ሀ ለ ሐ መ ሠ ረ ሰ ሸ ቀ በ ተ ቸ ኀ ነ ኘ አ ከ ኸ ወ ዐ ዘ ዠ የ ደ ጀ ገ ጠ ጨ ጰ ጸ ፀ ፈ ፐ
ረሐም ~
Raham:
‘ርኅሩኅ፣ አዛኝ፣ ወዳጅ’ ማለት ነው። ከካሌብ ወገኖች አንዱ፥ “ሽማዕም የዮርቅዓምን አባት ረሐምን ወለደ ...”
(1 ዜና 2:44)
ረቃት ~
Rakkath:
‘ርቃናት፣ ባዶዎች’
ማለት ነው። የቤተ መቅደስ አለቃ የነበረ፥ “ረቃት፥ ኬኔሬት፥ አዳማ፥ ራማ፥ አሶር፥” (ኢያ 19:36)
ረቡኒ ~ Rabboni: አባት
የሆነ፣ ታላቅ፣
መሪ፣ መምህር... ማለት
ነው። “ኢየሱስም፦ ማርያም አላት። እርስዋ ዘወር ብላ በዕብራይስጥ። ረቡኒ አለችው፤ ትርጓሜውም።
መምህር ሆይ
ማለት ነው።” (ዮሐ 30:18)
ረቢ ~ Rabbi: ረቢ፣ የሚራባ፣ የሚባዛ፣ የሚዋለድ፣ ትልቅ አባት፣ ታላቅ ሕዝብ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ረቢት፣ ረባት]
‘ረባ’
ከሚለው ቃል
የመጣ ስም ነው።
ከዮሐንስ ጋር
የነበሩ ሐዋርያት፥
ጌታን የጠሩበት
ስም፥ “እርሱም፦ ረቢ፥ ወዴት ትኖራለህ?
አሉት፤ ትርጓሜው
መምህር ሆይ
ማለት ነው።” (ዮሐ
1:38፣ 49)
ረቢት ~ Rabbith: ረብዓት፣
ረባ፣ ተራባ፣
ተባዛ፣ ተዋለደ... ማለት
ነው። [ተዛማጅ ስም- ረቢ፣ ረባት]
‘ረባ’
ከሚለው ቃል
የመጣ ስም ነው።
የቦታ ስም፥ “ወደ ረቢት፥ ወደ ቂሶን፥ ወደ አቤጽ፥” (ዮሐ 19:20)
ረባት ~
Rabbah:
ረብዓት፣ ረባ፣ ተራባ፣ ተባዛ፣ ተዋለደ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም-
ረቢ፣ ረቢት]
‘ረባ’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው።
በዚህ ስም የሚታወቁ ሁለት ቦታዎች አሉ።
1.
ሙሴ ለጋድ ነገድ ለጋድም ልጆች በየወገኖቻቸው ርስት አድርጎ የሰጣቸው የቦታ
ድንበር፥ (ኢያ 13:25)
2.
በይሁዳ ተራራ አቅራቢያ የሚገኝ ከተማ፥ (ኢያ 15:60)
ረአሶን ~ Rezin: ‘ጽኑ፣ ብርቱ፣ ጠንካራ’
ማለት ነው።
ከፋቁሔ ጋር የተባበረ የሶርያ ንጉሥ፥
“በዚያም ወራት እግዚአብሔር የሶርያን ንጉሥ ረአሶንንና የሮሜልዩን ልጅ ፋቁሔን በይሁዳ ላይ መስደድ ጀመረ።” (2 ነገ 15:37፥ 16:5-9፤ ኢሳ 7:1-8)
ረአብ ~ Rehob: ‘ስፋት፣ መስፋፋት’ ማለት ነው።
1.
የሱባ ንጉሥ
የአድርአዛር አባት፥
“ዳዊትም ደግሞ በኤፍራጥስ ወንዝ አጠገብ
የነበረውን ግዛት
መልሶ ለመያዝ
በሄደ ጊዜ
የረአብን ልጅ
የሱባን ንጉሥ
አድርአዛርን መታ።” (2 ሳሙ 8:3፣12)
2.
የቃል ኪዳኑን
ደብዳቤ ካተሙ፥
ከሌዋውያኑ ወገን የሆነ፥ የኤንሐዳድ ልጅ፥ “ፌልያ፥ ሐናን፥ ሚካ፥ ረአብ፥ ሐሸብያ፥” (ነህ 10:11)
3.
የሶርያ ከተማ፥
“የአሞንም ልጆች ወጥተው
በበሩ መግቢያ ፊት ለፊት ተሰለፉ የሱባና የረአብ ሶርያውያን፥ የጦብና የመዓካም ሰዎች ለብቻቸው በሰፊ ሜዳ
ላይ ነበሩ።” (2 ሳሙ
10:6፣8፤ መሣ 18:28)
4.
የአሴር ከተማ፥ “ከዚያም ወደ ዔብሮን፥ ወደ ረአብ፥ ወደ ሐሞን፥ ወደ ቃና እስከ ታላቁ ሲዶናም ደረሰ።” (ኢያ 19:28)
5.
ሌላ የአሴር ከተማ፥ “ዑማ፥ አፌቅ፥ ረአብ ደግሞ ነበሩ ሀያ ሁለት ከተሞችና
መንደሮቻቸው”
(ኢያ 19:30)
ረዓምያ ~
Raamiah:
‘ሕያው ነጎድጐድ’ ማለት ነው። ከምርኮ ከተመለሱ አለቆች አንዱ፥ “ከዘሩባቤል፥ ከኢያሱ፥ ከነህምያ፥ ከአዛርያስ፥ ከረዓምያ፥ ከነሐማኒ፥ ከመርዶክዮስ፥
... ከበዓና ጋር
መጡ።”
(ነህ 7:7)
ረዓብ ~ Rahab: ‘ትእቢት፣ ትምክህት’ ማለት
ነው። “የሚያውቁኝን ረዓብንና ባቢሎንን አስባቸዋለሁ እነሆ፥ ፍልስጥኤማውያን ጢሮስም የኢትዮጵያም ሕዝብ፥ እነዚህ በዚያ ተወለዱ።” (መዝ 87:4፥ 89:10፤ ኢሳ 51:9)
ረዓብያ ~
Rehabiah:
ረብዓ ያሕ፣ ረበ ያሕ፣ ጌታ ያበረከተው፣ አምላክ ያራባው፣ የተባዛ... ማለት ነው።
‘ረባ’
ከሚለው ቃል
የመጣ ስም ነው።
የአልዓዛር ልጅ፥ “የአልዓዛርም ልጆች አለቃ ረዓብያ ነበረ፤ አልዓዛርም ሌሎች ልጆች አልነበሩትም የረዓብያ ልጆች እጅግ ብዙ ነበሩ።” (1 ዜና 23:17)
ረዕላያ ~ Reelaiah: ‘የሕያው አገልጋይ’ ማለት ነው። ከባቢሎን ምርኮ ከተመለሱት፥ “ከዘሩባቤል፥ ከኢያሱ፥ ከነህምያ፥ ከሠራያ፥ ከረዕላያ፥ ከመርዶክዮስ፥ ከበላሳን፥ ከመሴፋር፥ ከበጉዋይ፥ ከሬሁም፥ ከበዓና ጋር መጡ።” (ዕዝ 2:2)
ረፋያ ~ Rapha, Rephaiah: ረፋያ፣ ረፈ ያሕ፣ ረፍተ ሕያው፣ ዘላለማዊ ዕረፍት፣ የአምላክ ሰላም... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ሪፋት፣ ራፋያ፣ ራፋይ]
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ረፋያ / Rapha: የሳዖል ወገን የሆነ የቢንዓ ልጅ፥ (1 ዜና 8:2፣ 37)፣ (1 ዜና 9:43)
ረፋያ / Rephaiah:
1.
የዘረሩባቤል ወገን፥
ረፋያ፥ (1 ዜና 3:21)
2.
ከስምዖን ልጆች አለቆች አንዱ፥ ረፋያ፥ (1 ዜና 4:42)
3.
የኢየሩሳሌም ግዛት እኵሌታ አለቃ የሆር ልጅ፥ ረፋያ፥ (ነህ 3:9)
4.
የቢንዓ ልጅ፥
ረፋያ፥ (1 ዜና 9:43)
5.
የቶላ ልጅ፥
ረፋያ፥ (1 ዜና 7:2)
ሩሃማ ~ Ruhamah: ‘መማር፣ ምሕረትን
ማግኘት’
ማለት ነው።
“ወንድሞቻችሁን፦ ዓሚ፥ እኅቶቻችሁንም። ሩሃማ በሉአቸው”
(ሆሴ 2:3)
ሩማ ~
Rumah:
ራመ፣ ቆመ፣ ተነሣ፣ ከፍ አለ... ማለት ነው። የኢየሩሳሌም ንጉሥ፣ የኢዮአቄም እናት፥ የፈዳያ ልጅ፥ “ኢዮአቄምም ...አሥራ አንድ ዓመት ነገሠ እናቱም ዘቢዳ ትባል ነበር እርስዋም የሩማ ሰው የፈዳያ ልጅ ነበረች።” (2 ነገ 23:36)
ሩት ~
Ruth:
ርቱዕ፣ ርትዕ፣ ርትዒት፣ ርትዑ፣ ርኡት፣ ቅን፣ እውነተኛ፣ አሸናፊ... ማለት ነው።
‘ረታ’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው።
የኑኃሚን ምራት፥
በጌታ የዘር
ሐረግ የተጠቀሰች፥
“እነርሱም ከሞዓባውያን ሴቶች
ሚስት አገቡ የአንዲቱ ስም ዖርፋ የሁለተኛይቱም ስም ሩት ነበረ። ...” (ሩት 1:4) ፣ (ማቴ 1:5)
ሩፎስ ~ Rufus: ‘ቀይ’
ማለት ነው።
የቀሬና ስምዖን
ልጅ፥ “አንድ መንገድ
አላፊም የአሌክስንድሮስና የሩፎስ አባት ስምዖን የተባለ የቀሬና ሰው ከገጠር ሲመጣ መስቀሉን
ይሸከም ዘንድ
አስገደዱት።”
(ማር 15:21)
ሪሞን ~
Remmon:
ፍራፍሬ የሞላበት፥ የስምዖን ነገድ ርስት የሆነ ከተማ፥ “ዓይን፥ ሪሞን፥ ዔቴር፥ አሻን አራት ከተሞችና መንደሮቻቸው” (ኢያ 19:7)
ሪሳ ~ Rissah: ሪሳ፣
ሬሳ፣ ሙት፣
አስከሬን፣ በድን... ማለት
ነው። እስራኤላውያን፣ የሰፈርበት፣ የቦታ ስም፥ “ከልብናም ተጕዘው በሪሳ ሰፈሩ” (ዘኁ
33:21፣ 22)
ሪባ ~ Reba: ረባ፣
ተዋለደ፣ አራት... ሆነ
ማለት ነው።
“...አምስቱም የምድያም ነገሥታት
ኤዊ፥ ሮቆም፥
ሱር፥ ሑር፥
ሪባ ነበሩ
የቢዖርንም ልጅ በለዓምን ደግሞ
በሰይፍ ገደሉት።” (ዘኊ
31:8፤ ኢያ 13:21)
ሪባይ ~ Ribai: ጠቃሚ፣
ለሐላፊነት የሚበቃ... ማለት
ነው። ‘አምላክን ተማፃኝ
ማለት ነው’ ተብሎም
ይተረጎማል። “ከጊብዓ የሪባይ ልጅ ኢታይ፥ ጲርዓቶናዊው
በናያስ፥ የገዓስ
ወንዝ ሰው” (2 ሳሙ
23:29፤ 1
ዜና 11:31)
ሪብላ ~ Riblah: ‘ለም፥ ዘርን
የሚቀበል፥ ፍሬ የሚሰጥ’ ማለት
ነው። በሰሜናዊ ፍልስጥኤም ፊተኛ፥ የነበረ የከተማ ስም፥ “በኢየሩሳሌምም እንዳይነግሥ ፈርዖን
ኒካዑ በሐማት
ምድር ባለችው
በሪብላ አሰረው
በምድሩም ላይ
መቶ መክሊት ብርና አንድ መክሊት ወርቅ ፈሰሴ ጣለበት” (2 ነገ 23:33፥ 25:6፣20፣ 21፤ ኤር
39:5፥ 52:10)
ሪትማ ~ Rithmah: ‘ጤና’
ማለት ነው።
እስራኤላውያን በምድረ
በዳ ካረፋባቸው
ቦታዎች፥ “ከሐጼሮትም ተጕዘው
በሪትማ ሰፈሩ።” (ዘኊ
33:18፣19)
ሪና ~ Rinnah: ‘ደስታ፣ ዘፈን’ ማለት
ነው። ከይሁዳ
ልጆች አንዱ፥
“የሺሞንም ልጆች አምኖን፥ ሪና፥ ቤንሐናን፥ ቲሎን ነበሩ። የይሽዒም ልጆች ዞሔትና ቢንዞሔት
ነበሩ።”
(1 ዜና 4:20)
ሪጽፋ ~ Rizpah: ‘ከሰል’ ማለት ነው። የንጉሥ ሳኦል
ቁባት፥ የኢዮሄል
ልጅ፥ “የሳኦልም ቁባት የኢዮሄል ልጅ ሪጽፋ ያደረገችውን ለዳዊት ነገሩት” (2 ሳሙ 21:8-11)
ሪፋት ~
Riphath:
ዕረፍት፣ ድኅነት፣ ምሕረት፣ ይቅርታ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ረፋያ፣ ራፉ፣ ራፋኤል፣ ራፋይ]
‘ረፍ’
ከሚለው ቃል
የመጣ ስም ነው።
የኖኅ ልጅ፥ የያፌት ልጅ፥ የጋሜር ልጅ፥ ሪፋት፥ (ዘፍ 10:3)
ራሔል ~
Rachel:
‘ቄብ’
ማለት ነው። የያዕቆብ ሚስት፥ (ዘፍ 29:6፣28)
“እርሱ። ደኅና
ነውን?
አላቸው። እርሱም፦
አዎን ደኅና
ነው አሁንም
ልጁ ራሔል ከበጎች ጋር መጣች አሉት።”
ራማ፣ ሬማት፣ አ ርማቴ ~ Ramah: ከፍተኛ ማለት ነው።
1.
ከብንያም ከተሞች
አንዱ፥ “ገባዖን፥ ራማ፥ ብኤሮት፥” (ኢያ 18:25)
2.
የሕልቃና እና
የሐና አገር፥ “ማልደው ተነሥተው በእግዚአብሔር ፊት ሰገዱ፥ ተመልሰውም ወደ አርማቴም ወደ ቤታቸው መጡ። ...” (1 ሳሙ 1:19፥ 2:11)
3.
ከንፍታሌም ምሽጎች
አንዱ፥ “ረቃት፥ ኬኔሬት፥ አዳማ፥ ራማ፥ አሶር፥” (ኢያ 19:36)
4.
ለአሴር ጉልህ
ድንበሮች አንዱ፥
“ድንበሩም ወደ ራማ፥ ወደ ተመሸገውም ከተማ ወደ ጢሮስ ዞረ ድንበሩም ወደ ሖሳ ዞረ መውጫውም በአክዚብ በኩል
ወደ ባሕሩ
ነበረ”
(ኢያ 19:29)
5.
“ንጉሡም ኢዮራም ከሶርያ ንጉሥ ከአዛሄል ጋር በተዋጋ ጊዜ ሶርያውያን በሬማት ያቈሰሉትን ቍስል ይታከም ዘንድ ወደ ኢይዝራኤል ተመለሰ። የአክዓብም
ልጅ ኢዮራም
ታምሞ ነበርና
የይሁዳ ንጉሥ
የኢዮራም ልጅ
አካዝያስ ሊያየው
ወደ ኢይዝራኤል
ወረደ።”
(2 ነገ 8:29)
6.
ከባቢሎን ምርኮ መልስ፥ የብንያም ወገኖች የሰፈሩበት፥
“በሐናንያ፥ በሐጾር፥ በራማ፥ በጊቴም፥ በሐዲድ፥” (ነህ 11:33)
ራማትሌሒ ~ Ramath-lehi: የመንጋጋ
ክምር ማለት
ነው። ሶምሶን
በአህያ መንጋጋ አንድ ሺህ ፍልስጥኤማውያንን የገደለበት፥ “መናገሩንም በፈጸመ ጊዜ መንጋጋውን
ከእጁ ጣለ
የዚያንም ስፍራ
ስም ራማትሌሒ ብሎ ጠራው።” (መሣ 15:15-17)
ራምያ ~ Ramiah: የሕያው
ተራራ፣ የጌታ
ከፍታ... ማለት ነው።
ከግዞት ከተመለሱ፥
እንግዳ ሚስቶችን
ካገቡ፥ “ከእስራኤልም ከፋሮስ
ልጆች፤ ራምያ፥
ይዝያ፥ መልክያ፥
ሚያሚን፥ አልዓዛር፥
መልክያ፥ በናያስ።” (ዕዝ
10:25)
ራሞት ~
Ramoth:
‘የተከበረ፣ ከፍተኛ’ ማለት ነው። በይሳኮር ነገድ፥ የሌዊ ከተማ፥ “በቤቴል ለነበሩ፥ በራሞት በደቡብ ለነበሩ” (1 ሳሙ 30:27፤ 1 ዜና 6:73)
ራስ ~ Rush: ራሽ፣
ራስ፣ የበላይ፣
ጭንቅላት... ማለት ነው።
የእስራኤልን አለቆች ለመግለጽ የተጠቀሰ ቃል፥ “ስለዚህ እግዚአብሔር ራስና
ራቆን ~
Rakkon:
‘ርቃን፣ ዕርቃን’ ማለት ነው። የነገደ ዳን ርስት የሆነ፥ ውኃ ገብ ቦታ፥
“ይሁድ፥ ብኔብረቅ፥ ጋትሪሞን፥
ሜያርቆን፥ በኢዮጴ
ፊት ለፊት
ካለው ዳርቻ
ጋር ራቆን።” (ኢያ 19:46)
ራብማግ ~
Rabmag:
‘ጀግና፣ አሸናፊ’ ማለት ነው። ከባቢሎን ንጉሥ ሹማምንት አንዱ፥ “የባቢሎንም ንጉሥ አለቆች ሁሉ፥ ኤርጌል ሳራስር፥ ሳምጋርናቦ፥ ሠርሰኪም፥ ራፌስ፥
ኤርጌል ሳራስር፥
ራብማግ፥ ከቀሩት
ከባቢሎን …።” (ኤር
39:3፣13)
ራዕማ~ Raamah: ‘ነጎድጓድ’
ማለት ነው።
የኩሽ ልጅ፥
“የኩሽም ልጆች ሳባ፥ ኤውላጥ፥ ሰብታ፥ ራዕማ፥ ሰበቃታ …
ናቸው” (ዘፍ 10:7)
ራኬብ ~ Rachab: ርካብ፣
መሰላል፣ መወጣጫ
ማለት ነው።
በጌታ የዘር
ሐረግ የተጠቀሰች፥
የቦኤዝ እናት፥
“ሰልሞንም ከራኬብ ቦኤዝን
ወለደ፤ ቦኤዝም
ከሩት ኢዮቤድን ወለደ፤ ኢዮቤድም እሴይን ወለደ” (ማቴ 1:5)
ራያ ~
Reaiah:
ራእይ ያሕ፣ የሕያው ራእይ ማለት ነው።
1.
የሦባል ልጅ፥ “የሦባልም ልጅ ራያ ኢኤትን ወለደ ኢኤትም አሑማይንና ላሃድን ወለደ። እነዚህ የጾርዓውያን ወገኖች ናቸው።” (1 ዜና 4:2)
2.
ከባቢሎን ምርኮ ከተመለሱ፥ የራያ ልጆች ይገኙበታል፥ “የጌዴል ልጆች፥ የጋሐር ልጆች፥ የራያ ልጆች፥” (ዕዝ 2:47፤ ነህ 7:50)
ራዳይ ~ Raddai: ረዲእ፣ ረዳ፣ ‘ረጅ፣ ረዳት፣ አጋዥ... ማለት ነው። የእሴይ ልጅ፥ የዳዊት ወንድም፥ “አምስተኛውንም ራዳይን፥ ስድስተኛውንም …”
(1 ዜና 2:14)
ራጉኤል ~
Raguel, Reuel: ረጋ ኤል፣ የአምላክ ዕረፍት፣ የጌታ ወዳጅ፣ ሰንበት... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም:- ራጋው]
‘ረጋ’ እና ‘ኤል’
ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ራጉኤል / Raguel: የሙሴ
አማት፥ ኢትዮጵያዊው ካህን፥ “ወደ አባታቸው ወደ ራጉኤልም በመጡ ጊዜ ...” (ዘጸ 2:18) ፣ (ዘኁ 10:29)
ራጉኤል / Reuel:
1.
የዔሳው ልጅ፣ ከቤሴሞት የወለደው፥ (ዘፍ 36:4፣ 10)
2.
የኤሊሳፍ አባት
ራጉኤል፥ (ዘኁ 2:14)
3.
የዪብንያ ልጅ፣ የሰፋጥያስ አባት ራጉኤል፥ (1 ዜና 9:8)
ራጉኤል ~
Deuel: ያምላክ ወዳጅ ማለት ነው። በሲና በረሓ ሲቆጠሩ፥ የጋድ ነገድ አለቃ፥ የኤሊሳፍ አባት፥ “ከጋድ የራጉኤል ልጅ ኤሊሳፍ” (ዘኊ 1:14፥ 7:42፣ 47፥ 10:20)
ራጋው ~
Ragau:
ረጋ፣ መርጋት፣ ማረፍ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም:- ራጉኤል]
Ragau-
‘ረጋ’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው።
በጌታ የዘር ሐረግ የተጠቀሰ፣ የሴሮህ ልጅ፥ (ሉቃ 3:35)
ራግው ~
Reu:
‘ረጋ፣ ወዳጅ’ ማለት ነው። በአብርሃም የዘር ሐረግ፥ የፋሌቅ ልጅ፥ “ፋሌቅም መቶ ሠላሳ ዓመት ኖረ፥ ራግውንም ወለደ”
(ዘፍ 11:18፤ 1
ዜና 1:25)
ራፉ ~ Raphu: ረፍ፣ ዐረፈ፣ ማረፍ፣ ዕረፍት፣ ማቆም፣ አለመሥራት... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ሪፋት፣ ረፋያ፣ ራፋኤል፣ ራፋይ]
‘ረፍ’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው።
የእስራኤል ልጆች
የከነዓንን ምድር
ይሰልሉ ዘንድ፥
ሙሴ እንደ
እግዚአብሔር ትእዛዝ ከፋራን ምድረ በዳ ከላካቸው፥ ከብንያም ነገድ የፈልጢ አባት፥ (ዘኁ 13:9)
ራፊስ ~ Rezeph: ‘ዐለት፣ ትኩስ ድንጋይ’
ማለት ነው።
የቦታ ስም፥
“አባቶቼ ያጠፉአቸውን፥ ጎዛንን፥
ካራንን፥ ራፊስን፥
በተላሳር የነበሩትንም
የዔድንን ልጆች፥
የአሕዛብ አማልክት
አዳኑአቸውን?”
(2 ነገ 19:12፤ ኢሳ 37:12)
ራፊዲም ~ Rephidim: ‘ረፈ ደም፣ የአካል ማረፊያ፣ መተኛ፣ አልጋ’
ማለት ነው።
እስራኤላውያን ከግብፅ
ምድር ወጥተው
ወደ ሲና
እስኪደርሱ ካረፉባቸው፥
“የእስራኤልም ልጆች ማኅበር ሁሉ እግዚአብሔር እንዳዘዘ ከሲን ምድረ በዳ ሊጓዙ ተነሡ፥ በራፊዲምም ሰፈሩ ...” (ዘጸ 17:1፣ 8፥ 19:2)
ራፋቃ ~ Dophkah: ‘ደፈቃ፣ ረፈቀ፣ ረፈቃ፣ ማረፍ፣ መቀመጥ’ ማለት ነው። በቁጥር መጽሐፍ የተጠቀሰ፥ “ከሲን ምድረ በዳም ተጕዘው በራፋቃ ሰፈሩ።” (ዘኊ 33:12)
ራፋኤል ~ Rephael: ረፈ ኤል፣ የአምላክ ዕረፍት፣ ሰንበት... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ሪፋት፣ ረፋያ፣ ራፉ፣ ራፋኤል፣ ራፋይ]
‘ረፍ’ እና ‘ኤል’
ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
የሸማያ ልጅ፥ “ለሸማያ ልጆች ዖትኒ፥ ራፋኤል፥ ዖቤድ...” (1 ዜና 26:7፣ 8)
ራኬብ ~ Rachab:
ርካብ፣ መሰላል፣ ደረጃ፣ መወጣጫ፣ መንኮራኩር... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ሬካብ]
በጌታ የዘር ሐረግ የተጠቀሰ፥ የሰልሞን ራኬብ፥ (ማቴ 1:5)
ራፋያ ~ Rephaiah: ... [ረፋያ / Rapha, Rephaiah- ይመልከቱ] ፥ [ተዛማጅ ስሞች-ሪፋት፣ ረፋያ፣ ራፋኤል፣ ራፋይ]
የቶላ ልጅ፥ “የቶላም ልጆች፥ ኦዚ፥ ራፋያ ፥ ይሪኤል ...” (1 ዜና 7:2)
ራፋይ ~ Rapha: ... [ረፋያ / Rapha, Rephaiah- የሚለውን ይመልከቱ።]፥ [ተዛማጅ ስሞች-
ሪፋት፣ ረፋያ፣ ራፋኤል፣ ራፋይ]
“ከዚህም በኋላ በጌዝር ላይ ከፍልስጥኤማውያን ጋር ሰልፍ ሆነ ኩሳታዊውም ሴቦካይ
ከራፋይም ወገን
የነበረውን ሲፋይን
ገደለ።”
(1 ዜና 20:4)
ሬሁም ~ Rehum: ‘መሓሪ፣ ይቅር
ባይ’
ማለት ነው።
1.
ከምርኮ ከተመለሱ፥ “ከዘሩባቤል፥ ከኢያሱ፥ ከነህምያ፥ ከሠራያ፥ ከረዕላያ፥
ከመርዶክዮስ፥ ከበላሳን፥
ከመሴፋር፥ ከበጉዋይ፥
ከሬሁም፥ ከበዓና
ጋር መጡ።” (ዕዝ 2:2)
2.
የንጉሡ የአርጤክስስ
አዛዥ፥ “አዛዡ ሬሁም ጸሐፊውም ሲምሳይ በኢየሩሳሌም ላይ ለንጉሡ ለአርጤክስስ እንዲህ የሚል ደብዳቤ ጻፉ።”
(ዕዝ 4:8-24)
3.
ሌዋዊው፥ “ከእርሱም በኋላ ሌዋውያንና የባኒ ልጅ ሬሁም አደሱ። በአጠገባቸውም
የቅዒላ ግዛት...
” (ነህ 3:17)
4.
ከባቢሎን ምርኮ ከተመለሱ፥ “አሎኤስ፥ ፈልሃ፥ ሶቤቅ፥ ሬሁም፥ ሐሰብና፥” (ነህ 10:25)
5.
ከባቢሎን ምርኮ
ከተመለሱ፥ “መሉክ፥ ሐጡስ፥ ሴኬንያ፥ ሬሁም፥
ሜሪሞት፥”
(ነህ 12:3)
ሬሕማ ~ Reumah: ‘ራማ፣ ከፍታ’ ማለት
ነው። የአብርሃም
ወንድም፣ የናኮር
ቁባት፥ “ሬሕማ የሚሉአት
ቁባቱ ደግሞ ጥባህን፥
ገአምን፥ ...” (ዘፍ 22: 24)
ሬምፉም ~ Remphan: ‘ዝግጁ’
ማለት ነው።
እስራኤላውያን ካመለኳቸው
ጣዖታት አንዱ፥
“ትሰግዱላቸውም ዘንድ የሠራችኋቸውን
ምስሎች እነርሱንም የሞሎክን ድንኳንና ሬምፉም የሚሉትን የአምላካችሁን ኮከብ አነሣችሁ፤ እኔም
ከባቢሎን ወዲያ
እሰዳችኋለሁ ተብሎ
እንዲህ ተጽፎአል።” (ሐዋ
7:43)
ሬሞን~ Rimmon: ‘ከፍተኛ’
ማለት ነው።
1.
የዛብሎን ከተማ፥
“ከሌዋውያን ለቀሩት ለሜራሪ ልጆች ከዛብሎን ነገድ ሬሞንና መሰምርያዋ፥ ...” (1 ዜና 6:77፤ ነህ 11:29)
2.
በይሁዳ የታችኛው
ክፍል የሚገኝ ቦታ፥ “መንደሮቻቸውም ኤጣም፥ ዓይን፥ ሬሞን፥ ቶኬን፥ ዓሻን፥ አምስቱ ከተሞች” (1 ዜና 4:32)
3.
እስራኤላውያን በምድረ
በዳ ካረፉባቸው ቦታዎች፥ “ከሪትማም ተጕዘው በሬሞን
ዘፋሬስ ሰፈሩ።” (ዘኊ 33:19፣20)
4.
“ስድስቱም መቶ ሰዎች ተመልሰው ወደ ምድረ በዳ ወደ ሬሞን ዓለት ሸሹ፥ በሬሞን ዓለት አራት ወር ተቀመጡ።” (መሣ 20:45፣47፥21:13)
5.
ከብንያም ልጆች ብኤሮታዊው፥ የሬካብ አባት፥ “ለሳኦልም ... የብኤሮታዊው የሬሞን ልጆች ነበሩ ብኤሮትም ለብንያም ተቈጥራ ነበር”
(2 ሳሙ 4:2፣5፣9)
ሬሲ ~
Rei:
‘ወዳጅ’ ማለት ነው። አዶንያስ በዳዊት ላይ ባመጸ ጊዜ፥ ከዳዊት ጋር
ጸንተው ከቆዩት፥
“ነገር ግን ካህኑ
ሳዶቅና የዮዳሄ
ልጅ በናያስ
ነቢዩም ናታን
ሳሚም ሬሲም የዳዊትም ኃያላን ከአዶንያስ ጋር አልነበሩም።” (1 ነገ 1:8)
ሬሴን ~ Resen: ራስ፣ የላይ፣ የወንዝ መነሻ፣ ምንጭ... ማለት ነው። ናምሩድ ከገነባቸው ከተሞች፥ “በነነዌና በካለህ መካከልም ሬሴንን ሠራ እርስዋም ... ከተማ ናት።”
(ዘፍ 10:12)
ሬስ ~ Rhesa: ሪስ፣ ራስ፣ ራሴ፣ እንደራሴ፣ እኔ፣ እንደኔ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም:- ሮስ]
በጌታ የዘር
ሐረግ የተጠቀሰ፣
የዘሩባቤል ልጅ፥
(ሉቃ 3:27)
ሬካብ ~
Rechab:
ርካብ፣ መወጣጫ፣ መሰላል... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ራኬብ]
‘ርካብ’ ማለት እንደ የበቅሎ ፥ የፈረስ መወጣጫ ማለት ነው። በመጽሐፍ
ቅዱስ ውስጥ
በዚህ ስም
የሚታወቁ ሰዎች:- 1.የኢዮናዳብን አባት፥ (2 ነገ 10:15፣ 23፣ ኤር 35:6-19)
2.የኢያቡስቴ ከጭፍራ አለቆች አንዱ፥ (2 ሳሙ 4:2)
ሬካብ ~ Rechab: ርካብ፣ መሰላል፣ ሰረገላ... ማለት ነው።
1.
የሳኦልም ልጅ፣ ኢያቡስቴ ልጅ፥ ከጭፍራ አለቆች አንዱ፥ “ለሳኦልም ልጅ ለኢያቡስቴ የጭፍራ አለቆች የሆኑ ሁለት ሰዎች ነበሩት የአንዱም ስም በዓና፥ የሁለተኛውም ስም ሬካብ ነበረ፥ ...” (2 ሳሙ 4:2)
2.
የኢዮናዳብ አባት፥ “ከዚያም በሄደ ጊዜ የሬካብን ልጅ ኢዮናዳብን ተገናኘው ደኅንነቱንም ጠይቆ፤ ልቤ ከልብህ ጋር እንደ ሆነ ያህል ልብህ ከልቤ
ጋር በቅንነት
ነውን?
አለው።”
(2 ነገ 10:15፣ 23፤ ኤር
35:6-19)
ሬዞን ~ Rezon: ‘ልዑል፣ አለቃ፣ ትልቅ፣ የበላይ፣ መሪ’
ማለት ነው።
የሶርያዊው፥ የኤልያዳ
ልጅ፥ “እግዚአብሔርም ... ሬዞንን ጠላት አድርጎ አስነሣበት።” (1 ነገ 11:23)
ሬጊዩም ~ Rhegium: ‘ክፍተት’
ማለት ነው።
ሐዋርያው ጳውሎስ
ከጎበኛቸው፥ በደቡባዊ ጣልያን የነበረ ከተማ፥ “ከዚያም እየተዛወርን ወደ ሬጊዩም ደረስን። ከአንድ ቀን በኋላም የደቡብ ነፋስ ... ፑቲዮሉስ መጣን።”
ሬጌሜሌክ ~
Regem-melech:
ረጅ መላክ፣ ተራዳይ፣ አጋዥ፣ የንጉሥ ተጠሪ፣ ረዳት መልእክተኛ... ማለት ነው።
‘ረጅ’ እና ‘መላክ’
ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ነው። ነቢዩ ዘካርያስ ወደ እግዚአብሔር ከላካቸው፥ (ዘካ 7:2)
ሬጌም~ Regem: ረጅ፥
ረዳት፣ አጋዥ፣ ጓደኛ... ማለት
ነው። የያሕዳይ
ልጅ፥ “ሐራንም ጋዜዝን ወለደ። የያሕዳይም ልጆች ሬጌም፥ ኢዮታም፥ ጌሻን፥ ፋሌጥ፥ ሔፋ፥
ሸዓፍ ነበሩ።” (1 ዜና 2:47)
ርኆቦት፣ ረሆቦት~ Rehoboth: ርባታ፣ መራባት፣ መባዛት፣ መስፋፋት... ማለት ነው።
1.
ይስሐቅ ከቆፈራቸው
የውኃ ጉድጓዶች ሦስተኛው፥ “...ስለ እርስዋም አልተጣሉም፤ ስምዋንም ርኆቦት ብሎ ጠራት፤ እንዲህ ሲል፦
አሁን እግዚአብሔር
አሰፋልን፥
በምድርም እንበዛለን” (ዘፍ 26:22)
2.
አሴር የገነባት ከተማ፥ “አሦርም ከዚያች አገር ወጣ ነነዌን፥ የረሆቦትን ከተማ፥ ካለህን፥”
(ዘፍ 10:11)
3.
ሳኦል የተባለ
የኤዶማውያን ሰው
የነገሠበት ከተማ፥ ... በወንዝ አጠገብ ካለችው ከርኆቦት ሳኦል ነገሠ።” (ዘፍ 36:37፤ 1
ዜና 1:48)
ርብቃ ~ Rebekah: ‘ወጥመድ፣ ሸምቀቅ፣ ማነቆ’ ማለት ነው። የባቱኤል
ልጅ፥ የይስሐቅ ሚስት፥ “ባቱኤልም ርብቃን ወለደ እነዚህን ስምንቱን ሚልካ ለአብርሃም ወንድም
ለናኮር ወለደች።” (ዘፍ
22:23፥ 24:67)
ሮማንቲዔዘር ~ Romamti-ezer: ‘ታላቅ ወገን፣
ከፍተኛ ረዳት’ ማለት
ነው። የኤማን
ልጅ፥ “ከኤማን የኤማን
ልጆች ቡቅያ፥
መታንያ፥ ዓዛርዔል፥
ሱባኤ፥ ኢያሪሙት፥ ሐናንያ፥ ሐናኒ፥ ኤልያታ፥ ጊዶልቲ፥ ሮማንቲዔዘር፥ ዮሽብቃሻ፥ መሎቲ፥
ሆቲር፥ መሐዝዮት” (1 ዜና 25:4፣31)
ሮሜ ~ Rome: ‘ኃይል፣ ብርታት’ ማለት
ነው። ጌታ
በተወለደበት ዘመን
የነበረ፥ የዓለም ዋና ከተማ፥ “በፍርግያም ... በሊቢያ ወረዳዎች የምንኖር፥ በሮሜም የምንቀመጥ፥
አይሁድም ወደ
ይሁዲነትም የገባን፥” (ሐዋ 2:10)
ሮሜልዩ ~ Remaliah:
‘ረማ ለያሕ፣ አምላክ
የጠበቀው፥ ሕያው
የተንከባከበው’
ማለት ነው።
የፋቁሔ አባት፥
“የሠራዊቱም አለቃ የሮሜልዩ ልጅ ፋቁሔ ተማማለበት፥ ... በእርሱም ፋንታ ነገሠ።” (2 ነገ 15:25-37፥ 16:1፣5)
ሮስ ~
Rosh:
ራስ፣ የበላይ አካል፣ አለቃ፣ ዋነኛ... ማለት ነው። (ወንድ ልጅ፥ ማለት
ነው ።
ተብሎም ይተረጎማል።
ኪወክ / አ)
[ተዛማጅ ስም:-
ሬስ]
‘ራስ’
ከሚለው ቃል
የመጣ ስም ነው።
በግብፅ የተወለደ ከብንያም ወገን የሆነ፣ የቤላ ልጅ፥ (ዘፍ 46:21)
ሮቆም፣ ሬቄም ~ Rekem: ‘የገነነ፣ ያሸበረቀ፣ የተንቆጠቆጠ’ ማለት ነው።
1.
እስራኤላውያን ካጠፏቸው፥
የምድያም ነገሥታ፣ “ከተገደሉትም ጋር የምድያምን ... ነገሥታት ኤዊ፥ ሮቆም፥ ሱር፥ ሑር፥ ሪባ ነበሩ ...” (ዘኊ 31:8)
2.
የኬብሮን ልጅ፥ “የኬብሮንም ልጆች ቆሬ፥ ተፉዋ፥ ሬቄም፥ ሽማዕ
ነበሩ።”
(1 ዜና 2:43፣44)
3.
የብንያም ከተማ፥ “ሬቄም፥ ይርጵኤል፥ ተርአላ፥ ጼላ፥ ኤሌፍ፥ ኢየሩሳሌም
የምትባል የኢያቡስ
ከተማ፥ ...የብንያም
ልጆች ርስት
በየወገኖቻቸው ይህ
ነበረ።”
(ኢያ 18:27)
ሮቤል ~ Reuben: ረባን፣
ወለድን፣ ልጅ
አገኘን፤ ረበ
ኤል፣ አምላክ
ያበረከተው... ማለት ነው። “ልያም ፀነሰች፥ ወንድ ልጅንም ወለደች፥ ስሙንም ሮቤል ብላ
ጠራችው፤ እግዚአብሔር መከራዬን
አይቶአልና፥ እንግዲህም
ወዲህ ባሌ
ይወድደኛል ብላለችና።” (ዘፍ 29:32)
ሮብዓም ~ Rehoboam: ረቢ፣ ተራቢ፣ ተባዢ፣ ሰፊ ሕዝብ... ማለት
ነው። የይሁዳ
ንጉሥ፥ የንጉሥ ሰሎሞን ልጅ፥ “የሰሎሞንም ልጅ ሮብዓም በይሁዳ ነገሠ፤ ሮብዓምም ንጉሥ በሆነ ጊዜ የአርባ አንድ ዓመት ጉልማሳ ነበረ እግዚአብሔርም ስሙን የእናቱም ስም ናዕማ
ነበረ እርስዋም
አሞናዊት ነበረች።” (1 ነገ 14:21፣31)
ሮኦጋ ~
Rohgah:
‘ጥሪ፣ አቤቱታ’ ማለት ነው። የአሴር ወገን፥ የሳሜር ልጅ፥ “የሳሜርም ልጆች አኪ፥ ሮኦጋ፥ ይሑባ፥ አራም ነበሩ።” (1 ዜና 7:34)
ሮዴ ~ Rhoda:
ሮዳ፣ ሬዳ፣ ጽጌሬዳ፣ አበባ... ማለት ነው።
ጴጥሮስ ከእስር ወጥቶ ወደ ማርቆስ እናት ቤት፣ በሄደ ጊዜ በር የከፈተችለት ገረድ፥
(ሥራ 12:12-15)
ሮግሊም ~ Rogelim: ‘እግር፣ እግረኛ’ ማለት
ነው። የገላያድ
ከተማ፥ “ዳዊትም ወደ መሃናይም ... የዓሚኤል ልጅ ማኪር፥ የሮግሊምም ሰው ገለዓዳዊ ቤርዜሊ፥” (2 ሳሙ
17:27፥ 19:31)
No comments:
Post a Comment