ተሐሸ ~ Thahash: ታጋሽ፣ ታዛዥ፣ ጭምትማለት ነው። የአብርሃም ወንድም፣ የናኮር ልጅ፥ (ዘፍ 22:24) “ሬሕማ የሚሉአት ቁባቱ ደግሞ ጥባህን፥ ገአምን፥ ተሐሸን፥ ሞክሳን ወለደች

ተሒናን ~ Tehinnah: አቤቱታማለት ነው። የዒርናሐሽን አባት፥ ኤሽቶንም ቤትራ ፋንና ፋሴሐን የዒርናሐሽንም አባት ተሒናን ወለደ እነዚህ የሬካ ሰዎች ናቸው።” (1 ዜና 4:12)

ተላሚ፣ ተልማይ ~ Talmai: መግል፣ ቦይ፣ ትልም... ማለት ነው።

1. የዔናቅ ልጅ፥ በካሌብ በኩል በይሁዳ ሰዎች ከተገደሉ፥ በደቡብም በኩል ውጡ፥ ወደ ኬብሮንም ደረሱ በዚያም የዔናቅ ልጆች አኪመን፥ ሴሲ፥ ተላሚ ነበሩ። ... (ዘኊ 13:22 ኢያ 15:14 መሣ 1:10)

2. የመዓካ አባት፥ ተልማይ፥ ሁለተኛውም የቀርሜሎሳዊው የናባል ሚስት ከነበረች ከአቢግያ የተወለደው ዶሎሕያ ነበረ። ሦስተኛውም ከጌሹር ንጉሥ ተልማይ ልጅ ከመዓካ የተወለደው ... (2 ሳሙ 3:3 13:37)

ተላሳር ~ Telassar: መነጠቅማለት ነው። የአሦርያ ደቡባዊ ምሥራቅ ክፍለ ግዛት፥ (ኢሳ 37:12 2 ነገ 19:12) አባቶቼ ያጠፉአቸውን ጎዛንን፥ ካራንን፥ ራፊስን፥ ተላሳር የነበሩትንም የዔድንን ልጆች የአሕዛብ አማልክት አዳኑአቸውን?”

ተሙዝ ~ Tammuz: ይወት ቅንጣቢማለትነው። ሕዝቅኤል ባየው በራእይ ሴቶች ተሰብስበው የሚያለቅሱለት፥ እግዚአብሔርን ያላስደሰተ ተግባር፥ ወደ ሰሜንም ወደሚመለከተው ወደ እግዚአብሔር ቤት በር መግቢያ አመጣኝ እነሆም፥ ሴቶች ተሙዝ እያለቀሱ በዚያ ተቀምጠው ነበር።” (ሕዝ 8:14)

ተምና ~ Timnah: ተመን፣ መጠን፣ ድርሻ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ቲምናዕ]

ተመነከሚለውቃል የተገኘ ስም ነው።

ለይሁዳ ልጆች በየወገናቸው በዙሪያው ያለ ድንበራቸው፥ (ኢያ 15:10) (ኢያ 15:57)

ተምና ~ Timnah: ተመን፣ ድርሻ... ማለት ነው።

1. የይሁዳ ከተማ፥ (ኢያ 15:10) “ድንበሩም ከበኣላ በምዕራብ በኩል ወደ ሴይር ተራራ ዞረ ክሳሎን ወደምትባል ወደ ይዓሪም ተራራ ወገን በሰሜን በኩል አለፈ ወደ ቤትሳሚስ ወረደ፥ ተምና በኩልም አለፈ።

2. በይሁዳ ተራራ ላይ ያለ ከተማ፥ (ኢያ 15:57) ዮቅድዓም፥ ዛኖዋሕ፥ ቃይን፥ ጊብዓ፥ ተምና አሥር ከተሞችና መንደሮቻቸው።

3. የኤዶም መስፍን፥ ቲምናዕ፥ (ዘፍ 36:40) “የዔሳውም የአለቆቹ ስም በወገናቸው በስፍራቸው በስማቸውም ይህ ነው ቲምናዕ አለቃ፥ ዓልዋ አለቃ፥ የቴት አለቃ

ተምናሔሬስ ~ Timnath-heres: የፀሓይ ክፋይማለት ነው። የኢያሱ የቀብር ቦታ፥ በተራራማውም በኤፍሬም አገር በገዓስ ተራራ በሰሜን ባለችው በርስቱ ዳርቻ ተምናሔሬስ ቀበሩት።” (መሣ 2:9)

ተሰሎንቄ ~Thessalonic: ጳውሎስ በሐዋርያዊ ጉዞው ካለፈባቸው ከተሞች፥ በአንፊጶልና በአጶሎንያም ካለፉ በኋላ ወደ ተሰሎንቄ መጡ፥ በዚያም የአይሁድ ምኵራብ ነበረ።” (ሐዋ 17:1-4 1 ተሰ 1:9)

ተራፊም ~ Teraphim: ትርፋም፣ ትርፍ፣ ጸጋን ሰጭ ሀብት የሚያድል... ማለት ነው። የጣዖት ስም፥ ሰውውም ሚካ የአምላክ ቤት ነበረው ኤፉድና ተራፊም አደረገ፥ ከልጆቹም አንዱን ቀደሰው፥ ካህንም ሆነለት።” (መሣ 17:5)

ተርሴስ ~ Tarshish: ምርመራማለት ነው።

1. የያዋን ልጅ፥ የያዋንም ልጆች ኤሊሳ፥ ተርሴስ ኪቲም፥ ሮድኢ ናቸው።” (ዘፍ 10:4 1 ዜና 1:7)

2. የአገር ስም፥ ኢዮሣፍጥም ወደ ኦፊር ሄደው ወርቅ ያመጡ ዘንድ ተርሴስ መርከቦች ሠራ ነገር ግን መርከቦቹ በዔጽዮንጋብር ተሰበሩ እንጂ አልሄዱም” (1 ነገ 22:48 2 ዜና 9:21)

ተርታቅ ~ Tartak: የጨለማው ልዑልማለት ነው። በሰማርያ የነ ሰዎች ያመልኩት የነበረ፥ የጣዖት ስም፥ የሐማትም ሰዎች አሲማትን ሠሩ አዋውያንም ኤልባዝርንና ተርታቅ ሠሩ ... ለሴፈርዋይም አማልክት ለአድራሜሌክና ለአነሜሌክ ልጆቻቸውን በእሳት ያቃጥሉ ነበር” (2 ነገ 17:31)

ተርታን ~ Tartan: የጦር አዛዥ ማለት ነው።

1. የአሦር ንጉሥ ወደ ሕዝቅኤል ከላካቸው አንዱ፥ የአሦርም ንጉሥ ተርታንንና ራፌስን ራፋስቂስንም ከብዙ ሠራዊት ጋር ከለኪሶ ወደ ንጉሡ ወደ ሕዝቅያስ ወደ ኢየሩሳሌም ላከ። ...” (2 ነገ 18:17)

2. የአሦር ንጉሥ፣ የሳርጎን የጦ አዛዥ፥ (ኢሳ 20:1) የአሦር ንጉሥ ሳርጎን ተርታን በሰደደ ጊዜ እርሱም ወደ አዛጦን በመጣ ጊዜ አዛጦንም ወግቶ በያዛት ጊዜ፥

ተርአላ ~ Taralah: መጠም፣ ማጠቃለል ማለት ነው። ለብንያም ልጆች የተሰጠ፥ የቦታ ስም፥ ሬቄም፥ ይርጵኤል፥ ተርአላ ጼላ፥ ኤሌፍ፥ ኢየሩሳሌም የምትባል የኢያቡስ ... የብንያም ልጆች ርስት በየወገኖቻቸው ይህ ነበረ።” (ኢያ 18:27)

ተቤራ ~ Taberah: ተበራ በራ፣ ነደደ፣ ተቃጠለ... ማለት ነው። እስራኤል በማጉረምረማቸው እሳት የወረደበት፥ በፋራን ምድረ በዳ የነበረ፥ የቦታ ስም፥ የእግዚአብሔርም እሳት በመካከላቸው ስለነደደች የዚያን ስፍራ ስም ተቤራ ብሎ ጠራው።” (ዘኊ 11:3 ዘዳ 9:22)

ተንሑሜት ~ Tanhumeth: ማጽናናትማለት ነው። በጎዶልያስ ዘመን የነበረ፥ የሠራያ ልጅ፥ የጭፍሮቹም አለቆች ሁሉ፥ የናታንያ ልጅ እስማኤል፥ የቃሬያም ልጅ ዮሐናን፥ የነጦፋዊውም ተንሑሜት ልጅ ሠራያ፥ የማዕካታዊውም ልጅ ያእዛንያ፥ ሰዎቻቸውም ... ወደ ምጽጳ መጡ።” (2 ነገ 25:23 ኤር40:8)

ተንትናይ ~ Tatnai: ስጦታማለት ነው። የሰላትያል ልጅ ዘሩባቤል የኢዮሴዴቅም ልጅ ኢያሱ ተነሥተው በኢየሩሳሌም ያለውን የእግዚአብሔርን ቤት መሥራት ሲጀምሩ መጥተ ከጠየቋቸው አንዱ፥ በዚያም ዘመን በወንዝ ማዶ የነበረው ገዥ ተንትናይ ደግሞ ሰተርቡዝናይ፥ ...” (ዕዝ 5:36 6:613)

ተድሞር ~ Tadmor: ም፣ የተምር ከተማ ማለት ነው። ሰሎሞን በምድረ በዳ የገነባው ከተማ፥ በምድረ በዳም ያለውን ተድሞርን፥ በሐማትም የሠራቸውን የዕቃ ቤቱን ከተሞች ሁሉ ሠራ።” (2 ዜና 8:4)

ቱሚም ~ Thummim: ትሙን፣ የታመነ፣ እውነተኛማለት ነው። በፍርዱ በደረት ኪስም ውስጥ ኡሪምንና ቱሚም ታደርጋለህ በእግዚአብሔርም ፊት በገባ ጊዜ በአሮን ልብ ላይ ይሆናሉ አሮንም በእግዚአብሔር ... (ዘጸ 28:30 ዘዳ 33:8 መሣ 1:1 20:18 1 ሳሙ 14:318 23:9 2 ሳሙ 21:1)

ቱባልቃይን ~ Tubal-cain: ምድራዊ ሀብትማለት ነው። የላሜሕን ልጅ፥ ሴላም ደግሞ ከናስና ከብረት የሚቀጠቀጥ ዕቃን የሚሠራውን ቱባልቃይን ወለደች። የቱባልቃይንም እኅት ናዕማ ነበረች (ዘፍ 4:22)

ቲሎን~ Tilon: ጥሎሽ፣ ስጦታ... ማለት ነው። ከሲሞን አራት ልጆች አንዱ፥ የሺሞንም ልጆች አምኖን፥ ሪና፥ ቤንሐናን፥ ቲሎን ነበሩ። የይሽዒም ልጆች ዞሔትና ቢንዞሔት ነበሩ።” (1 ዜና 4:20)

ቲምናዕ ~ Timnah: ተመን፣ መጠን፣ ድርሻ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ተምና]

ከዔሳው የአለቆች ስም፥ (ዘፍ 36:40)

ቲርሐቅ ~ Tirhakah: የከበረ ከፍተኛማለት ነው። የኢትዮጵያ ንጉሥ፥ እርሱም፦ የኢትዮጵያ ንጉሥ ቲርሐቅ ሊወጋህ መጥቶአል የሚል ወሬ በሰማ ጊዜ ደግሞ ወደ ሕዝቅያስ መልእክተኞችን ላከ፥ እንዲህ ሲል” (2 ነገ 19:9 ኢሳ 37:9)

ቲርያ ~ Tiria: ጥሪ፣ ጩኽት... ማለት ነው። ከይሁዳ ነገድ፥ የይሃሌልኤል ልጅ፥

... የይሃሌልኤል ልጆች ዚፍ፥ ዚፋ፥ ቲርያ አሣርኤል ነበሩ” (1 ዜና 4:16)

ቲርጻ ~ Tirzah: ደስታማለት ነው። የሰለጰዓድ ትንሿ ልጅ፥ የኦፌርም ልጅ ሰለጰዓድ ... የሴቶች ልጆቹ ስም ማህለህ፥ ኑዓ፥ ዔግላ፥ ሚልካ፥ ቲርጻ ነበረ።” (ዘኊ 26:33 27:1 36:11 ኢያ 17:3)

ቲቁዋ፣ ቴቁዋ ~ Tikvah: ተስፋማለት ነው።

1. ልብስ ጠባቂው፥ የሐስራ ልጅ፥ የሴሌም አባት፥ እንዲሁም ካህኑ ኬልቅያስና አኪቃም ዓክቦርም ሳፋንና ዓሳያም ወደ ልብስ ጠባቂው ወደ ሐስራ ልጅ ወደ ቲቁዋ ልጅ ወደ ሴሌም ሚስት ወደ ነቢያቱ ... (2 ነገ 22:14)

2. የሕዝያ አባት፥ ነገር ግን የአሣሄል ልጅ ዮናታንና ቴቁዋ ልጅ የሕዝያ ይህን ነገር ተቃወሙ፤ ሜሱላምና ሌዋዊውም ሳባታይ ረዱአቸው። (ዕዝ 10:15)

ቲቶ ~ Titus: የተከበረማለት ነው። ከጳውሎስና ከባርናባስ ጋር በኢየሩሳሌም ጉባኤ የነበረ፥ ከዚያ ወዲያ ከአሥራ አራት ዓመት በኋላ ከበርናባስ ጋር ቲቶ ደግሞ ይዤ ወደ ኢየሩሳሌም ሁለተኛ ወጣሁ፤ (ገላ 2:1-3 ሐዋ 15:2)

ቲኪቆስ ~ Tychicus: ወሳኝ፣ ቁርጥማለት ነው። የእስያ ሰው፥ ቅዱስ ጳውሎስን በጉዞው የተባበረ፥ የሸኙትም የቤርያው ሱሲጳጥሮስ ከተሰሎንቄ ሰዎችም

አርስጥሮኮስና ሲኮንዱስ የደርቤኑም ጋይዮስና ጢሞቴዎስ የእስያ ሰዎችም ቲኪቆስ ጥሮፊሞስም ነበሩ (ሐዋ 20:4 21:29 2 ጢሞ 4:20)

ቲድዓል ~ Tidal: ታደል፣ ታደለ፣ ተድላ፣ የታደለማለት ነው። የአሕዛብ ንጉሥ የነበረ፥ በሰናዖር ንጉሥ በአምራፌል፥ በእላሳር ንጉሥ በአርዮክ፥ በኤላም ንጉሥ በኮሎዶጎምር፥ በአሕዛብ ንጉሥ ቲድዓል ዘመን እንዲህ ሆነ” (ዘፍ 14:19)

ቲፍሳ ~ Tiphsah: መተላለ መሻገሪያማለት ነው። ሰሎሞን የነገሠበት የግዛት ድንበር፥ ከወንዙ ወዲህ ባሉት ነገሥታት ሁሉ ከወንዙም ወዲህ ባለው አገር ሁሉ ላይ ቲፍሳ ጀምሮ እስከ ጋዛ ድረስ ነግሦ ነበር ... (1 ነገ 4:24)

ታሐት ~ Tahath: ማረፊያ መነኻሪያማለት ነው።

1. የእስራኤል ልጆች በጉዞ ካረባቸው ቦታዎች፥ ከመቅሄሎትም ተጕዘው ታሐት ሰፈሩ” (ዘኊ 33:26)

2. ሰሎሞን የእግዚአብሔርን ቤት በኢየሩሳሌም እስኪሠራ ድረስ በመገናኛ ድንኳን ማደሪያ ፊት እያዜሙ ያገለግሉ ከነበሩ፥ ታሐት ልጅ፥ የአሴር ልጅ፥” (1 ዜና 6:37 9:22)

3. የኤፍሬም ልጆች ሹቱላ፥ ልጁ ባሬድ፥ ልጁ ታሐት ልጁ ኤልዓዳ፥ ልጁ ታሐት፥ ልጁ ዛባድ፥ ልጁ ሽቱላ (1 ዜና 7:20)

4. የኤፍሬም ልጆች ሹቱላ፥ ልጁ ባሬድ፥ ልጁ ታሐት፥ ልጁ ኤልዓዳ፥ ልጁ ታሐት ልጁ ዛባድ፥ ልጁ ሽቱላ (1 ዜና 7:20)

ታሐን ~ Tahan: ሰፈራማለት ነው። የኤፍሬም ልጅ፥ በየወገናቸው የኤፍሬም ልጆች እነዚህ ናቸው ከሱቱላ የሱቱላውያን ወገን፥ ከቤኬር የቤኬራውያን ወገን፥ ታሐን የታሐናውያን ወገን።” (ዘኊ 26:35)

ታማር ~ Tamar: ተምር፣ የተምር ዛፍ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ትዕማር]

የቦታ ስም፥ የደቡቡም ድንበር ታማር ጀምሮ እስከ ...” (ሕዝ 47:19 48:28)

ታምኒ ~ Tibni: ታማኒ፣ ታማኝ... ማለት ነው። የጎናትን ልጅ፥ በዚያም ጊዜ የእስራኤል ሕዝብ በሁለት ተከፈለ የሕዝቡም እኩሌታ የጎናትን ልጅ ታምኒ ያነግሡት ዘንድ ተከተለው እኩሌታውም ዘንበሪን ተከተለ።” (1 ነገ 16:2122)

ታራ ~ Tarah, Terah: ተራማለት ነው። እስራኤላውያን ከግብፅ ከወጡ በኋላ፥ በርቀት ከሰፈሩባቸው ቦታዎች አንዱ፥ ከታሐትም ተጕዘው ታራ ሰፈሩ” (ዘኊ 33:27)

       ታራ / Terah: ተራ፣ ሰፈራ ማለት ነው። የአብራም፣ የናኮር፣ የሐራን አባት፥ ታራ መቶ ዓመት ኖረ፥ አብራምንና ናኮርን ሐራንንም ወለደ” (ዘፍ 11:24-32)

ታሬዓ ~ Tahrea, Tarea: ንዴት፣ ጥላቻ ማለት ነው። የሚካ ልጅ፥

የሚካም ልጆች ፒቶን፥ ሜሌክ፥ ታሬዓ አካዝ ነበሩ። (1 ዜና 9:41)

       ታሬዓ / Tarea: ጠራ፣ ተጣራ፣ ጮኽ ማለት ነው። የሚካ ልጅ፥

የሚካም ልጆች ፒቶን፥ ሜሌክ፥ ታሬዓ አካዝ ነበሩ። (1 ዜና 8:35)

ታቦር ~ Tabor: ኮረ ማለት ነው። የዛብሎን ልጆች ርስት የተሰጠ የቦታ ድንበር፥ ድንበሩም ወደ ታቦር ወደ ሻሕጹማ፥ ወደ ቤትሳሚስ ደረሰ፥ የድንበራቸውም መውጫ ዮርዳኖስ ነበረ አሥራ ስድስት ... (ኢያ 19:22)

ታዕናክ ~ Taanach, Tanach: ማለት ነው። የከነናውያን ጥንታዊ ከተማ፥ ንጉሡን ኢያሱ የያዘው፥ የአዚፍ ንጉሥ፥ ታዕናክ ንጉሥ፥ የመጊዶ ንጉሥ፥” (ኢያ 12:21)

       ታዕናክ / Tanach: ከምናሴም ነገድ እኩሌታ ታዕናክንና መሰምርያዋን፥ ጋትሪሞንንና መሰምርያዋን ሁለቱን ከተሞች ሰጡአቸው (ኢያ 21:25)

ታዴዎስ ~ Thaddeus: ተወዳሽ፣ ተወዳጅ፣ ተመስጋኝ... ማለት ነው። ልብድዮስ ለተባለው ሐዋርያ መጠሪያ ስም፥ ፊልጶስም ... የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብም ታዴዎስ የተባለው ልብድዮስ፥” (ማቴ 10:3 ማር 3:18)

ታጱዋ ~ Tappuah: የፍራፍሬ ከተማማለት ነው።

1. በይሁዳ ሸለቆ የነበረ የከተማ ስም፥ ቀደም ብሎ የከነናውያን መናገሻ የነበረ፥ ታጱዋ ንጉሥ፥ የኦፌር ንጉሥ፥ የአፌቅ ንጉሥ፥ (ኢያ 12:17)

2. በኤፍሬም ድንበር የሚገኝ ከተማ፥ ንበሩም ታጱዋ ወደ ምዕራብ እስከ ቃና ወንዝ ድረስ አለፈ፥ መውጫውም በባሕሩ አጠገብ ነበረ። የኤፍሬም ልጆች ነገድ ርስት በየወገኖቻቸው ይህ ነበረ። (ኢያ 16:8)

3. የምናሴም ድንበር ከአሴር ጀምሮ በሴኬም ፊት ፊት እስካለው እስከ ሚክምታት ድረስ ነበረ ድንበሩም በቀኝ በኩል ወደ ዓይንታጱዋ ሰዎች አለፈ።” (ኢያ 17:7)

ቴላ ~ Telah: ጠል፣ ጥላ፣ ጠለል ርጥበት... ማለት ነው። የኤፍሬም ወገን፥ የኢያሱ ቅድመ አያት፥ ወንዶች ልጆቹም ፋፌ፥ ሬሴፍ፥ ልጁ ቴላ (1 ዜና 7:25)

ቴላሬሳ~Telharsa: የባቢሎናውያን ከተማ፥ ከቴልሜላ፥ ቴላሬሳ ከክሩብ፥ ከአዳን፥ ከኢሜር የወጡ እነዚህ ነበሩ ነገር ግን የአባቶቻቸውን ቤቶችና ዘራቸውን ... ያስታውቁ ዘንድ አልቻሉም (ዕዝ 2:59 ነህ 7:61)

ቴልሜላ ~ Tel-melah: የጨው ክምርማለት ነው። የባቢሎናውያን ከተማ፥ ቴልሜላ ከቴላሬሳ፥ ከክሩብ፥ ከአዳን፥ ከኢሜር የወጡ እነዚህ ነበሩ ነገር ግን የአባቶቻቸውን ቤቶችና ዘራቸውን ወይም ከእስራኤል ወገን መሆናቸውን ያስታውቁ ዘንድ አልቻሉም” (ዕዝ 2:59 ነህ 7:61)

ቴልአቢብ ~ Telabib: ክምር የአበባ ሐውልትማለት ነው። ሕዝቅኤል ባየው ራእይ የተጠቀሰ፥ የከተማ ስም፥ ቴልአቢብ ወዳሉ በኮቦርም ወንዝ አጠገብ ወደ ተቀመጡ ምርኮኞች መጣሁ፥ በተቀመጡበትም ቦታ ተቀመጥሁ በዚያም ሰባት ቀን በድንጋጤ በመካከላቸው ተቀመጥሁ።” (ሕዝ 3:15)

ቴማ ~ Tamah: ሳቂታ ማለት ነው። ከባቢሎን ምርኮ ከተመለሱ የቴማ ልጆች ይገኙበታል፥ የሲሣራ ልጆች፥ የቴማ ልጆች፥ የንስያ ልጆች፥ የሐጢፋ ልጆች።” (ዕዝ 2:54)

ቴማ ~ Thamah: ልጅ ማለት ነው። ከባቢሎን ምርኮ ከተመለሱ የቴማ ልጆች ይገኙበታል፥ የሲሣራ ልጆች፥ ቴማ ልጆች፥ የንስያ ልጆች፥ የሐጢፋ ልጆች።” (ዕዝ 2:54)

ቴማን ~ Tema, Teman: ደቡብማለት ነው። የእስማኤል ልጅ፥ ዱማ፥ ማሣ፥ ኩዳን፥ ቴማን ኢጡር፥ ናፌስ፥ ቄድማ” (ዘፍ 25:15 1 ዜና 1:30 ኢዮ 6:19 ኢሳ 21:14 ኤር 25:23)

      ቴማን / Teman: የደቡብማለት ነው።

1. የዔሳው ልጅ፣ የኤልፋዝ ልጅ፥ የኤልፋዝም ልጆች እነዚህ ናቸው ቴማን ኦማር፥ ስፎ፥ ጎቶም፥ ቄኔዝ” (ዘፍ 36:111541 1 ዜና 1:36)

2. ስለ ኤዶምያስ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በውኑ ቴማን ጥበብ የለምን? ከብልሃተኞችስ ምክር ጠፍቶአልን?” (ኤር 49:78 ሕዝ 25:13)

ቴስብያዊው ~ Tishbite: ሚይዝ ንዝ ማለት ነው። ነቢዩ ኤልያስ በዚህ ስም ተጠርቷል፥ በገለዓድ ቴስቢ የነበረው ቴስብያዊው ኤልያስ አክዓብን፦ በፊቱ የቆምሁት የእስራኤል አምላክ ሕያው እግዚአብሔርን! ከአፌ ቃል በቀር በእነዚህ ዓመታት ጠልና ዝናብ አይሆንም አለው (1 ነገ 17:1 21:1728)

ቴርጋማ ~ Togarmah: አጥንማለት ነው። የጋሜርም ልጅ፥የጋሜርም ልጆች አስከናዝ፥ ሪፋት፥ ቴርጋማ ናቸው( 10:3)

ቴቁሔ ~ Tekoa: እውጅማለት ነው።

1. በይሁዳ ነገድ የነበረ ከተማ፥ በይሁዳና በብንያም ያሉትንም የተመሸጉትን ከተሞች፥ ቤተ ልሔም፥ ኤጣምን፥ ቴቁሔን፥ (2 ዜና 11:6)

2. በይሁዳ የዘር ሐረግ የተጠቀሰ፥ የአሽሑር ልጅ፥ ኤስሮምም በካሌብ ኤፍራታ ከሞተ በኋላ የኤስሮም ሚስት አቢያ ቴቁሔን አባት አሽሑርን ወለደችለት።” (1 ዜና 2:24 4:5)

ቴቄል ~ Tekel: ተክል፣ ልክ፥ ለካ፣ መዘነ፣ መጠነ ክብደት... ማለት ነው።

የሰው እጅ ጣቶች ወጥተው በንጉሡ ቤት በተለሰነው ግንብ ላይ በመቅረዙ አንጻር ጻፉ ንጉሡ ብልጣሶር የሚጽፉትን ጣቶች አየ፥ የተጻፈውም ጽሕፈት፥ ቴቄል ማለት፥ በሚዛን ተመዘንህ፥ ቀልለህም ተገኘህ ማለት ነው” (ዳን 5:27)

ቴቄምናስ ~ Tahpenes: የፈርዖን ሚስት፥ የሚስቱንም የእቴጌይቱን ቴቄምናስ እኅት እስኪያጋባው ድረስ ሃዳድ በፈርዖን ፊት እጅግ ባለምዋል ሆነ።” (1 ነገ 11:1920)

ቴቤስ ~ Thebez: ግልጥ ዕውቅማለት ነው።

አቤሜሌክ የሞተበት ቦታ፥አቤሜሌክም ወደ ቴቤስ መጣ፥ ቴቤስንም ከብቦ ያዛት (መሣ 9:50)

ቴዎዳስ ~ Theudas: ተወዳሽ፣ ተመስጋኝ... ማለት ነው። እኔ ታላቅ ነኝ ብሎ የተነሣ፥ ገማልያ በኢየሩሳሌም ባደረገው ንግግር የጠቀሰው። ከዚህ ወራት አስቀድሞ ቴዎዳስ እኔ ታላቅ ነኝ ብሎ ተነሥቶ ነበርና፥ አራት መቶ የሚያ ሰዎችም ከእርሱ ጋር ተባበሩ፤ እርሱም ጠፋ የሰሙትም ሁሉ ተበተኑ እንደ ምናምንም ሆኑ” (ሐዋ 5:36)

ቴዎፍሎስ ~ Theophilus: የአምላክ ወዳጅ የጌታ ጓደኛማለት ነው። ሉቃስ ወንጌልን የጻፈለት ሮማዊ ክርስቲያን፥ የከበርህ ቴዎፍሎስ ሆይ፥ ከመጀመሪያው በዓይን ያዩትና የቃሉ አገልጋዮች የሆኑት እንዳስተላለፉልን፥ በኛ ዘንድ ስለ ተፈጸመው ነገር ብዙዎች ታሪክን በየተራው ለማዘጋጀት ስለ ሞከሩ፥ እኔ ደግሞ ስለ ተማርኸው ቃል እርግጡን እንድታውቅ በጥንቃቄ ሁሉን ከመጀመሪያው ተከትዬ በየተራው ልጽፍልህ መልካም ሆኖ ታየኝ።” (ሉቃ 1:3)

ትዕማር ~ Tamar: ትማር፣ ተማረ፣ ይቅር ተባለ፣ ምሕረት አገኘ... ማለት ነው (‘ታምር ተምር፣ የተምር ዛፍ ማለት ነው ተብሎም ተተርጉሟል)

[ተዛማጅ ስም- ታማር]

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-

1. የይሁዳም የበኵር ልጁ፣ የዔር ሚስት፥ (ዘፍ 38:8-30)

2. የዳዊት ልጅ፣ የአቤሴሎም እኅት፥ (2 ሳሙ13:1-32) (1 ዜና 3:9)

3. የአቤሴሎም ልጅ፥ (2 ሳሙ 14:27)

ትያጥሮን ~ Thyatira: ሽቶማለት ነው። (የሳቅ የጨዋታ ቤት፥ ብዙ ይነት የጥጋብ ጨዋታ፥ ምሳሌና ተረት፥ ምትሀትና ውሸትማለት ነው። ኪወክ /) በታናሽቱ እስያ የነበረ ከተማ፥ እንዲሁም። የምታየውን በመጽሐፍ ጽፈህ ወደ ኤፌሶንና ወደ ሰምርኔስ ወደ ጴርጋሞንም ወደ ትያጥሮን ወደ ሰርዴስም ወደ ፊልድልፍያም ... ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት ላክ አለኝ (ራእ 1:112:18-28)

ቶሑ ~ Tohu: የበታች ትሑት፣ ምስኪንማለት ነው። የነቢዩ ሳሙኤል ቅድመ አያት፥ በተራራማው በኤፍሬም አገር ከአርማቴም መሴፋ የሆነ ስሙ ሕልቃና የተባለ ... የኢያሬምኤል ልጅ የኢሊዮ ልጅ ቶሑ ልጅ የናሲብ ልጅ ነበረ። (1 ሳሙ 1:1)

ቶላ ~ Tola: ትል ማለት ነው።

1. የይሳኮር ልጅ፥ የይሳኮርም ልጆች ቶላ ፉዋ፥ ዮብ፥ ሺምሮን።” (ዘፍ 46:13)

2. የፎሖ ልጅ፥ ከአቤሜሌክም በኋላ ከይሳኮር ነገድ የሆነ የዱዲ ልጅ የፎሖ ልጅ ቶላ እስራኤልን ለማዳን ተነሣ በተራራማውም በኤፍሬም አገር ባለችው በሳምር ተቀምጦ ነበር።” (መሣ 10:12)

ቶላድ ~ Tolad: ትውልድ፣ ልጅ፣ ዘር... ማለት ነው። በይሁዳ ደቡብ፥ የስምዖን ከተማ፥ ቶላድ በቤቱኤል፥ በሔርማ፥ በጺቅላግ፥” (1 ዜና 4:30)

ቶማስ ~ Thomas: መንታ ማለት ነው። ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ፥ ፊልጶስም በርተሎሜዎስም፥ ቶማስ ቀራጩ ማቴዎስም፥ የእልፍዮስ ልጅ ያዕቆብም ታዴዎስም የተባለው ልብድዮስ፥ (ማቴ 10:3 ማር 3:18)

ቶቤል ~ Tubal: ምድርማለት ነው። የያፌት ልጅ፥ የያፌት ልጆች ጋሜር፥ ማጎግ፥ ማዴ፥ ያዋን፥ ይልሳ፥ ቶቤል ሞሳሕ፥ ቴራስ ናቸው። (ዘፍ 10:2)

ቶዑ ~ Toi: የሐማት ንጉሥ፥ የዳዊትን ድል ማድረግ ሲሰማ የወርቅ፣ የብርና ሐስ ስጦታን አስይዞ የላከ፥ የሐማትም ንጉሥ ቶዑ ዳዊት የአድርአዛርን ጭፍራ ሁሉ እንደ መታ ሰማ።” (2 ሳሙ 8:910)

ቶኬን ~ Tochen: የተመተረ፣ የተለካ ማለት ነው። የስምዖን ከተማ፥

መንደሮቻቸውም ኤጣም፥ ዓይን፥ ሬሞን፥ ቶኬን ... (1 ዜና 4:32)

ቶዋ ~ Toah: ጦር መሣሪያ ቀስት ማለት ነው። የዘማሪው የኤማን ቅድመ አያት፥ የሳሙኤል ልጅ፥ የሕልቃና ልጅ፥ ... የኤሊኤል ልጅ፥ ቶዋ ልጅ፥ (1 ዜና 6:34)

ቶፌት ~ Tophet: ጥፋት ማለት ነው። ለጣዖት አምልኮ ልጆቻቸውን ያቃጥሉበት የነበረ ቦታ፥ ...ወንዶችና ሴቶች ልጆቻቸውን በእሳት ያቃጥሉ ዘንድ በሄኖም ልጅ ሸለቆ ያለችውን ቶፌት መስገጃዎች ተዋል። (ኤር 7:31)


No comments:

Post a Comment

ማውጫ

    ሀ   ለ   ሐ   መ   ሠ   ረ   ሰ   ሸ   ቀ   በ   ተ   ቸ   ኀ   ነ   ኘ   አ   ከ   ኸ   ወ   ዐ   ዘ   ዠ   የ   ደ   ጀ   ገ   ጠ   ጨ   ጰ   ጸ   ፀ   ፈ   ፐ