዑላ ~
Ulla:
‘ቀንበር’ ማለት ነው። የአሴር ልጅ፥ “የዑላ ልጆች ኤራ፥ ሐኒኤል፥
ሪጽያ ነበሩ።” (1 ዜና 7:39)
ዑማ ~ Ummah: ‘ውኅደት’
ማለት ነው።
ለአሴር ነገድ፥
ድርሻ የተሰጠ
ከተማ፥ “ዑማ፥ አፌቅ፥
ረአብ ደግሞ
ነበሩ ሀያ
ሁለት ከተሞችና
...” (ኢያ 19:30)
ዑሪ ~
Huri:
‘ሸማኔ፣ ዘዋሪ፣ ዝሐ ዘጊ፣ ተሽከርካሪ፣ ተመላላሽ’ ማለት ነው። የጋድ ወገን፥ የአቢካኢል ልጅ፥ “እነዚህም የቡዝ ልጅ የዬዳይ ልጅ ... የሚካኤል ልጅ የገለዓድ
ልጅ የኢዳይ
ልጅ የዑሪ ልጅ የአቢካኢል ልጆች
ነበሩ።”
(1 ዜና 5:14)
ዑር ~ Ur: ኡር፣
ብርሃን፣ የብርሃን
መውጫ፣ ምሥራቅ
አገር ማለት
ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ኡሪ፣ ኡር]
በዚህ ስም
የሚታወቁ አንድ
ሰው እና
አንድ አገር አሉ።
1.
የኤሊፋል አባት፥
(1 ዜና 11:36)
2.
ሐራን የተወለደበት አገር፥ (ዘፍ 11:28፣ 31)
ዑታይ ~ Uthai: ‘ተባባሪ፣ ረዳት’ ማለት ነው።
1.
የይሁዳ ወገን፥ የዓሚሁድ ልጅ፥ “ከይሁዳ ልጅ ከፋሬስ ልጆች የባኒ ልጅ የአምሪ ልጅ
የፆምሪ ልጅ
የዓሚሁድ ልጅ
ዑታይ ደግሞ
ተቀመጠ”
(1 ዜና 9:4)
2.
ከምርኮ ከተመለሱ፥
“ከበጉዋይ ልጆች ዑታይና
ዘቡድ፥ ከእነርሱም ጋር ሰባ ወንዶች።” (ዕዝ 8:14)
ዑኒ~
Unni: ‘ጭንቀታም’
ማለት ነው።
1.
ከዳዊት ዘበኞች አንዱ፥ “ከእነርሱም ጋር በሁለተኛው ተራ የሆኑትን ወንድሞቻቸውን ዘካርያስን፥
ቤንን፥ ያዝኤልን፥
ሰሚራሞትን፥ ይሒኤልን፥
ዑኒን፥ ኤልያብን፥ ... በረኞችንም ዖቤድኤዶምንና ይዒኤልን አቆሙ።” (1 ዜና 15:18፣20)
2. ከባቢሎን ምርኮ ከተመለሱ፥
“ወንድሞቻቸውም በቅቡቅያና ዑኒ በየሰሞናቸው በአንጻራቸው ነበሩ።” (ነህ 12:9)
ዑፅ ~
Huz:
‘አሸዋማ’ ማለት ነው። የናኮርና ሚልካ ትልቁ ልጅ፥ “እነርሱም በኵሩ ዑፅ፥ ወንድሙ ቡዝ፥ የአራም አባት ቀሙኤል፥” (ዘፍ 22:21)
ዑፅ ~ Uz: ‘እዝ፣ ትእዛዝ’ ማለት ነው።
1.
የአራም ልጅ፥ “የአራምም ልጆች ዑፅ፥ ሁል፥ ጌቴር፥ ሞሶሕ ናቸው።”
(ዘፍ 22:21)
2.
የዲሳን ልጅ፥ “የዲሳን ልጆችም እነዚህ ናቸው ዑፅ፥ አራን” (ዘፍ 36:28)
3.
የናኮር ልጅ፥ “እነርሱም በኵሩ ዑፅ፥ ወንድሙ ቡዝ፥ የአራም አባት ቀሙኤል፥”
(ዘፍ 22:21)
ዒስካ ~
Ikkesh:
‘የካሽ፣ የከፋይ፣ ፈቃደኛ፣ ጽኑዕ’
ማለት ነው። የቴቁሐዊው የዒራስ አባት፥
“የዒስካ ልጅ ዒራስ፥ ዓናቶታዊው” (2 ሳሙ 23:26፤ 1 ዜና 11:28፥ 27:9)
ዒሪ ~
Iri:
ብርሃን ማለት ነው።የቤላ ልጅ፥ “የቤላም ልጆች፥ ኤሴቦን፥ ኦዚ፥ ዑዝኤል፥ ኢያሪሙት፥ ዒሪ፥
አምስት ነበሩ
የአባቶቻቸው ቤቶች
አለቆች፥ ጽኑዓን
ኃያላን ሰዎች
ነበሩ በትውልድ
የተቈጠሩ ሀያ
ሁለት ሺህ
ሠላሳ አራት
ነበሩ።”
(1 ዜና 7:7፣12)
ዒራም ~ Iram: ‘ከተሜ’
ማለት ነው።
የኤዶማውያን መሪ፥
“መግዲኤል አለቃ፥ ዒራም አለቃ፥ እነዚህ በግዛታቸው
ምድር በየመኖሪያቸው
የኤዶም አለቆች
ናቸው። የኤዶማውያን አባት ይህ ዔሳው ነው።” (ዘፍ 36:43፤ 1
ዜና 1:54)
ዒር ~
Ir:
‘ከተማ’ ማለት ነው። “ደግሞም ሳፊን፥ ሑፊም የዒር ልጆች፥ ሑሺም
የአሔር ልጆችም
ነበሩ።”
(1 ዜና 7:12)
ዒርሼሜሽ ~ Irshemesh: ‘የፀሓይ ከተማ’ ማለት
ነው። የዳን
ነገድ ከተማ፥
“የርስታቸውም ዳርቻ ... ጾርዓ፥
ኤሽታኦል፥ ዒርሼሜሽ፥” (ኢያ
19:41)
ዒዋ ~ Ivah: ’ቅሪት፣ ባድማ፣ ውድቅዳቂ’ ማለት ነው። “የሐማትና የአርፋድ
አማልክት ወዴት
አሉ? የሴፈርዋይምና
የሄና የዒዋም አማልክት
ወዴት አሉ? “(2 ነገ 18:34፣ 19:13)
ዒዪም ~ Iim: ‘ባድማ፣ ውዳቂ፣
ፍርስራሽ፣ ቅሬት’ ማለት
ነው። በይሁዳ
የደቡብ ወሰን የሚገኝ ከተማ፥ “በኣላ፥ ዒዪም፥ ዓጼም፥ ኤልቶላድ፥” (ኢያ 15:29)
ዒዮን ~
Ijon: ‘ባድማ፣ ውዳቂ፣ ፍርስራሽ፣ ቅሬት’ ማለት ነው። የንፍታሌም ርስት
የሆነ ሰሜናዊ
የፍልስጥኤም ክፍል፥
“ወልደ አዴርም ... ከተሞች
ላይ ሰድዶ
ዒዮንንና ዳንን፥
አቤልቤት መዓካንና
ኪኔሬትን ሁሉ
የንፍታሌምንም አገር
ሁሉ መታ።” (1 ነገ
15:20፤ 2
ዜና 16:4)
ዒዶ ~ Iddo: ‘ውድ፣ ተወጃጅ’ ማለት ነው።
1.
የአሚናዳብ አባት፥ “በመሃናይም የዒዶ ልጅ አሒናዳብ” (1 ነገ 4:14)
2.
የጌድሶን ልጅ፥ አዶ፥ “ልጁ ዮአክ፥ ልጁ አዶ፥ ልጁ ዛራ...” (1 ዜና 6:21)
3.
በዳዊት ዘመን፥
በዮ ርዳኖስ
በስተምሥራቅ የምናሴ
ነገድ ገዥ፣ የዘካርያስ ልጅ፥ “በገለዓድ ባለው
በምናሴ ነገድ
እኵሌታ ላይ
የዘካርያስ ልጅ አዶ በብንያም ላይ
የአበኔር ልጅ
የዕሢኤል”
(1 ዜና 27:21)
4.
ባለ ራእዩ፥ ነቢዩ ኢዶ፥ “የቀረውም ፊተኛውና ኋለኛው የሰሎሞን ነገር በነቢዩ በናታን
ታሪክ፥ በሴሎናዊውም
በኦሒያ ትንቢት፥
ስለ ናባጥም
ልጅ ስለ
ኢዮርብዓም ባየው በባለ ራእዩ በአዶ ራእይ የተጻፈ አይደለምን?” (2 ዜና 9:29)
5.
የነቢዩ የዘካርያስ
አባት፣ የበራክዩ
አባት፥ “... የእግዚአብሔር
ቃል ወደ
አዶ ልጅ ወደ በራክዩ ልጅ ወደ ነቢዩ ወደ ዘካርያስ እንዲህ ሲል መጣ” (ዘካ 1:1፣7)
6.
ከባቢሎን ምርኮ ከተመለሱ፥ “በካሲፍያ ስፍራ ወደ ነበረው ወደ አለቃው ወደ አዶ ላክኋቸው ለአምላካችን ቤት አገልጋዮችን ያመጡልን ዘንድ...” (ዕዝ 8:17)
ዓሌሜት ~ Alameth: ዓለማት
ማለት ነው።
[ተዛማጅ ስም-
ጋሌማት]
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
የቤኬር ልጅ፥
(1 ዜና 7፡8)
2.
የይሆዓዳ ልጅ፥
(1 ዜና 8:32)
3.
የዕራ ልጅ፥
(1 ዜና 9:42)
ዓልዋን ~
Alian:
ዓላይነ፣ ዕላይ፣ ከፍተኛ፣ ትልቅ፣ የበላይ... ማለት ነው። የሦባል
ልጅ፥ “የሦባል ልጆች
ዓልዋን፥ ማኔሐት፥
ዔባል፥ ስፎ፥
አውናም። የጽብዖንም
ልጆች አያ፥
ዓና።”
(1 ዜና 1:40)
ዓልዋ ~ Alvah: ‘ላይኛ፣ የበላይ’ ማለት ነው።
ከኤዶማውያን አለቆች
አንዱ፥ “የዔሳውም የአለቆቹ ስም በወገናቸው በስፍራቸው በስማቸውም ይህ ነው ቲምናዕ አለቃ፥
ዓልዋ አለቃ፥
የቴት አለቃ፥” (ዘፍ 36:40)
ዓሚሁድ ~ Ammihud:
አሚ ሑድ፣ አም ውድ፣ የተወደደ፣ የተዋሐደ... ማለት ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
የአዳን ልጅ፥ የኤሊሳማ አባት፥ (1 ዜና 7:26) ፣ (ዘኁ 1:10)
2.
ከስምዖን ነገድ የሰላሚኤል አባት፥ (ዘኁ 34:20)
3.
ከንፍታሌ ነገድ፣
የፈዳሄል አባት፥
(ዘኁ 34:28)
4.
የጌሹር ንጉሥ የተልማይ አባት፥ (2 ሳሙ 13:37)
5.
የፆምሪ ልጅ፥
(1 ዜና 9:4)
ዓሚኤል ~
Ammiel:
አሚ ኤል፣ ሕዝበ እግዚአብሔር፣ የአምላክ ሕዝብ... ማለት ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
የከነዓንን ምድር እንዲሰልሉ ሙሴ ከላካቸው፥ የገማሊ ልጅ፥ (ዘኁ
13:12)
2.
የሳዖል ልጅ፣ የዮናታን ልጅ ከንጉሥ ዳዊት ሸሽቶ የሔደበት ሰው፥ የማኪር
አባት፥ (2 ሳሙ 17:27) ፣ (2 ሳሙ 9:4)
3.
የዳዊት ሚስት የቤርሳቤህ አባት፥ (1 ዜና 3:5)
4.የዖቤድኤዶም ልጅ፥
(1 ዜና 26:5)
ዓሚዛባድ ~ Ammizabad: ‘የሕዝብ ስጦታ፣
ጥሎሽ’
ማለት ነው።
በሠላሳው ኃያላን ላይ የሦስተኛው ክፍል አለቃ የነበረ፣ የበናያስ ልጅ፥ “ይህ በናያስ በሠላሳው መካከል ኃያል ሆኖ በሠላሳው ላይ ነበረ በእርሱም ክፍል ልጁ ዓሚዛባድ ነበረ።” (1 ዜና 27:6)
ዓማል ~ Amal: ‘ዐመል፣ ጠባይ፣ ሥራ፣ ሱስ’ ማለት ነው። የኤላም ልጅ፥ “የወንድሙም የኤላም ልጆች ጾፋ፥ ይምና፥ ሰሌስ፥ ዓማል ነበሩ።” (1 ዜና7:35)
ዓማሣይ ~
Amasai:
ዐማፂ፣ ያመጸ፣ የሸፈተ፣ አልታዘዝም ያለ፣ ትዕቢተኛ፣ ትምክሕትኛ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- አማሢ ፣ አማሳይ፣ ዓማስያ፣ አሜሳይ፣ ዓሜሳይ]
‘ዐመፀ’
ከሚለው ግስ
የተገኘ ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
ከዳዊት ጋር ከተቀላቀለ ሠራዊት የሠላሳ አለቃ የነበረ፥ (1 ዜና 12:18)
2.
በእግዚአብሔር ታቦት ፊት መለከት ይነፉ ከነበሩ ካህናት፥ (1
ዜና 15:24)
. የሕልቃና ልጅ፥
አማሢ-
(1 ዜና 6፡25፣35)
. የእግዚአብሔርን ቤት ያነጹ ዘንድ ወደ ውስጥ ከገቡ ካህናት፣ የቀዓት ልጅ፥ አማሢ- (2
ዜና 29:12)
ዓማስያ ~ Amasiah: አማሲ ያሕ፣ ዐማፂ ሕያው፣ ኃጢአተኛ፣ ጌታን የሚበድል፣ የአምላክን ሕግ የጣሰ፣ አሻፈረኝ ያለ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ዓማሣይ፣ አማሢ ፣ አማሳይ፣ አሜሳይ፣ ዓሜሳይ]
‘ዐማፂ’ እና ‘ያሕ’
(ያሕዌ)
ከሚሉት ቃላት
የተመሠረተ ስም
ነው። በፈቃዱ ራሱን ለእግዚአብሔር የቀደሰ፣ የዝክሪ ልጅ፥ (2 ዜና 17፡16)
ዓሜሳይ ~ Amasa: አመሳ፣ ዐመፃ፣ የሚያምስ፣ የሚበጠብጥ፣ የሚረብሽ፣ ተቃዋሚ፣ የማይታዘዝ፣ የማይገዛ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ዓማሣይ፣ አማሢ ፣ አማሳይ፣ ዓማስያ፣ አሜሳይ]
‘ዐመፀ’
ከሚለው ግስ
የመጣ ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
የዳዊት እኅት የአቢግያ ልጅ፣ የዬቴር ልጅ፥ (1 ዜና 2፡17)
2.
ከኤፍሬም ልጆች አለቆች፣ የሐድላይ ልጅ፥ (2
ዜና 28:12)
ዓምዓድ ~
Amad:
አማድ፣ አዕማድ፣ ዐምድ፣ መሠረት፣ ምሰሶ... ማለት ነው።
‘አምደ’ ከሚለው ግስ የመጣ የቦታ ስም ነው። የአሴር ልጆች ነገድ ድንበር፥ (ኢያ 19:26)
ዓሞቅ ~
Amok:
አሞቅ፣ አመቅ፣ መቅ፣ መቀመቅ፣ ጥልቅ ጉድጓድ፣ መቃብር... ማለት ነው።
‘አመቀ’ ከሚለው ቃል የተገኘ
ስም ነው።
ከሰላትያል ልጅ ከዘሩባቤልና ከኢያሱ ጋር ከወጡ ካህናትና ሌዋውያን፥ (ነህ 12:7
፣ 20)
ዓሢኤል ~
Asiel:
አሥ ኤል፣ የጌታ ሥራ፣ ግብረ ኤል፣ እሥራ ኤል፣ የአምላክ ሥራ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ዓሣያ፣ ዓሳያ]
የሠራያ ልጅ፥
(1 ዜና 4፡35)
ዓሣያ ~
Asaiah:
ዓሣ ያሕ፣ አሳይ ያሕ፣ የሕያው ሥራ፣ ጌታ ሠራ፣ አምላክ አከናወነ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ዓሳያ፣ ዓሢኤል]
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
የሠራያ ልጅ የዓሢኤል ልጅ፥ ዓሣያ፥ (1 ዜና 4፡36)
2.
ዳዊት ታቦቱ ዐርፎ ከተቀመጠ በኋላ በእግዚአብሔር ቤት ካቆማቸው የመዘምራን አለቆች፥ የሐግያ ልጅ፥ ዓሣያ፥ (1 ዜና 6፡30)፣ (1
ዜና 15፡6)
3.
የሴሎናዊያን ልጅ፥ ዓሣያ፥ “ከሴሎናዊያንም በኵሩ ዓሣያና ልጆቹ” (1ዜና 9፡5)
4.
“ንጉሡም ካህኑን
ኬልቅያስን፥ ... የንጉሡንም ብላቴና ዓሳያን።”
(2 ዜና 34:20)
ዓረባ ~
Arabah:
ዓረባ፣ ዓረባዊ፣ የዓረብ አገር፣ ምድረ ባዕዳ፣ በረሐ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ዓረባዊ፣ ዓረብ]
‘ረባ’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው።
. “በዮርዳኖስ
ማዶ በምድረ
በዳ፥ በዓረባ ውስጥ በኤርትራ ባሕር ፊት ለፊት ...
ሙሴ ለእስራኤል ሁሉ የነገራቸው ቃል ይህ ነው።” (ዘዳ 1:1)
. “በሰሜንም ወገን ወደ ዓረባ አጠገብ አለፈ፥ ወደ ዓረባም ወረደ…”
(ኢያ 18፡18)
ዓረባዊ ~
Arbathite:
ዓረባያት፣ ዓረባዊያት፣ የዓረብ አገር ሰዎች... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ዓረባ፣ ዓረብ]
ከዳዊት ወታደሮች አንዱ፣ አቢዓልቦን፥ (2 ሳሙ 23:31፣ 1 ዜና 11:32) ፣ (ኢያ 15:61)
ዓረብ ~ Arabia: ዓረባዊ፣ ዓረባውያን፣ የዓረብ አገር... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ዓረባ፣ ዓረባዊ]
ከምድሩ ሹማምንት ወደ ሰሎሞን ወርቅና ብር ግብር ካመጡ፥ (1 ነገ 10፡15)
ዓራድ ~
Arad:
‘የሜዳ አህያ’ ማለት ነው። “ዝባድያ፥ ዓራድ፥ ዔድር፥ ሚካኤል፥ ይሽጳ፥ ዮሐ፥ የበሪዓ ልጆች” (1 ዜና 8:15)
ዓሻን ~
Ashan:
‘ጭስ’ ማለት ነው። በይሁዳ የታችኛው ክፍል የነበረ ከተማ፥ “ልብና፥ ዔቴር፥ ዓሻን፥ ይፍታሕ፥ አሽና፥” (ኢያ 15:42)
ዓቁብ ~
Akkub:
ዐቁብ፣ ዕቁብ፣ ዐቃቢ ፥ ዐቀበ፣ ጠበቀ፣ ከለከለ፣ አገደ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ያቆብ፣ ያዕቆባ፣ ያዕቆብ]
‘ዐቀበ’
ከሚለው ግስ
የተገኘ ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
ከዘሩባቤል ወገን፣ የኤልዮዔናይ ልጅ፥ (1
ዜና 3:24)
2.
ከነቢዩ ዕዝራ ጋር ከባቢሎን ከተመለሱ፣ የአጋባ ልጅ፥ (ዕዝ 2:45፣ 46)
3.
ከምርኮ ተመልሰው በረኛ ከነበሩ፥ (1
ዜና 9:17) ፣ (ዕዝ 2:42፣ ነህ
7:45)
ዓቃን ~
Jakan:
‘ጠቢብ፣ አስተዋይ፣ አርቆ አሳቢ፣ ቅን ፈራጅ’ ማለት ነው። የኤጽር ልጅ፥ “የኤጽር ልጆች ቢልሐን፥ ዛዕዋን፥ ዓቃን፦ የዲሳን ልጆች ...” (1 ዜና 1:42)
ዓባሪም ~ Abarim: አባሪ፣
ተባባሪ፣ ረዳት፣
አጋዥ... ማለት ነው።
በሞዓብ ምድር፥
በዮርዳኖስ በስተምሥራቅ፥
በእያሪኮ አቅጣጫ፥
የዮርዳኖስ ሸለቆ
አዋሳኝ፥ የሆነ
ተራራማ ቦታ።
ከተራራዎቹ ጎልቶ
የሚታየው ኔቦ
በመባል የሚታወቀው ሲሆን፥
ሙሴ ሊሞት
ሲል ወደዚያ
ተራራ በመውጣት
ከዚያ የተስፋውን
አገር በዓይኑ ለመቃኘት በቅቷል። “እግዚአብሔርም ሙሴን አለው፦ ወደዚህ ወደ ዓባሪም ተራራ ውጣ፥ ለእስራኤልም ልጆች የሰጠኋትን ምድር እይ” (ዘኊ 27:12፤
33:47፣48) እና (ዘዳ 32:49)
ዓብዳ ~Abda: አገልጋይ፣ ተላላኪ፣ ታዛዥ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- አብዲ፣ አቤድ]
‘አብዴ’
ከሚለው ቃል
የመጣ ስም ነው።
. አስገባሪ የነበረ፣ የአዶኒራም አባት፥
(1 ነገ 4:6)
. የሳሙስ ልጅ፥ አብድያ-
(ነህ 11:17)
ዓብድኤል ~
Abdeel:
አብድ ኤል፣ የአምላክ አገልጋይ... ማለት ነው።
[ተዛማጅ ስሞች- አብዲኤል፣ አብድያ፣ አብድያስ]
‘አብድ’ እና ‘ኤል’
ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
የሰሌምያ አባት፥ “ንጉሡም ጸሐፊውን ባሮክንና ነቢዩን ኤርምያስን ይይዙ ዘንድ የንጉሡን
ልጅ ይረሕምኤልንና
የዓዝርኤልን ልጅ
ሠራያን የዓብድኤልንም ልጅ ሰሌምያን አዘዘ፥ እግዚአብሔር ግን ሰወራቸው” (ኤር 36:26)
ዓብዶን ~
Abaddon, Abdon: አብ ዶን፣ አባት ዳኛ፣
የመጨረሻ ፍርድ
አስፈጻሚ... ማለት ነው።
‘አብደ’ እና ‘ዳኘ’ ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ዓብዶን / Abaddon:
. የገሃነም መልአክ ስም፥ “በእነርሱም ላይ ንጉሥ አላቸው፤ እርሱም የጥልቅ መልአክ ነው፥ ስሙም በዕብራይስጥ አብዶን በግሪክም አጶልዮን ይባላል”
(ራእ 9፡11)
. በኢዮብ መጽሐፍ ጥፋት ይላል፥ “ጥፋትና ሞት- (ኢዮ 26:6)
. የመጨረሻ ፍርድ፥ “ሲኦልና ጥፋት- (ምሳ 15:11) ፣ “ሲኦልና ጥፋት- (ምሳ 27:20)
ዓብዶን / Abdon:
1.
በእስራኤል ላይ ፈራጅ የነበረ፣ የሂሌል ልጅ፥ (መሣ 12፡13)
2.
የይዒኤል ልጅ፥ “ዔቤር፥ ኤሊኤል፥ ዓብዶን፥ ዝክሪ፥” (1 ዜና 8:23)
3.
“የበኵር ልጁ ዓብዶን፥ የበኵር ልጁም ዓብዶን፥” (1 ዜና 8:30)፣ (9:35
፣ 36)
4.
የሚክያስ ልጅ፥
(2 ዜና 34:20)
5.
የቦታ ስም፥ “...ዓብዶንንና መሰምርያዋን፥” (ኢያ 21:30) ፣ (1 ዜና 6:74)
ዓታክ ~
Athach:
‘የመንገደኛ ማረፊያ’ ማለት ነው። በይሁዳ አገር የታችኛው አካባቢ
የነበረ የቦታ
ስም፥ “በሔርማ ለነበሩ፥
በቦራሣን ለነበሩ፥
በዓታክ ለነበሩ፥
በኬብሮን ለነበሩ፥” (1 ሳሙ 30:30)
ዓታይ ~ Attai:
‘እጣ የደረሰው፣ ጊዜ የሰጠው፣ ዕደለኛ’ ማለት ነው።
1.
የሶሳን የልጅ ልጅ፥ “ሶሳንም ለአገልጋዩ ለኢዮሄል ልጁን አጋባት፥ እርስዋም
ዓታይን ወለደችለት።” (1 ዜና 2:35፣36)
2.
ያንበሳ ገጽ ካላቸው የጋድ ጦረኞች አንዱ፥ የዳዊት የጦር አዛዥ፥ (1 ዜና
12:11)
3.
የሰሎሞን ልጅ ሮብዓም፥ ከመዓካ የወለደው፥ “ከእርስዋም በኋላ የአቤሴሎምን ልጅ መዓካን አገባ እርስዋም አብያን፥ ዓታይን፥ ዚዛን፥ ሰሎሚትን ወለደችለት።” (2 ዜና 11:20)
ዓኑብ ~
Anub:
‘መተባበር፣ መረዳዳት፣ ኅብረት መፍጠር’ ማለት ነው። የይሁዳ ወገን
የሆነ፥ የቆጽ
ልጅ፥ “ቆጽ ዓኑብን፥
ጾቤባን፥ የሃሩምንም
ልጅ የአሐርሔልን
ወገኖች ወለደ።” (1 ዜና 4:8)
ዓኒም ~
Anim:
‘ፏፏቴ’ ማለት ነው። በይሁዳ ተራራዎች የነበረ ከተማ፥ “ዓናብ፥ ኤሽትሞዓ፥
ዓኒም፥ ጎሶም፥
ሖሎን፥ ጊሎ
አሥራ አንድ
ከተሞችና መንደሮቻቸው።” (ኢያ 15:50)
ዓና~ Anah: ‘ታዛዥ’ ማለት ነው። የዔሳው ሚስት
አባት፥ የኤዊያዊው
የፅብዖን ልጅ፥
“ዔሳው ከከነዓን ልጆች ሚስቶችን አገባ የኬጢያዊውን የዔሎንን ልጅ ዓዳን፥ የኤዊያዊው የፅብዖን ልጅ ዓና የወለዳትን አህሊባማን፥” (ዘፍ 36:2፣14፣25)
ዓናብ ~
Anab: ‘የዘቢብ
ከተማ’
ማለትነው። ከይሁዳ
ተራራማ ከተሞች
አንዱ፥ “ዓናብ፥ ኤሽትሞዓ፥ ዓኒም፥ ጎሶም፥ ሖሎን፥ ጊሎ አሥራ አንድ ከተሞችና መንደሮቻቸው።” (ኢያ 15:50)
ዓናቶት ~
Anathoth:
‘ሥምረት፣ ስእለቱ የደረሰ፣ ልመናው የተሰማ’ ማለት ነው።
1.
የቤኬርም ልጅ፥” የቤኬርም ልጆች ዝሚራ፥ ኢዮአስ፥ አልዓዛር፥ ኤልዮዔናይ፥ ዖምሪ፥ ኢያሪሙት፥ አብያ፥ ዓናቶት፥ ዓሌሜት እነዚህ ሁሉ የቤኬር ልጆች
ነበሩ።”
(1 ዜና 7:8)
2.
በነህምያ ዘመን
ቃል ኪዳን ከተፈራረሙትአንዱ፥ “ሐሪፍ፥ ዓናቶት፥ ኖባይ፥
መግጲዓስ፥ ሜሱላም” (ነህ 10:19)
ዓናኒ ~
Anani:
‘አምላክ የጠበቀው’ ማለት ነው። ከይሁዳ ነገሥታት ወገን፥ የኤልዮዔናይ
ልጅ፥ “የኤልዮዔናይም ልጆች
ሆዳይዋ፥ ኤልያሴብ፥
ፌልያ፥ ዓቁብ፥
ዮሐናን፥ ደላያ፥ ዓናኒ ሰባት ነበሩ።” (1 ዜና 3:24)
ዓኔም ~ Anem: ‘መንታ ምንጭ’ ማለት ነው። የይሳኮር ከተማ፥ “ራሞትና መሰምርያዋ፥ ዓኔምና መሰምርያዋ” (1 ዜና 6:73)
ዓኔር ~ Aner: ‘ጎልማሳ’ ማለት ነው። ለቀዓት ልጆች ወገን የተሰጠ የምናሴ ከተማ፥ “ከምናሴም ነገድ እኵሌታ ዓኔርንና መሰምርያዋን፥ ...
ከቀዓት ልጆች ወገን ለቀሩት ሰጡ።” (1 ዜና 6:70)
ዓንቶትያ ~ Antothijah:
‘የሕያው መልስ’
ማለት ነው።
የይሮሐም ልጅ፥ “ሐናን፥ ሐናንያ፥
ኤላም፥ ዓንቶትያ፥
ይፍዴያ፥ ... የሶሴቅ
ልጆች”
(1 ዜና 8:24)
ዓክሳ ~ Achsah: ካሳ፣
ጥሎሽ፣ ስጦታ... ማለት
ነው። (አምባር ማለት
ነው፥ ተብሎም
ይተረጎማል) የካሌብ ሴት
ልጅ ዓክሳ፥
(1 ዜና 2:49)
“ደግሞም የመድማናን
አባት ሸዓፍንና
የመክቢናንና የጊብዓን
አባት ሱሳን
ወለደች የካሌብም
ሴት ልጅ
ዓክሳ ነበረች።”
ካሌብ፥ ቂርያትሤፍርን
ለሚመታ ለሚይዛትም
ልጄን ዓክሳን
አጋባዋለሁ በማለቱ
ለቄኔዝ ልጅ
ለጎቶንያል አጋባው።
(ኢያ 15:16-19፤ መሣ 1:9-15)
ዓክቦር~ Achbor: የከበደ፣ የጠጠረ፣ የጠነከረ... መከራ ማለት ነው።
1.
የኤዶም ንጉሥ የኣልሐናን አባት፥ “ሳኦልም ሞተ፥ በስፍራውም የዓክቦር ልጅ በኣልሐናን
ነገሠ።”
(ዘፍ 36:38፣39፥ 1 ዜና 1:49)
2.
በኢዮስያ ንግሥ ዘመን የነበረ፥ የሚክያስ ልጅ፥ “ንጉሡም ካህኑን ኬልቅያስን፥ የሳፋንንም ልጅ አኪቃምን፥ የሚክያስንም ልጅ ዓክቦርን፥ ጸሐፊውንም ሳፋንን፥ የንጉሡንም ብላቴና ዓሳያን።” (2 ነገ 22:12፣14፥ ኤር 26:22፥ 36:12)፤ “ዓብዶን”
ተብሎም ተጠርቷል፥
(2 ዜና34:20)
ዓዊት ~
Avith:
‘አውድማ፣ ፍርስራሽ፣ ቅሪት’ ማለት ነው። የባዳድ ልጅ ሃዳድ
የነገሠበት ከተማ
ስም፥ “ሑሳምም ሞተ፥
በስፍራውም ... ሃዳድ
ነገሠ የከተማውም ስም ዓዊት ተባለ።” (ዘፍ 36:35፣1
ዜና 1:46)
ዓዙር ~
Azur, Azzur: አዘር፣ ዘር፣ ወገን፣ ዘመድ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ዕዝራ]
‘ዘር’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ዓዙር / Azur:
1.
ነቢዩ የገባዖን ሰው፣ የሐናንያ አባት፥ (ኤር 28፡1)
2.
የያእዛንያን አባት፥
(ሕዝ 11:1)
ዓዙር / Azzur: ከነቢዩ ነህምያ ጋር የቃል ኪዳኑን ደብዳቤ ያተመ፥ (ነህ 10:17
፣ 18)
ዓዙባ ~ Azubah: ‘አዛባ፣ የተጣለ፣ የተረሳ’ ማለት ነው።
1.
የኤስሮም ልጅ የካሌብ ሚስት፥ “የኤስሮምም ልጅ ካሌብ ከሚስቱ ከዓዙባ ከይሪዖትም ልጆች ወለደ ...” (1 ዜና 2:18፣19)
2.
የንጉሥ ኢዮሣፍጥ እናት፥ “ኢዮሣፍጥ መንገሥ በጀመረ ጊዜ ... እናቱም ዓዙባ የተባለች የሺልሒ ልጅ ነበረች።” (1 ነገ 22:42፤ 2 ዜና 20:31)
ዓዛሪያስ ~
Azariah:
ዘረ ዋስ፣ ዘረ ያሕ፣ ዘረ ሕያው፣ የጌታ ወገን፣ የአምላክ ቤተሰብ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
አዛርያ፣ ዓዛርያስ፣ ዔዛርያስ]
Azariah- ‘ዘር’
እና ‘ያሕ’ (ያሕዌ ፣ ሕያው) ከሚሉት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
ከሳዶቅ ወገን የሆነ ዋነኛ ካህን፥ (2 ዜና 31:10-13)
ዓዛርኤል ~
Azareel:
ዘረ ኤል፣ ዘረ አምላክ፣ ዘረ ሕያው፣ የእግዚብሔር ቤተሰብ፣ የአምላክ ዘር... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ኤዝርኤል፣ ዓዝሪኤል፣ ዓዝርኤል፣ ኤዝርኤል፣ አዛርኤል]
‘ዘረ’
እና ‘ኤል’
ከሚሉ ሁለት
ቃላት የተመሠረተ
ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
የኤማን ልጅ፥
(1 ዜና 25:4)
2.
የይሮሐም ልጅ፥
(1 ዜና 27:22)
3.
በጺቅላግም ከቂስ ልጅ ከሳኦል በተሸሸገ ጊዜ ወደ ዳዊት ከመጡ፥ አዛርኤል፥
(1 ዜና 12)
. ኤዝርኤል፥ (ዕዝ 10:41)
. የአሕዛይ
ልጅ፥ ኤዝርኤል፥ (ነህ 11:13)
ዓዛርያስ ~
Azariah:
ዘረ ዋስ፣ ዘረ ያሕ፣ ዘረ ሕያው፣ የጌታ ወገን፣ የአምላክ ቤተሰብ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ዓዛሪያስ፣ ዔዛርያስ፣ ኤዝርኤል፣ አዛርኤል፣ ዓዛርኤል]
‘ዘር’ እና ‘ዋስ፣ ያሕ’ (ያሕዌ ፣ ሕያው) ከሚሉት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
የአኪማአስ ልጅ፥
“አኪማአስም ዓዛርያስን ወለደ”
(1 ዜና 6:9)፣ (1
ነገ 4:2)
2.
የንጉሥ ሰሎሞን የሹሞች አለቃ የነበረ፣ የናታን ልጅ፥ (1 ነገ 4:5)
3.
የይሁዳ ንጉሥ፣ የአሜስያስ ልጅ፥ (2 ነገ 14:21፥ 15:1፣6፣8፣17፣
23፣27፥ 1 ዜና8:12)
4.
የኢዩ ልጅ፥ “ኢዩም ዓዛርያስን ወለደ” (1 ዜና 2:38፣39)
5.
የዮሐናን ልጅ፥
(1 ዜና 6:10)
6.
የኬልቅያስ ልጅ፥
(1 ዜና 6:13፣14)
7.
የሶፎንያስ ልጅ፥
(1 ዜና 6:36)
8.
የዖዴድ ልጅ፥
(2 ዜና 15:1)
9.
የይሁዳ ንጉሥ የኢዮሣፍጥ ልጅ፥ (2
ዜና 21:2)
10.
ሌላ የይሁዳ ንጉሥ የኢዮሣፍጥ ልጅ፥ (2 ዜና 21:2)
11.
የይሮሐም ልጅ፥
(2 ዜና 23:1)
12.
ካህኑ ዓዛርያስ ፥ (2
ዜና 26:17-20)
13.
የዮሐናን ልጅ፥
(2 ዜና 28:12)
14.ኢዮኤል አባት፥
(2 ዜና 29:12)
15.
የይሃሌልኤል ልጅ፥
(2 ዜና 29:12)
16.
በንጉሡም በሕዝቅያስ ዘመን የነበረ ካህን፥ (2 ዜና 31:10፣13)
17.
በነህምያ ዘመን
የኢየሩሳሌምን ቅጥር
ከጠገኑ፣ የመዕሤያ
ልጅ፥ (ነህ
3:23፣24)
18.
ከዘሩባቤል ጋር ከምርኮ ከተመለሱ፥ (ነህ 7:7)
19.
ከነቢዩ ዕዝራ ጋር የሕጉን መጽሐፍ ካስተማሩ፥ (ነህ 8:7)
20.
ከነቢዩ ነህምያ ጋር የቃልኪዳኑን ደብዳቤ ካተሙት፥ (ነህ 10:2)
“ዓዛርያስ፥ ዕዝራ” (ነህ 12:33)
21.
የሆሻያ ልጅ፥
(ኤር 43:2)
22.
ከነቢዩ ዳንኤል ጋር ወደ ምርኮ ከተወሰዱ ሦስት ልጆች፥ የአብዲኔጎ ስም፥
(ዳን 1:6፣7፣11፣19)
ከይሁዳ ወገን፣ የኤታን ልጅ፥ “የኤታንም ልጅ አዛርያ ነበረ።” (1
ዜና 2:8)
ዓዜቃ ~
Azekah:
‘መከታ፣ ብርቱ ግንብ’ ማለት ነው። በይሁዳ የታችኛ ኮረብቶች የሚገኝ
ከተማ፥ “ዓዶላም፥ ሰኰት፥
ዓዜቃ፥ ሽዓራይም፥
ዓዲታይም፥ ግዴራ፥
ግዴሮታይም አሥራ
አራት ከተሞችና
መንደሮቻቸው።”
(ኢያ 15:36)
ዓዝሞት ~
Azmaveth:
አዘ ሞት፣ እንደሞት የበረታ... ማለት ነው።
1.
ከዳዊት ሠላሳ ኃያላን አንዱ፥ “ዓዝሞት፥ ሸዓልቦናዊው ኤሊያሕባ” (2 ሳሙ 23:32)
2.
በንጉሥ ዳዊትና ሰሎሞን ዘመን የነበረ፥ የመዝገብ ቤት ሐላፊ፥ “በንጉሡም ቤተ መዛግብት ላይ የዓዲኤል ልጅ ዓዝሞት ሹም ነበረ ...” (1 ዜና 27:25)
3.
በኢየሩሳሌም አቅራቢያ የነበረ፥ የይሁዳ ነገድ ከተማ፥ “...የመዘምራኑ ልጆች ከኢየሩሳሌም ዙሪያና
ከነጦፋውያን መንደሮች፥
ከቤትጌልገላም፥ ከጌባና
ከዓዝሞት እርሻዎች ተሰበሰቡ።” (ነህ 12:29፤ ዕዝ 2:24)
4.
የዓሌሜት ልጅ፥ “አካዝም ይሆዓዳን ወለደ ይሆዓዳም ዓሌሜትን፥ ዓዝሞትን፥ ዘምሪን ወለደ ዘምሪም ሞጻን ወለደ።” (1 ዜና 8:36)
ዓዝሪቃም ~
Azrikam:
አዛረ ቆመ፣ ዘረ ቋሚ፣ ቋሚ ዘር፣ ለወገን ደራሽ፣ ረዳት... ማለት ነው።
‘ዘረ’ እና ‘ቆመ’
ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
ከይሁዳ ነገድ የዘረባቢሎን ወገን፣ የነዓርያ ልጅ፥ (1 ዜና 3፡23)
2.
ከሳኦል ወገን፣ የኤሴል ልጅ፥ (1 ዜና 8:38 ፣ 9:44)
3.
በነህምያ ዘመን የኖረ፣ ከሜራሪ ልጆች፣ የአሳብያ (1 ዜና 9:14)፣ (ነህ11:15)
4.
በንጉሥ አካዝ ዘመን፣ ዝክሪ የገደለው፥ (2 ዜና 28:7)
ዓዝሪኤል ~ Azriel: አዛረ ኤል፣ ዘረ ኤል፣ ዘረ አምላክ፣ የጌታ ወገን፣ የእግዚአብሔር ቤተ ሰብ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ዓዛርኤል፣ ኤዝርኤል፣ ዓዝርኤል፣ ዓዛርኤል፣ ኤዝርኤል፣ አዛርኤል፣ ዓዛርኤል]
‘ዘረ’
እና ‘ኤል’
ከሚሉ ሁለት
ቃላት የተመሠረተ
ስም ነው።
በንፍታሌም ላይ አለቃ የነበር፣ የኢያሪሙት አባት፥ (1 ዜና 27:19)
ዓዝርኤል ~ Azriel: አዛረ ኤል፣ ዘረ ኤል፣ ዘረ አምላክ፣ የጌታ ወገን፣ የእግዚአብሔር ቤተ ሰብ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ዓዛርኤል፣ ኤዝርኤል፣ ዓዝሪኤል፣ ዓዛርኤል፣ ኤዝርኤል፣ አዛርኤል፣ ዓዛርኤል]
‘ዘረ’ እና ‘ኤል’
ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
ከጽኑዓን ኃያላን የታወቁ ሰዎች የአባቶቻቸው ቤቶች አለቆች፥ የምናሴ ነገድ እኩሌታ
አለቃ፥ (1 ዜና 5፡24)
2.
የይሁዳ ንጉሥ የኢዮስያስ ልጅ ኢዮአቄም ያዘዘው፥ የሠራያ ልጅ፥ (ኤር 6:26)
ዓዝጋድ ~ Azgad: እዘ
ገድ፣ በገድ
የታዘዘ... ማለት ነው።
ከባቢሎን ምርኮ
ከተመለሱ የዓዝጋድ ልጆች ይገኙበታል፥ “የዓዝጋድ ልጆች፥ ሁለት ሺህ ሦስት መቶ ሀያ
ሁለት።”
(ነህ 7:17)
ዓይናም ~
Enam:
አይናም፣ የሚታይ፣ ገላጣ ስፍራ... ማለት ነው። በረባዳው የይሁዳ ክልል ያለ የይሁዳ ከተማ፥ “ዓይንገኒም፥ ታጱዋ፥ ዓይናም፥ የርሙት” (ኢያ
15:35)
ዓይን ~ Ain: ‘የውኃ ምንጭ’
ማለት ነው።
1.
የፍልስጥኤም ምሥራቃዊ ዳርቻ የሆነ ጉልህ ሥፍራ፥ “ዳርቻውም ከሴፋማ በዓይን ምሥራቅ ወዳለው ወደ ሪብላ ይወርዳል ...” (ዘኊ 34:11)
2.
የይሁዳ የመጨረሻ ደቡባዊ ከተማ፥ “ልባዎት፥ ሺልሂም፥ ዓይን፥ ሪሞን ሀያዘጠኝ ከተሞችና
መንደሮቻቸው”
(ኢያ 15:32)
ዓይንሀቆሬ ~
En-hakkore:
‘ዓይን አቆረ፥ የሚታይ የተጠራቀመ ውኃ፥ የጸሎት ምንጭ፣ ጠበል’ ማለት ነው። ሶምሶን ከፍልስጥኤማውያን ጋር ባደረገው ፍልሚያ፥ በተጠማና ጉልበቱ በዛለ ጊዜ፥ የጸለየበት ቦታ፥ “እግዚአብሔርም ... የዚያን ቦታ ስም ዓይንሀቆሬ ብሎ ጠራው ይህም እስከ ዛሬ ድረስ በሌሒ አለ።” (መሣ 15:19)
ዓይንሮጌል ~ En-rogel: “ዮናታንና አኪማአስ የተሸሸጉበት ቦታ፥ “ዮናታንና አኪማአስ ተገልጠው ወደ ከተማ ይገቡ ዘንድ አልቻሉም ነበርና በዓይንሮጌል ተቀምጠው ነበር፤ ...” (2 ሳሙ 17:17)
ዓይንኤግላይም ~ En-eglaim: ‘የሁለት እምቦሶች ‘ፏፏቴ’ ማለት ነው። በነቢዩ ሕዝቅኤል የተጠቀሰ የቦታ ስም፥ “አጥማጆችም በዚያ ይቆማሉ ከዓይንጋዲ ጀምሮ እስከ ዓይንኤግላይም ድረስ መረብ መዘርጊያ ...”
(ሕዝ 47:10)
ዓይንገኒም ~ En-gannim: ‘የገነት ፏፏቴ’
ማለት ነው።
1.
በይሁዳ መስክ የነበረ ከተማ፥ “ዓይንገኒም፥ ታጱዋ፥ ዓይናም፥ የርሙት” (ኢያ 15:34)
2.
የዛብሎን ልጆች ርስት፥ የሆነ ከተማ፥ “ወደ ሬሜት፥ ወደ ዓይንጋኒም፥ ወደ ዓይንሐዳ፥ ወደ ቤትጳጼጽ ደረሰ” (ኢያ 19:21)
ዓዲና ~
Adina:
አዱኛ ማለት ነው።
‘አዱኛ’
ከሚለው ቃል
የመጣ ስም ነው።
በዮርዳኖስ ማዶ የዳዊት ወታደሮች የሮቤላውያ አለቃ የነበረ፣ የሺዛ ልጅ፥ (1
ዜና 11፡42)
ዓዲን ~
Adin:
አዲነ፣ አደን፣ ደን፣ ደኔ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ዓዲና፣ ዓዳን፣ አዳን]
የባቢሎንም ንጉሥ
ናቡከደነፆር ወደ
ባቢሎን ከማረካቸው
ምርኮኞች ወደ ኢየሩሳሌምና ወደ ይሁዳ ወደ እየከተማቸው ከተመለሱ የአገር ልጆች፥ (ዕዝ 2፡1) ፣
(ነህ 10፡16)
ዓዲኤል ~ Adiel: ‘አምላክ ያሳመረው፣ የአምላክ ጌጥ’
ማለት ነው።
1.
የዓዝሞት አባት፥
በንጉሥ ሰለሞን
እና ዳዊት
ዘመን የመዝገብ ቤት ሐላፊ
የነበረ፥ “በንጉሡም ቤተ
መዛግብት ላይ
የዓዲኤል ልጅ
ዓዝሞት ሹም
ነበረ። በሜዳውም ... ቤተ መዛግብት ላይ የዖዝያ ልጅ ዮናታን ሹም ነበረ” (1 ዜና 27:25)
2.
“ኤልዮዔናይ፥ ያዕቆባ፥ የሾሐያ፥ ዓሣያ፥ ዓዲዔል፥ ዩሲምኤል፥ በናያስ፥”
(1 ዜና 4:36)
3.
የየሕዜራ ልጅ፥ ካህኑ፥ “የመልኪያ ልጅ የጳስኮር ... ልጅ የምሺላሚት ልጅ የሜሱላም ልጅ የየሕዜራ ልጅ የዓዲኤል ልጅ መዕሣይ” (1 ዜና 9:12)
ዓዳ ~ Adah: ‘ጌጥ፣ ውበት’ ማለት ነው።
1.
ከላሜሕ ሁለት
ሚስቶች፥ ሁለት
ልጆችን የወለደችለት፥
የአንደኛዋ ስም፥ “ላሜሕም ለራሱ ሁለት ሚስቶችን አገባ የአንዲቱ ስም ዓዳ፥ ...” (ዘፍ 4:19)
2.
ከዔሳው ሦስቱ
ሚስቶቹ አንዷ፥
የኤልፋዝ እናት፥
“ዔሳው ከከነዓን ልጆች
ሚስቶችን አገባ የኬጢያዊውን የዔሎንን ልጅ ዓዳን፥ የኤዊያዊው የፅብዖን ልጅ ዓና የወለዳትን
አህሊባማን፥”
(ዘፍ 36:2፣10፣12፣16)
ዓዳን ~
Addan, Addon: አዲነ፣ አደን፣ ደን... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- አዳን፣ ዓዲና፣ ዓዲን፣ ዓድና]
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ቦታዎች:-
ዓዳን / Addan:
ከምርኮ ከተመለሱባቸው
ከተሞች፣ ነገር ግን የአባቶቻቸውን ቤቶችና ዘራቸውን ወይም ከእስራኤል ወገን መሆናቸውን ያስታውቁ ዘንድ
ካልቻሉ፥ (ዕዝ 2፡59)
ዓዳን / Addon:
(ነህ 7:61)
ዓድላይ ~ Adlai: አድሎ፣ ሚዛን፣ ፍርድ፣ ፍትሕ... ማለት
ነው። የዳዊት
እረኞች አለቃ፣
የሻፍጥ አባት፥ “... በሸለቆቹም ውስጥ በነበሩት ከብቶች ላይ የዓድላይ ልጅ ሻፍጥ ሹም
ነበረ”
(1 ዜና 27:29)
ዓድና ~
Adna, Adnah: አዲነ፣ አደን፣ ደን፣ ደኔ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ዓዲና፣ ዓዲን፣ ዓዳን፣ አዳን]
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ዓድና / Adna:
1.
ከካህናቱ ወገን ልጆች እንግዶቹን ሴቶች ያገቡ፥ ከፈሐት ሞዓብ ልጅ፥
(ዕዝ 10:30)
2.
በዮአቂም ዘመን የአባቶች ቤቶች አለቆች ከነበሩ፥ (ነህ 12፡15)
ዓድና / Adnah:
1.
ዳዊትም ከፍልስጥኤማውያን ጋር ሳኦልን ሊወጋ በመጣ ጊዜ ከምናሴ ወገን ሰዎች ወደ ዳዊት ከከዱ፥ (1 ዜና 12፡20)
2.
የኢዮሣፍጥ ፥
በኢየሩሳሌም ጽኑዓን
ኃያላን ሰልፈኞች
ከነበሩ፥ (2 ዜና
17:14)
ዓድዓዳ ~
Adadah:
በይሁዳ ደቡባዊ ዳርቻ የሚገኝ ከተማ፥ “ቀብስኤል፥ ዔዴር፥ ያጉር፥ ቂና፥ ዲሞና፥ ዓድዓዳ፥ ቃዴስ፥ ሐጾር፥ ዪትናን፥” (ኢያ 15:22)
ዓዶላም ~
Adullam:
‘ዓድሎ ዓለም፣ የሕዝብ ፍርድ፣ የዓለም ፍትኅ’ ማለት ነው። ከጥንታዊ የከነናውያን የመናገሻ ከተማ፥ “የዓራድ ንጉሥ፥ የልብና ንጉሥ፥ የዓዶላም ንጉሥ” (ኢያ 12:15፥15:35)
ዓጣራ ~ Atarah: ‘ዘውድ’
ማለት ነው።
የይረሕምኤል ሚስት፥
የኦናም እናት፥ “ለይረሕምኤልም ዓጣራ የተባለች ሌላ ሚስት ነበረችው እርስዋም የኦናም እናት
ነበረች።”
(1 ዜና 2:26)
ዓጽሞን~ Azmon: ‘ጽኑ፣ ብርቱ፣ ጠንካራ’ ማለት ነው። የቅድስት አገር ደቡባዊ ዳርቻ፥
“ዳርቻችሁም በአቅረቢም ዐቀበት
በደቡብ በኩል
ይዞራል ወደ
ጺንም ያልፋል
መውጫውም በቃዴስ
በርኔ በደቡብ
በኩል ይሆናል
ወደ ሐጸርአዳር
ይሄዳል ወደ ዓጽሞንም ያልፋል” (ዘኊ 34:4፣5፤ ኢያ 15:4)
ዔሊዮዔናይ ~
Elioenai:
ኤል ዓየነ፣ አምላክ ያየው፣ ጌታ ያየው... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ኤሊሆዔናይ፣ ኤሊዔናይ፣ ኤልዮዔናይ]
‘ኤል’ እና ‘ዓይን’ ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
በግዞት ሲኖሩ እንግዳ ሚስቶች ካገቡ፣ የዛቱዕ ልጅ፥ (ዕዝ 10:27)
ዔሳው ~
Esau:
እሱ፣ የሹ፣ የእሱ፣ የሽው... ማለት ነው። የይስሐቅ ልጅ፥ የያዕቆብ ወንድም፥ “በፊትም የወጣው
ቀይ ነበረ፥
ሁለንተናውም ጠጕር
ለብሶ ነበር
ስሙም ዔሳው ተባለ።” (ዘፍ25:25)
ዔሪ ~
Eri:
‘እረኛዬ፣ ጠባቂዬ’ ማለት ነው። የጋድ ልጅ፥ “ከሹኒ የሹናውያን ወገን፥ ከኤስናን የኤስናናውያን ወገን፥ ከዔሪ የዔራውያን ወገን፥” (ዘኊ 26:16)
ዔር ~
Ar, Er: ‘መግነን፣ መባነን፣ መገለጥ’ ማለት ነው። በሞዓባውያን ዘንድ ያለ ቦታ፥ “እሳት ከሐሴቦን፥ ነበልባልም ከሴዎን ከተማ ወጣ የሞዓብን ዔር፥ የአርኖንን ተራራ አለቆች በላ” (ዘኊ 21:28፤ ኢሳ 15:1)
ዔር / Er: እረኛ፣ ጠባቂ ማለት ነው።
1.
የይሁዳ ትልቁ ልጅ፥ “ፀነሰችም ወንድ ልጅንም ወለደች ስሙንም ዔር ብላ ጠራችው።” (ዘፍ 38:3-7፤ ዘኊ 26:19)
2.
የሴሎም ወገን፥ የሌካ አባት፥ “የይሁዳም ልጅ የሴሎም ልጆች የሌካ አባት ዔር፥ የመሪሳ አባት ለዓዳ፥ ከአሽቤዓ ...” (1 ዜና 4:21)
3.
በጌታ የዘር ሐረግ የተጠቀሰ፥ የኤልሞዳም አባት፥ “የሚልኪ ልጅ፥ የሐዲ ልጅ፥ የዮሳስ ልጅ፥ ... የኤር ልጅ፥” (ሉቃ 3:28)
ዔቄር ~ Eker: ‘መካን፣ ጥፍ፣ የገበረ መሬት’
ማለት ነው። የይሁዳ ወገን፥ “የይረሕምኤል የበኵሩ የራም ልጆች መዓስ፥ ያሚን፥ ዔቄር ነበሩ” (1 ዜና 2:27)
ዔባል፣ ዖባል ~ Ebal: ‘ድንጋይ፣ ዓለት’ ማለት ነው።
1.
ከሦባል ልጆች አንዱ፥ “የሦባል ልጆችም እነዚህ ናቸው ዓልዋን፥ ማኔሐት፥ ዔባል፥ ስፎ፥ አውናም።” (ዘፍ 36:23፤ 1 ዜና 1:40)
2.
የዮቅጣን ልጅ፥ “አውዛልን፥ ደቅላን፥ ዖባልን፥ አቢማኤልን፥” (1 ዜና
1:22)
ዔቤር ~
Eber:
እብር፣ ኅብር፣ አባሪ፣ ረዳት፣ ተባባሪ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ዔቦር፣ ሔቤር፣ አቤር፣ ዔብሪ፣ ዔብሮን፣ አቤር፣ ዔብሮና፣ ዕብራዊ፣ ኦቦር፣ ኬብሮን]
Eber- ‘ኅብር’
ከሚለው ቃል የመጣ ስም ሲሆን ‘አበረ’ ከሚለው ግስ የተገኘ ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
በዮአቂም ዘመን የአባቶች ቤቶች አለቆች፥ (ነህ 12:20)
2.
የኤልፍዓል ልጅ፥
(1 ዜና 8:12)
3.
የሰሜኢ ልጅ፥
(1 ዜና 8:22፣23)
. የሳላ ልጅ፥ ዔቦር፥ (ዘፍ 10፡24)፣ አቤር ፥ (ሉቃ 3:35)
ዔብሪ ~ Ibri: እብር፣ ኅብር፣ አባሪ፣ ረዳት፣ ተባባሪ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ዔቦር፣ ሔቤር፣ አቤር፣ ዔብሮን፣ ዔቤር፣ ዔብሮና፣ ዕብራዊ፣ ኦቦር፣ ኬብሮን] ‘ኅብር’ ከሚለው ቃል የመጣ ስም ነው።
በዳዊት ዘመን የነበረ፣ የሜራሪ ልጅ፥ ዔብሪ፥ (1 ዜና 24፡27)
ዔብሮና ~
Ebronah:
ኤብረን፣ አብረን፣ ኅብር፣ አባሪ፣ ረዳት፣ ተባባሪ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ዔቦር፣ ሔቤር፣ ዔብሪ፣ አቤር፣ ዔቤር፣ ዕብራዊ፣
ኦቦር፣ ኬብሮን]
‘ኅብር’
ከሚለው ቃል የመጣ
ስም ነው።
የእስራኤልም ልጆች
ጕዞ ከሙሴና
ከአሮን እጅ
በታች በጭፍሮቻቸው
ከግብፅ በወጡ ጊዜ፥ ከአለፉባቸው ቦታዎች፥ “ከዮጥባታም ተጕዘው በዔብሮና ሰፈሩ...”
(ዘኁ 33፡34፣35)
ዔብሮን ~ Hebron:
ሄብሮን፣ ኅብር፣ አባሪ፣ ረዳት፣ተባባሪ፣ ማኅበርተኛ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ዔቦር፣ ሔቤር፣ አቤር፣ ዔብሪ፣ ዔቤር፣ ዕብራዊ፣ ኦቦር፣ ኬብሮን]
[ኅብረት ማለት
ነው / መቅቃ]
. አብራም የሰፈረበት የቦታ ስም፥ “.. በኬብሮን ባለው በመምሬ የአድባር ዛፍ ተቀመጠ በዚያም ለእግዚአብሔር መሠውያን ሠራ” (ዘፍ 13፡18)
. የቀዓት ልጅ፥ (ዘጸ 6:18)፣ (ዘኁ 3:19) ፥ (1
ዜና 6:2፣ 18)፣ (1
ዜና23:12)
ዔቦር ~
Eber:
እብር፣ ኅብር፣ አባሪ፣ ረዳት፣ ተባባሪ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ሔቤር፣ አቤር፣ ዔብሪ፣ ዔብሮን፣ ዔቤር፣ ዔብሮና፣ ዕብራዊ፣ ኦቦር፣ ኬብሮን]
‘ኅብር’
ከሚለው ቃል
የመጣ ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
. የሳላ ልጅ፥ (ዘፍ 10፡24) ፣ አቤር -
(ሉቃ 3:35)
. በዮአቂም ዘመን ከአባቶች ቤቶች አለቆች፣ ካህን፥ ዔቤር- (ነህ 12:20)
. የኤልፍዓል ልጅ፥
ዔቤር-
(1 ዜና 8:12)
. የሰሜኢ ልጅ፥
ዔቤር-
(1 ዜና 8:22፣23)
ዔቴር ~
Ether:
‘ተራፊ’
ማለት ነው። በደልዳላው የይሁዳ ክፍል ያለ የይሁዳ ከተማ። “ልብና፥ ዔቴር፥ ዓሻን፥ ይፍታሕ፥ አሽና፥” (ኢያ 15:42)
ዔናቅ ~
Anak:
አነቅ፥ አንገት... ማለት ነው። የአርባቅ ልጅ፥ “እግዚአብሔርም ኢያሱን እንዳዘዘው ... ድርሻ አድርጎ ሰጠው እርስዋም ኬብሮን ናት፥ ይህም አርባቅ የዔናቅ አባት ነበረ።” (ኢያ 15:13፥ 21:11)
ዔናን ~
Enan:
‘ዓይን፣ ዓይናማ’ ማለት ነው። እስራኤላውያን በሲና ምድረ ባዳ፥ የሕዝብ
ቆጠራ በተደረገ
ጊዜ፥ አለቃ
የነበረ፥ የአኪሬ
አባት፥ “ከንፍታሌም የዔናን ልጅ አኪሬ”
(ዘኊ 1:15)
ዔዝሪ ~
Ezri:
እዝሬ፣ ዘሬ፣ ወገኔ፣ ዘመዴ፣ ረዳቴ... ማለት ነው። [ተዛማች ስም- አዛርያ]
‘ዘር’ ከሚለው ቃል ጋር የተገኘ ስም ነው። የክሉብ
ልጅ፥ (1 ዜና 27፡26)
ዔዴር ~ Eder: እድር፣ ማኅበር፣ መንጋ... ማለት ነው።
1. በደቡብ በኩል በምድራቸው ዳርቻ አጠገብ እስከ ኤዶምያስ ድንበር ካሉት የይሁዳ ልጆች ነገድ ከተሞች፥ “ቀብስኤል፥ ዔዴር፥ ያጉር፥ ቂና፥”
(ኢያ 15:22)
2. በዳዊት ዘመን የነበረ፥ የመራሪ ወገን፥ “የሙሲ ልጆች ሞሖሊ፥ ዔደር፥
ኢያሪሙት ሦስት
ነበሩ።”
(1 ዜና 23:23፥ 24:30)
ዔዴን ~ Eran: ‘እረኛ፣ ጠባቂ’ ማለት
ነው። የኤፍሬም
የትልቁ ልጅ፥
የሱቱላ ልጅ፥ “እነዚህ የሱቱላ ልጆች ናቸው፤ ከዔዴን የዔዴናውያን ወገን። ከዔዴን የዔዴናውያና
ወገን”
(ዘኊ 26:36)
ዔድን ~ Eden: ‘አስደሳች’ ማለት ነው።
1. የመጀመሪ ሰዎች መኖሪያ፥
“እግዚአብሔር አምላክም በምሥራቅ በዔድን ገነትን ተከለ የፈጠረውንም ሰው ከዚያው አኖረው።” (ዘፍ 2:8-17)
2. “ካራንና ካኔ ዔድንም ነጋዴዎችሽ ነበሩ አሦርና ኪልማድ ነጋዴዎችሽ ነበሩ።” (ሕዝ 27:23)
3. የዩአክ ልጅ፥ “ሌዋውያኑም፥ ... የይሃሌልኤል ልጅ ዓዛርያስ፥ ከጌድሶንም
ልጆች የዛማት
ልጅ ዩአክና
የዩአክ ልጅ
ዔድን፥”
(2 ዜና 29:12)
ዔግላ ~ Eglah: ‘ጊደር’
ማለት ነው።
ዳዊት በሔብሮን
በነገሠ ጊዜ
የነበረችው ሚስት፥ “ስድስተኛውም የዳዊት ልጅ ሚስት የዔግላ ልጅ ይትረኃም ነበረ።
እነዚህም ለዳዊት
በኬብሮን ተወለዱለት።” (2 ሳሙ
3:5፤ 1
ዜና 3:3)
ዔግሎም ~
Eglon: ‘ጥጃ፣ እምቦሳ... ’ ማለት ነው።
1. የሞባውያን ንጉሥ፥ “የእስራኤልም ልጆች በእግዚአብሔር ፊት እንደ ገና
ክፉ ሥራ
ሠሩ። በእግዚአብሔርም ፊት
ክፉ ስለ
ሠሩ እግዚአብሔር የሞዓብን ንጉሥ ዔግሎምን በእስራኤል ላይ አበረታባቸው።” (መሣ 3:12)
2. የይሁዳ የታችኛው ግዛት ከተማ፥ ኦዶላም፥ “ኦዶላም፥ ከቦን፥ ለሕማስ፥ ኪትሊሽ፥ ግዴሮት፥ ቤትዳጎን፥ ናዕማ፥ መቄዳ አሥራ ስድስት ከተሞችና መደሮቻቸው።” (ኢያ 15:39)
ዔጼም ~
Ezem: አጽም፣ አጥንት... ማለት ነው። ከሺሞን ከተሞች አንዱ፥ “በሐጸርሹዓል፥
በቢልሃ፥ በዔጼም” (1 ዜና 4:29)
ዔጽዮንጋብር ~
Eziongaber:
ጽዬን ገብር፣ ገብረ ጽዮን፣ የጽዮን አገልጋይ፣ መመኪያ... ማለት ነው።
‘ጽዮን’
እና ‘ገብር’
ከሚሉ ሁለት
ቃላት የተመሠረተ
ስም ነው።
የእስራኤልም ልጆች ጕዞ ከሙሴና ከአሮን እጅ በታች በጭፍሮቻቸው ከግብፅ ወጡ ጊዜ፥ ያለፉበት የቦታ ስም፥ “ከዔብሮናም ተጕዘው በዔጽዮንጋብር ሰፈሩ።”
(ዘኁ 33፡35)
ዔፋ ~ Ephah: ‘የጠወለገ፣ የደከመ’
ማለት ነው።
1. በይሁዳ የዘር ሐረግ፥
የካሌብ ቁባት
፥ “የካሌብም ቁባት ዔፋ ሐራንን፥ ሞዳን፥
ጋዜዝን ወለደች።” (1 ዜና 2:46)
2. ሔፋ፥ “ሐራንም ጋዜዝን ወለደ። የያህዳይም ልጆች ሬጌም፥ ኢዮታም፥ ጌሻን፥ ፋሌጥ፥ ሔፋ፥ ሸዓፍ ነበሩ።” (1 ዜና 2:47)
ዔፌር ~ Epher:
አፈር፣ ትቢያ፣ አቧራ... ማለት ነው።
‘አፈር’
ከሚለው ቃል
የመጣ ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1. የምድያም ልጅ፥ (ዘፍ 25:4)
2. ከጽኑዓን ኃያላን የታወቁ ሰዎች ከአባቶቻቸው ቤቶች አለቆች የነበረ፥ (1 ዜና 5:24)
ዕላም ~
Jaalam:
የለም፣ ጠፋ፣ ተሰወረ... ማለት ነው። የዔሳው ልጅ፥ “አህሊባማም የዑስን፥
የዕላምን፥ ቆሬን
ወለደች በከነዓን
ምድር የተወለዱለት
የዔሳው ልጆች
እነዚህ ናቸው።” (ዘፍ 36:5፣14፣18)
ዕሢኤል ~
Jaasiel, Jasiel: የሢ ኤል፣ የአምላክ ሥራ፣ ያምላክ ኃይል... ማለት ነው።
ዕሢኤል / Jaasiel: የዳዊት ጭፍራ፣ የአበኔር ልጅ፥ (1 ዜና 27:21)
ዕሢኤል / Jasiel:
“ኤልኤል፥ ዖቤድ፥ ምጾባዊው የዕሢኤል:” (1
ዜና 11 ፡47)
ዕቃ ቤቱ ~ Asuppim: ‘ማከማቻ፣ ማጠራቀሚያ’ ማለት
ነው። የካህናቱ
አልባሳትና የንዋየ ቅዱሳት ማስቀመጫ ክፍል፥ “በምሥራቅ በኩል ስድስት ሌዋውያን ነበሩ። በሰሜን በኩል ለየዕለቱ አራት፥ በደቡብ በኩል ለየዕለቱ አራት፥ ለዕቃ ቤቱም ሁለት
ሁለት ነበሩ።” (1 ዜና 26:15፣17)
ዕብራዊ ~
Hebrew:
ኂብሪው፣ ዕብር፣ ዕብራዊ፣ ዕብራይስጥ... ማለት ነው።
‘ኅብር’ ከሚለው ቃል የመጣ የነገድ ስም ነው።
አብራም ዕብራዊ ተብሎ ተጠራ፥ “አንድ የሸሸ ሰውም መጣ፥ ለዕብራዊው ለአብራምም
ነገረው እርሱም
...” (ዘፍ 14:13)
. ዮሴፍ ዕብራዊ ተብሎ ተጠራ፥ (ዘፍ 41፡12)
. የአማቴ ልጅ፣ ነቢዩ ዮናስ፥ “እርሱም፦ እኔ ዕብራዊ ነኝ ...” (ዮና 1:9)
. ሐዋርያው ጳውሎስ፥ “... ከዕብራውያን ዕብራዊ ነኝ፤ ስለ ሕግ ብትጠይቁ፥ ፈሪሳዊ
ነበርሁ”
(ፊል 3:5)
ዕንባቆም ~
Habakkuk: ዕንባ አቁም፣ አጽናኝ፣ አስተዛዛኝ፣ ለመከራ ደራሽ፣ የሐዘን አስረሽ፣ ከጭንቅ አዳኝ... ማለት ነው።
‘ዕንባ’ እና ‘አቁም’
ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
ከአሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት በስምንተኛ ተራ ላይ ይገኛል፥ “ነቢዩ ዕንባቆም ያየው ሸክም
ይህ ነው።”
(ዕንባ1:1)
ዕዝራ ~
Ezra:
እዝራ፣ ዘረ፣ ዘር፣ ወገን፣ ዘመድ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ዓዙር]
‘ዘረ’
ከሚለው ግስ
የመጣ ስም ነው።
ከሰላትያል ልጅ ከዘሩባቤልና ከኢያሱ ጋር ከምርኮ የተመለሰ፣ የሠራያ ልጅ፥ (ዕዝ7:
1) ፣ (ነህ 12፡2)
ዖሜጋ ~ Omega: የግሪክ
የመጨረሻው ፊደል።
የሁሉ ነገር
ፍጻሜና መጨረሻ መግለጫ ሁኖ ያገለግላል፥ “ያለውና የነበረው የሚመጣውም ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ። አልፋና ዖሜጋ እኔ ነኝ ይላል” (ራእ 1:8፣11)
ዖምሪ ~
Omri:
ኦማር፣ ማሪ፣ መሐሪ፣ ይቅር ባይ፣ አምላካዊ... ማለት ነው።
[ተዛማጅ ስሞች- ኦማር፣ አምሪ]
በዚህ ስም የሚታወቁ አራት ሰዎች አሉ።
1. የቤኬር ልጅ፥ (1 ዜና 7:8)
2.የሚካኤል ልጅ
፥ (1 ዜና 27:18)
3. የባኒ ልጅ፥ (1 ዜና 9:4)
. ኦማር-
(1 ነገ 16:15-27)
ዖርፋ ~ Orpah: ‘አንገት’
ማለት ነው።
የኑኃሚን፥ ምራት፥
የልጇ ሚስት፥
“እነርሱም ከሞዓባውያን ሴቶች
ሚስት አገቡ። የአንዲቱ
ስም ዖርፋ የሁለተኛይቱም ስም ሩት
ነበረ። በዚያም
አሥር ዓመት
ያህል ተቀመጡ” (ሩት
1 2:4፣14)
ዖባል ~ Obal: ‘እራቁት’
ማለት ነው።
የዮቅጣን ልጅ፥ “ደቅላንም፥ ዖባልንም፥
አቢማኤልንም፥”
(ዘፍ 10:28)
ዖቤድኤዶም ~
Obed-Edom: የኤዶም አገልጋይ ማለት ነው።
1. ሌዊያዊ፥ ከቃል ኪዳኑ ታቦት ጠባቂዎች አንዱ ፥ “እግዚአብሔርም ባርኮታልና ዖቤድኤዶም ልጆች ነበሩት። በኵሩ ሸማያ፥ ሁለተኛው ዮዛባት፥ ሦስተኛው ኢዮአስ፥
አራተኛው ሣካር፥
አምስተኛው ናትናኤል፥” (1 ዜና 26:1፣4-8)
2. የደቡባዊውን መግቢያ ከሚጠብቁ፣ ከቤተመቅደሱ በረኞች አንዱ፥ “ከእነርሱም ጋር በሁለተኛው ተራ የሆኑትን ወንድሞቻቸውን ዘካርያስን፥ ቤንን፥ ያዝኤልን፥
ሰሚራሞትን፥ ይሒኤልን፥
... በረኞችንም ዖቤድኤዶምንና
ይዒኤልን አቆሙ።” (1 ዜና 15:18፣21፥26:4፣8፣15)
3. የቤተ መቅደሱ ዕቃ ቤትና የንጉሡን ቤት መዛግብት
አለቃ፥ “ወርቁንና ብሩን ሁሉ፥ በእግዚአብሔርም ቤት ከዖቤድኤዶም ጋር የነበሩትን ዕቃዎች ሁሉ፥ የንጉሡን
ቤት መዛግብት፥
...” (2 ዜና 25:24)
ዖትኒ ~
Othni:
‘የሕያው አንበሳ’ ማለት ነው። የሸማያ ልጅ፥ “ለሸማያ ልጆች ዖትኒ፥ ራፋኤል፥ ዖቤድ፥ ወንድሞቹም...” (1 ዜና 26:7)
ዖዛ ~
Uzzah:
‘ጥንካሬ’ ማለት ነው። የአሚናዳብ ልጅ፥ “የእግዚአብሔርንም ታቦት
... የአሚናዳብ ልጆችም
ዖዛ እና
አሒዮ አዲሱን
ሰረገላ ይነዱ
ነበር”
(2 ሳሙ 6:3)
ዖዛዝ ~
Azaz:
‘አዛዥ፣ ብርቱ’
ማለት ነው። የቤላ አባት፥ “ዘካርያስ፥ እስከ ናባውና እስከ በኣልሜዎን ድረስ በአሮዔር የተቀመጠው የኢዮኤል ልጅ የሽማዕ ልጅ የዖዛዝ ልጅ
ቤላ”
(1 ዜና 5:8)
ዖዛያ ~ Hazaiah: ‘ሕያው አምላክ
ያየው’
ማለት ነው።
የሴሎናዊውያን ወገን የሆነ የይሁዳ ሰው። “የሴሎናዊውም ልጅ የዘካርያስ ልጅ የዮያሪብ ልጅ የዓዳያ ልጅ የዖዛያ ልጅ የኮልሖዜ ልጅ የባሮክ ልጅ መዕሤያ።” (ነህ 11:5)
ዖዝያ ~ Uzziah: ‘የሕያው ኃይል’ ማለት ነው።
1. የይሁዳ ንጉሥ፥ “አባቱም ዖዝያን እንዳደረገ ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት ቅን ነገር አደረገ። ነገር
ግን ወደ
እግዚአብሔር መቅደስ
አልገባም ሕዝቡም
ገና ይበድል
ነበር።”
(2 ዜና 27:2)
2. “ልጁ አቢሳፍ፥ ልጁ አሴር፥ ልጁ ኢኢት፥ ልጁ ኡሩኤል፥ ልጁ ዖዝያ፥ ልጁ
ሳውል።”
(1 ዜና 6:24)
3. የካሪም ልጅ፥ “ከካሪም ልጆችም መዕሤያ፥ ኤልያስ፥ ሸማያ፥ ይሒኤል፥ ዖዝያ።” (ዕዝ 10:21)
4. የዘካርያስ ልጅ፥ ...ከይሁዳ ልጆች ከፋሬስ ልጆች የመላልኤል ልጅ የሰፋጥያስ ልጅ የአማርያ ልጅ የዘካርያስ ልጅ የዖዝያ ልጅ አታያ” (ነህ 11:4)
5. የዮናታን አባት፥ “በንጉሡም ቤተ መዛግብት ላይ የዓዲኤል ልጅ ዓዝሞት ሹም ነበረ። በሜዳውም
... ላይ የዖዝያ ልጅ ዮናታን ሹም
ነበረ”
(1 ዜና 27:25)
ዖዝያን ~
Ozias:
‘የጌታ ኃይል’ ማለት ነው። “አሣፍም ኢዮሣፍጥን ወለደ፤ ኢዮሣፍጥም
ኢዮራምን ወለደ፤
ኢዮራምም ዖዝያንን
ወለደ፤”
(ማቴ 1:8፣9)
ዖዴድ ~ Oded: ማዋደድ፣
ማስማማት፣ ማነጽ፣
መጠገን...
ማለት ነው።
1. የነቢዩ ዓዛርያስ አባት፥ “የእግዚአብሔርም መንፈስ በዖዴድ ልጅ በዓዛርያስ ላይ
ሆነ”
(2 ዜና 15:1፣8)
2. በንጉሥ አካዝ ዘመን የነበረ ሌላ ነቢይ፥ “በዚያም ዖዴድ የተባለ የእግዚአብሔር ነቢይ ነበረ ወደ ሰማርያም የሚመጣውን ጭፍራ ሊገናኘው ወጣ፥ እንዲህም
አላቸው፦ ...” (2 ዜና 28:9-15)
ዖፌል ~ Ophel: ‘ኮረብታ’ ማለት ነው። የጥንታዊ ኢየሩሳሌም ክፍል፥ “የእግዚአብሔርን ቤት የላይኛውን በር ሠራ፥ በዖፌልም ቅጥር ...” (2 ዜና 27:3)
ዖፍኒ ~ Ophni: ‘ሻጋታ’ ማለት ነው። የብንያማውያን ከተማ፥ “ዓዊም፥ ፋራ፥ ኤፍራታ፥ ክፊርዓሞናይ፥ ዖፍኒ፥ ጋባ አሥራ ሁለት ከተሞችና መንደሮቻቸው” (ኢያ 18:24)
No comments:
Post a Comment