ሀ ለ ሐ መ ሠ ረ ሰ ሸ ቀ በ ተ ቸ ኀ ነ ኘ አ ከ ኸ ወ ዐ ዘ ዠ የ ደ ጀ ገ ጠ ጨ ጰ ጸ ፀ ፈ ፐ
የሕማይ ~ Jahmai: ‘ሕያው ያየው፣ አምላክ የጠበቀው’ ማለት
ነው። የይሳኮር
ሰው፥ በቶላ
ቤት አለቃ
የነበረ፥ “የቶላም ልጆች፥
ኦዚ፥ ራፋያ፥
ይሪኤል፥ የሕማይ፥
ይብሣም፥ ሽሙኤል፥ የአባታቸው የቶላ ቤት አለቆች፥ በትውልዳቸው” (1 ዜና 7:2)
የሕዚኤል ~ Jahaziel: ያሕዘ
ኤል፣ አምላክ
ያዘ፣ በአምላክ
እጅ ያለ... ማለት
ነው።
‘ያዘ’ እና ‘ኤል’
ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1. የኬብሮን ሦስተኛ ልጅ፥ የሕዚኤል፥ (1 ዜና 23፡19)
2. በጺቅላግ ከቂስ ልጅ ከሳኦል በተሸሸገ ጊዜ ወደ ዳዊት ከመጡ፥ የሕዚኤል፥
(1 ዜና 12:4)
3. በዳዊት ዘመን የነበረ ካህን፥ የሕዚኤል፥ (1 ዜና 16:6)
4. የዘካሪያስ ልጅ፥ የሕዚኤል፥
(2 ዜና 20:14-17)
5. በዕዝራ ዘመን ከተመለሱት፣ አባት፥ የሕዚኤል፥ (ዕዝ 8:5)
የሕዜራ ~
Jahzerah:
ያሕ ዘራ፣ የሕያው ዘር፣ የአምላክ ወገን... ማለት ነው።
‘ያሕ’
(ያሕዌ ፣
ሕያው)
እና ‘ዘር’
ከሚሉ ሁለት
ቃላት የተመሠረተ
ስም ነው።
ይሁዳ ስለ ኃጢአታቸው ወደ ባቢሎን ሲማረኩ፣ ከይሁዳ ልጆችና ከብንያም ልጆች ከኤፍሬምና
ከምናሴ ልጆች
በኢየሩሳሌም የቀመጡ።
የሜሱላም ልጅ፥
የዓዲኤል አባት፥
(1 ዜና 9፡12)
የሕዝያ ~ Jahaziah:
‘በሕያው የተያዘ፣ አምላክ
ያየው’
ማለት ነው።
“ነገር ግን የአሣሄል ልጅ ዮናታንና የቴቁዋ ልጅ የሕዝያ ይህን ነገር ተቃወሙ፤ ሜሱላምና
ሌዋዊውም ሳባታይ
ረዱአቸው።”
(ዕዝ 10:15)
የማአት ~
Ahimoth:
አሂሞት፣ አያ ሞት፣ አያሞቴ፣ እስከሞት የሚጸና ወንድም፣
ብርቱ ወዳጅ፣
ሐቀኛ... ማለት ነው።
[ተዛማጅ ስም-
አኪሞት]
Ahimoth- ‘አያ’ እና
‘ሞት’ ከሚሉ ሁለት ቃላት
የተመሠረተ ስም
ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
. በጌታ የዘር ሐረግ የተጠቀሰ፣ የማታትዩ ልጅ፥ (ሉቃ 3:26)
. “ከሕልቃናም
ልጆች አማሢ፥
አኪሞት”
(1 ዜና 6፡25)
የምሌክ ~ Jamlech:
የአምላክ፣ የእግዚአብሔር፣ የጌታ፣ የፈጣሪ... ማለት ነው።
‘መለከ’
ከሚለው ግስ
የመጣ ስም ነው።
በስማቸው ከተጠሩ በወገኖቻቸው ላይ አለቆች ከነበሩ፥ (1
ዜና 4:34)
የሰናዖር ካባ ~ Babylonish garment: በባቢሎናውያን የተሠራ ልብስ፣ ዋጋው ውድ የሆነ፣ የባቢሎን ግምጃ። “በዘረፋ መካከል አንድ ያማረ የሰናዖር ካባ፥ ሁለት መቶም ሰቅል ብር፥ ሚዛኑም አምሳ ሰቅል የሆነ ወርቅ ...” (ኢያ 7:21)
የሱዊ ~
Isui:
‘እሽ፣ ዝም፣ ጸጥ’
ማለት ነው። የአሴር ሦስተኛ ልጅ፥
“የአሴርም ልጆች ዪምና፥ የሱዋ፥ የሱዊ፥ በሪዓ፥ እኅታቸው ሤራሕ የበሪዓ ልጆችም ሔቤር፥
መልኪኤል።”
(ዘፍ 46:17)
የሱዋ ~
Ishuai:
‘እሽታ፣ ጸጥታ፣ ዝምታ’ ማለት ነው።
‘እሽ’ ከሚለው ድምፅ የተገኘ ስም ነው።
የአሴር ልጅ፥ (1 ዜና 7፡30)
፣ (ዘፍ 46:17)
የሱዋ ~ Jesui: ‘ታጋሽ’
ማለት ነው።
የአሴር ልጅ፥
“የአሴር ልጆች በየወገናቸው ከዪምና የዪምናውያን ወገን፥ ከየሱዋ የየሱዋውያን ወገን፥ ከበሪዓ የበሪዓውያን
ወገን።”
(ዘኊ 26:44)
የሴሞ ~ Jeshimon: ‘ብቸኛ፣ ገለልተኛ፣
ዘዋራ፣ ሰዋራ
ስፍራ’
ማለት ነው።
በሙት ባሕር
በስተደቡብ ያለ
የተተወ ቦታ፥
“እነዚያም ተነሥተው ከሳኦል
በፊት ወደዚፍ ሄዱ ዳዊትና ሰዎቹ ግን በየሴሞን ደቡብ በኩል በዓረባ በማዖን ምድረ በዳ
ነበሩ።”
(1 ሳሙ 23:19፣24)
የስለታም ሰይፍ እርሻ ~ Helkath-hazzurim: የጦርነት አውድማ... ማለት ነው። የዳዊት ሠራዊት ከሳኦል ሠራዊት ጋር ፍልሚያ ያደረገበት ቦታ፥ “ሁሉም እያንዳንዱ የወደረኛውን ራስ ያዘ፥ ሰይፉንም በወደረኛው ጎን ሻጠ፥ ተያይዘውም ወደቁ። የዚያም ስፍራ ስም የስለታም ሰይፍ እርሻ ተብሎ ተጠራ፥ እርሱም በገባዖን ነው።” (2 ሳሙ 2:16)
የስቦቅ ~
Ishbak:
‘የሽ በቅ፣ መሄድ’ ማለት ነው። አብርሃም ከኬጡራ ከወለዳቸው ልጆች
አንዱ፥ “እርስዋም ዘምራንን፥
ዮቅሳንን፥ ሜዳንን፥
ምድያምን፥ የስቦቅን፥
ስዌሕን ወለደችለት።” (ዘፍ 25:2)
የሪያ ~ Irijah: ‘የሕያው ብርሃን፣ አምላክ ያየው’ ማለት
ነው። የሰሌምያ
ልጅ፥ “... የሐናንያ
ልጅ የሰሌምያ
ልጅ የሪያ የተባለ የዘበኞች አለቃ
በዚያ ነበረ። እርሱም፦
ወደ ከለዳውያን መኰብለልህ ነው ብሎ ነቢዩን ኤርምያስን ያዘው።” (ኤር 37:13፣14)
የርሙት ~ Jarmuth: ‘የራማት፣ ከፍተኛ’ ማለት ነው።
1.
በይሁዳ መስክ ያለ ከተማ፥ “ዓይንገኒም፥ ታጱዋ፥ ዓይናም፥ የርሙት” (ኢያ 15:35)
2.
“የርሙትንና መሰምርያዋን፥ ዓይንጋኒምንና መሰምርያዋን አራቱን ከተሞች
ሰጡአቸው።”
(ኢያ 21:29)
የሼብአብ ~ Jeshebeab
የሺ አብ፣ የብዙዎች አባት...
ማለት ነው።
የአራተኛው የካህናት ምድብ አለቃ፥ “አሥራ ሦስተኛው
ለኦፓ፥ አሥራ
አራተኛው ለየሼብአብ፥” (1 ዜና 24:13).
የሻያ ~
Jesaiah, Jeshaiah: የሺህ ያሕ፣ የሽዎች ጌታ፣ የብዙኃን አምላክ... ማለት ነው።
‘የሺህ’ እና ‘ያሕ’(ያሕዌ ፣ ሕያው) ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
የሻያ / Jesaiah:
የሐናንያ ልጅ፥ (1
ዜና 3፡21)
የሻያ / Jeshaiah:
1.
የኤዶታ ልጅ፥
(1 ዜና 25:3)
2.
የአልዓዛር ልጅ፥
(1 ዜና 26:25)
3.
የጎቶልያ ልጅ፥
(ዕዝ 8:7)
4.
ከሜራሪ ልጆች
ወገን፥ (ዕዝ 8:19)
5.
የብንያም ልጅ፥
(ነህ 11:7)
የቃምያ ~
Jekamiah:
ያቆም ያሕ፣ ሕያው ቋሚ፣ ለጌታ የቆመ፣ በአምላክ የጸና፣ ሕዝበ እግዚአብሔር... ማለት ነው።
‘ቆመ’
እና ‘ያሕ’ (ያሕዌ) ከሚሉ
ሁለት ቃላት
የተመሠረተ ስም
ነው። የሰሎም
ልጅ፥ (1 ዜና 2፡41)
የበራክዩ ~ Jeberechiah:
‘ይባረክ ያሕ፣ ሕያው የባረከው፣ እግዚአብሔር የባረከው’
ማለት ነው። በአካዝ ዘመን የነበረ፣ ዘካርያስ የተባለ ሰው አባት፥ (ኢሳ 8:2)
የብኒኤል ~
Jabneel:
ያብነ ኤል፣ የጌታ መሠረት፣ የእግዚአብሔር ሥራ... ማለት ነው። (በአምላክ የታነጸ ተብሎም ይተረጎማል።)
‘ያብ’ እና ‘ኤል’
ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
. የይሁዳ ልጆች ነገድ ዕጣ ድንበር፥ (ኢያ 15:11)
. (ኢያ 19:33)
የብና ~
Jabneh:
የአብነህ፣ የአምላክ፣ የእግዚአብሔር ሥራ... ማለት ነው። ሕንጻ ማለት ነው ተብሎ ይተረጎማል። [ተዛማጅ ስም-
የብኒኤል]
‘የአብ’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው። የይሁዳ ንጉሥ ዖዝያን ከያዛቸው ከተሞች፥ (2 ዜና 26፡6)
የተረገመ ~
Anathema:
‘ለቅጣት የተለየ’ ማለት ነው። “ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን የማይወድ ቢኖር የተረገመ ይሁን። ጌታችን ሆይ፥ ና።” (1 ቆሮ 12:3፥
16:22፤ ገላ1:9)
የቲር ~
Jattir:
የተከበረ፣ ክቡር፣ ግርማዊ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ዮቶር]
ለካህኑ ለአሮን ልጆች ከተሰጡ የመማፀኛ ከተሞች፥ “በተራራማውም አገር ሳምር፥ የቲር” (ኢያ 15፡48)
የቴት ~ Jetheth: ‘ምጽዋት፣ መስጠት’ ማለት
ነው። ከኤዶም
አለቆች፥ “የዔሳውም የአለቆቹ ስም በወገናቸው በስፍራቸው በስማቸውም ይህ ነው ቲምናዕ አለቃ፥
ዓልዋ አለቃ፥
የቴት አለቃ፥” (ዘፍ 36:40)
የትኒኤል ~ Jathniel: ‘ያምላክ ስጦታ’ ማለት ነው። ከቆሬያውያን በበረኝነት ከተመደቡ፥ ከሜሱላም ልጆች አራተኛው፥ “አራተኛው የትኒኤል፥ አምስተኛው ኤላም፥ ... ሰባተኛው ኤሊሆዔናይ”
(1 ዜና 26:2)
የአራተኛው ክፍል ገዥ ~ Tetrarch: አራተኛ ገዥ ማለት ነው።
በአራተኛ ክፍል፥
ገዥ ለነበረ
የሄሮድስ መጠሪያ፥
“በዚያ ዘመን የአራተኛው
ክፍል ገዥ ሄሮድስ የኢየሱስን ዝና ሰማ” (ማቴ 14:1፤ ሉቃ 3:1፣19፥ 9:7፤ ሐዋ 13:1)
የዑስ ~ Jeush: ‘ሰብሳቢ፣ አደራጅ፣ ገጣጣሚ’ ማለት ነው።
1.የዔሳው ትልቁ ልጅ፥ “አህሊባማም የዑስን፥ የዕላምን፥ ቆሬን ወለደች በከነዓን
ምድር የተወለዱለት
የዔሳው ልጆች
...” (ዘፍ 36:5፣14፣18)
2.
ቢልሐን ልጅ፥ “የይዲኤልም ልጅ ቢልሐን ነበረ። የቢልሐንም ልጆች
የዑስ፥ ብንያም፥
ኤሁድ፥ ... ተርሴስ፥
አኪሳአር ነበሩ።” (1 ዜና
7:10)
3.የሰሜኢ ልጅ፥ “የሰሜኢ ልጆች ኢኢት፥ ዚዛ፥ የዑስ፥ በሪዓ ነበሩ። እነዚህ አራቱ የሰሜኢ ልጆች ነበሩ።” (1 ዜና 23:10፣11)
4.
የሮብዓም ልጅ፥ “እርስዋም የዑስን፥ ሰማራያን፥ ዘሃምን ወንዶች ልጆች ወለደችለት።” (2 ዜና 11:19)
የኢያቢስ ~ Jabesh: ‘ደረቅ’ ማለት ነው።
1.
የሰሎም አባት፥ የእስራኤል አምስተኛ ንጉሥ፥ “የኢያቤስም ልጅ ሰሎም ተማማለበት፥ በይብልዓም መትቶ ገደለው፥ በእርሱም ፋንታ ነገሠ።” (2 ነገ 15:10፣ 13፣14)
2.
“የኢያቢስም ሽማግሌዎች።
ወደ እስራኤል አገር ሁሉ መልክተኞችን
እንድንልክ ሰባት
ቀን ቆይልን
ከዚያም …” (1 ሳሙ 11:3፣ 9፣ 10)
የኢያዕር መንደሮች ~ Havoth-jair: ‘የሠለጠነ መንደር’
ማለት ነው።
1.
የምናሴ ልጅ ኢያዕር፥ የወረራቸውን መንደሮች ሲሰይም የሰጠው ስም፥ “የምናሴም ልጅ
ኢያዕር ሄዶ
መንደሮችዋን ወሰደ፥
የኢያዕርም መንደሮች ብሎ
ጠራቸው።”
(ዘኊ 32:41)
2.
“የምናሴ ልጅ ኢያዕር እስከ ጌሹራውያንና እስከ ማዕካታውያን ዳርቻ ድረስ የአርጎብን ምድር ሁሉ ወሰደ። ይህችንም የባሳንን ምድር እስከ ዛሬ ድረስ በስሙ የኢያዕር መንደሮች
ብሎ ጠራ።” (ዘዳ 3:41)
የኤላ ~ Joelah: ‘የላይ፣አምላክ የረዳው’ ማለት
ነው።የጌዶርዓዊው የይሮሃም ልጅ፥ “የጌዶር ሰው የይሮሃም ልጆች የኤላ፥ ዝባድያ” (1 ዜና 12:7)
የዕላ ~
Jaala:
‘የአላ፣ የላይ’ ማለት ነው። ከምርኮ ከተመለሱ፥ የሰሎሞን አገልጋዮች፥
“የየዕላ ልጆች፥ የደርቆን
ልጆች፥ የጌዴል
ልጆች፥”
(ነህ 7:58)
የዕሡ ~ Jaasau: ‘ሥራዬ’
ማለት ነው።
እንግዳ ሚስቶች
ካገቡ፥ “መትናይ፥ የዕሡ፥
ባኒ፥ ቢንዊ፥
ሰሜኢ፥”
(ዕዝ 10:37)
የዕራ ~ Jarah: ‘ማር’
ማለት ነው።
ከሳኦል ወገን፥
የሚካ ልጅ፥
“አካዝም የዕራን ወለደ
የዕራም ዓሌሜትን፥
ዓዝሞትን፥ ዘምሪን
ወለደ ...” (1 ዜና 9:42)
የክርስቶስ ተቃዋሚ ~ Antichrist: “ልጆች ሆይ፥ መጨረሻው ሰዓት ነው፥
የክርስቶስም ተቃዋሚ ይመጣ ዘንድ እንደ
ሰማችሁ አሁን
እንኳ ብዙዎች
የክርስቶስ ተቃዋሚዎች
ተነሥተዋል፤ ስለዚህም
መጨረሻው ሰዓት
እንደ ሆነ
እናውቃለን”
(1 ዮሐ 2:18፣22፥ 4:3፥ 2
የሐ 1:7)
የዳን ሰፈር ~ Mahanehdan:
‘የዳኝነት ድንኳን፣ የፍርድ
ቤት’
ማለት ነው።
እስራኤላውያን ከግብፅ
ሲወጡ ካረፉባቸው
ስፍራዎች፥ “ወጥተውም በይሁዳ ባለችው በቂርያትይዓሪም ሰፈሩ። ስለዚህም የዚያ ስፍራ ስም እስከ ዛሬ ድረስ የዳን ሰፈር
ተብሎ ተጠራ
እነሆም፥ ከቂርያትይዓሪም በስተ ኋላ ነው።” (መሣ
18:12)
የድላፍ ~
Jidlaph:
‘ማንባት፣ ማልቀስ’
ማለት ነው። የናኮር ልጅ፥ “ኮዛት፥ ሐዞ፥ ፊልዳሥ፥ የድላፍ፥ ባቱኤል ናቸው” (ዘፍ 22:22)
ዩልያ ~
Julia, Junia: ‘ሉጫ ጸጉር’ ማለት ነው። “ለፍሌጎንና ለዩልያ ለኔርያና ለእኅቱም ለአልንጦንም ... ሰላምታ አቅርቡልኝ።”
(ሐዋ 16:15)
ዩልያ / Junia: ‘ወጣት’ ማለት ነው። በሮም የነበረች ክርስቲያን፣ ጳውሎስ በሰላምታ
ደብዳቤው የጠቀሳት፥
“በሐዋርያት መካከል ስመ
ጥሩዎች ለሆኑ፥
ደግሞም ክርስቶስን
በማመን ለቀደሙኝ፥
አብረውኝም ለታሰሩ
ለዘመዶቼ ለአንዲራኒቆንና ለዩልያን ሰላምታ አቅርቡልኝ።” (ሮሜ 16:7)
ዩልዮስ ~
Julius:
‘ሉጫ ጸጉር’ ማለት ነው። ጳውሎስ ታስሮ ወደ ጣሊያን በተወሰደ
ጊዜ፥ የነበረው
የቄሳር መቶ
አለቃ፥ “ወደ ኢጣሊያም
በመርከብ እንሄድ
ዘንድ በተቈረጠ ጊዜ፥ ጳውሎስንና ሌሎችን እስረኞች ከአውግስጦስ ጭፍራ ለነበረ ዩልዮስ ለሚሉት ለመቶ አለቃ አሳልፈው ሰጡአቸው” (ሐዋ 27:1፣3)
ዩሲምኤል ~
Jesimiel:
‘የስመ ኤል፣ የኃያል ስም፣ የአምላክ ስም’ ማለት
ነው። የሰሚ
ልጅ፥ የሲሞናውያን
አለቃ፥ “ኤልዮዔናይ፥ ያዕቆባ፥
የሾሐያ፥ ዓሣያ፥
ዓዲዔል፥ ዩሲምኤል፥
በናያስ፥”
(1 ዜና 4:36)
ዩባል ~
Jubal:
‘ተወርዋሪ፣ ተወንጫፊ’ ማለት ነው። የላሜሕ ልጅ፥ ከዓዳ የወለደው፥
“የወንድሙም ስም ዩባል ነበረ እርሱም በገናንና
መለከትን ለሚይዙ
አባት ነበረ።” (ዘፍ 4:21)
ዩባብ ~ Jobab:
የአባ አባ፣ የአባባ፣ የአባት፣ የአብ፣ የጌታ... ማለት ነው።
[ተዛማጅ ስሞች- ኢዮባብ፣ ዮባብ]
የዮቅጣን ልጅ፥ (ዘፍ 10፡29)
ዩዳሄ ~ Jehoiada: ያሕ ወዴ፣ በጌታ የተወደደ፣ ለአምላክ የቀረበ፣ የእግዚአብሔር ወዳጅ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ዮዳሄ፣ ያሕዳይ፣ ያዱአ፣ ያዳ፣ ዬዳይ፣ ይሆዓዳ፣ ይዲዳ፣ ይዲድያ፣ ዮአዳ፣ ዮዓዳን]
‘ያሕ’(ያሕዌ ፣ ሕያው) እና ‘ወደደ’
ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
የበናያስ አባት፥ (2 ሳሙ 20:23) ፣ (2 ሳሙ 8:18) ፣ (1 ዜና 18:17)
2.
የአሮን ቤት
አለቃ፥ (1 ዜና 12:27)
3.
“...በእግዚአብሔር ቤት አለቃ እንድትሆን እግዚአብሔር በካህኑ በዮዳሄ ፋንታ ካህን አድርጎሃል።” (ኤር 29:25-29፣ 2 ነገ 25:18)
4.
የፋሴሐ ልጅ፥
(ነህ 3:6)
ዩጣ ~ Juttah: ‘የወጣ፣ የተዘረጋ’ ማለት
ነው። በተራራማው
የይሁዳ አገር
የነበረ ከተማ፥ ዩጣ እና ቀርሜሎስ፥ ያዋስኑታል፥ (አያ 15:55) “ማዖን፥ ቀርሜሎስ፥ ዚፍ፥ ዩጣ፥ ኢይዝራኤል፥”
ዪምና ~ Imnah, Jimnah:
ያመነ፣ የታመነ... ማለት ነው። [ተዛማች ስሞች-
ያሚን፣ ይምና]
‘እሙን’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ዪምና / Imnah:
የአሴር ልጅ፥ (1
ዜና 7:30)
. ይምና-
(2 ዜና 31:14)
ዪምና / Jimnah:
(ዘኁ 26:44)
ዪምና / Jimnah: ‘ያመነ፣ የታመነ፣
ቀኝ እጅ’ ማለት ነው። የአሴር ልጅ፥ “የአሴርም ልጆች ዪምና፥ የሱዋ፥ የሱዊ፥ በሪዓ፥ እኅታቸው ሤራሕ የበሪዓ
ልጆችም ሔቤር፥
መልኪኤል።”
(ዘፍ 46:17)
ያሐት ~
Jahath:
አሐቲ፣ አንድ፣ አንድ የሆነ፣ የተዋሐደ ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ኢኢት፣ ኢኤት]
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
. የሰሎሚት
ልጅ፥ (1 ዜና 24:22)
. የሰሜኢ
ልጅ፥ ኢኢት፥
(1 ዜና 23፡10)
. የራያ
ልጅ፥ ኢኤት፥
(1 ዜና 4:2)
. የጌድሶን ልጅ፥ “ከጌድሶን ልጁ ሎቤኒ፥ ልጁ ኢኤት፥ ልጁ ዛማት” (1
ዜና 6:20)
. የሜራሪ
ልጅ፥ (2 ዜና 34:12)
ያሀጽ ~
Jahaz:
‘ጠብ፣ ክርክር’ ማለት ነው። በአርኖን ወንዝ በስተሰሜን፥ በሞዓብና
በአሞራውያን ድንበር፥
በዮርዳኖስ ማዶ
የሚገኝ፥ ሴዎን
የተሸነፈበት ከተማ፥ “ሴዎንም ሕዝቡን ሁሉ ሰበሰበ፥ እስራኤልንም ለመውጋት ወደ ምድረ በዳ ወጣ፥ ወደ ያሀጽም መጣ፥ ከእስራኤልም ጋር ተዋጋ።” (ዘኊ 21:23፤ ዘዳ 2:32)
ያሕልኤል ~
Jahleel:
ያሕለ ኤል፣ ለሕያው አምላክ፣ ለዘላለም ጌታ... ማለት ነው።
[ተዛማጅ ስም- ያሕጽኤል]
‘ያሕ’፣ ‘ለ’ እና ‘ኤል’
ከሚሉት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። የዛብሎን
ልጅ፥ (ዘፍ 46:14)
ያህዌ ይርኤ ~ Jehovah-jireh: ‘ሕያው አምላክ ያያል’ ማለት ነው። መሪያ ተራራ፥ አብርሃም መሥዋዕት ያቀረበበት ቦታ፥ “አብርሃምም ያንን ቦታ ያህዌ ይርኤ ብሎ ....ድረስ በእግዚአብሔር ተራራ ይታያል ይባላል።” (ዘፍ 22:14)
ያህዳይ ~ Jahdai:
ያሕ ዲያ፣ ያሕ ውድ፣ የሕያው ውድ፣ የተወደደ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ዩዳሄ፣ ዮዳሄ፣ ያዱአ፣ ያዳ፣ ዬዳይ፣ ይሆዓዳ፣ ይዲዳ፣ ይዲድያ፣ ዮአዳ፣ ዮዓዳን፣ ዮዳሄ]
‘ያሕ’ (ያሕዌ
፣ ሕያው) እና
‘ውድ’ ከሚሉት ቃላት የተመሠረተ
ስም ነው።
“ሐራንም ጋዜዝን ወለደ። የያሕዳይም ልጆች ሬጌም፥ ኢዮታም፥ ጌሻን፥ ፋሌጥ፥ ሔፋ፥
ሸዓፍ ነበሩ።” (1 ዜና 2፡47)
ያሕጽኤል ~ Jahleel, Jahziel: ያሕ ዘ ኤል፣ ለሕያው አምላክ፣ ለዘላለም ጌታ ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም-
ያሕልኤል]
Jahleel, Jahziel-
‘ያሕ’፣ ‘ለ(ዘ)’ እና ‘ኤል’ ከሚሉት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ያሕጽኤል / Jahleel:
የንፍታሌም ልጅ፥ (ዘፍ 46፡24)
ያሕጽኤል / Jahziel:
(1 ዜና 7:13)
ያሕጽኤል /
Jahzeel: ‘ያሕ ዘ ኤል፣ ሕያው አምላክ፣ የእግዚአብሔር ጸጋ፣ በአምላክ የተሰጠ’ ማለት ነው። ከአራቱ የንፍታሌም ልጆች የመጀመሪያው፥ “የንፍታሌምም ልጆች ያሕጽኤል፥ ጉኒ፥ ዬጽር፥ ሺሌም።” (ዜና 46:24)
ያሎን ~ Jalon: ‘ጢሰኛ፣ ነዋሪ’
ማለት ነው።
ከይሁዳ ነገድ
የሆነ፥ የዕዝራ አራተኛና የመጨረሻ ልጅ፥ “የዕዝራም ልጆች ዬቴር፥ ሜሬድ፥ ዔፌር፥ ያሎን ነበሩ። ዬቴርም
ማርያምን፥ ሸማይን፥
የኤሽትምዓን አባት
ይሽባን ወለደ።” (1 ዜና
4:17)
ያሚን ~ Jamin: ያሚን፣ ያምን፣ ያመነ፣ የተቀበለ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች:- ሐማ፣ ሄማን፣ ንዕማን፣ አሒማን፣ አማና፣ አሜን፣ አሞን፣ አኪመን፣ ዪምና፣ ይምና]
‘አመነ’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
የስምዖን ልጅ፥
(ዘኁ 26፡12)
2.
የራም ልጅ፥
(1 ዜና 2:27)
3.
ዕዝራም ታላቁን አምላክ እግዚአብሔርን ሲባርክ ሕዝቡን ያስተምሩ ከነበሩ፥ (ነህ 8:7)
ያሱብ ~
Jashub, Shear- jashub: ያስብ፣ ቸር ያሽብ፣ ጌታ ያስብ፣ በአምላክ የታሰበ ማለት ነው።
‘አሰበ’
ከሚለው ግስ
የመጣ ስም ነው።
[ትርጓሜውም “ቅሬታ ይመለሳል” ማለት
ነው / መቅቃ]
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ያሱብ / Jashub:
1.
የይሳኮር ልጅ፥
(1 ዜና 7፡1)
2.
እንግዶች ሚስቶቻ ቸውን ከተው፣ የባኒ ልጅ፥ (ዕዝ 10:29)
ያሱብ / Shear - jashub: የኢሳይያስ ልጅ፥ (ኢሳ 7:3)
ያሳር ~ Jesher: ‘ቀጥተኛ፣ እውነተኛ’ ማለት
ነው። የካሌብ
ልጅ፥ “የኤስሮምም ልጅ ካሌብ ከሚስቱ ከዓዙባ ከይሪዖትም ልጆች ወለደ ልጆቹዋም ያሳር፥
ሶባብ፥ አርዶን
ነበሩ”
(1 ዜና 2:18)
ያሪን ~ Jarib: ‘ተቀናቃኝ፣ ጠላት፣ ምቀኛ’ ማለት ነው።
1.
የስምዖን ልጅ፥ “የስምዖንም ልጆች ነሙኤል፥ ያሚን፥ ያሪን፥ ዛራ፥
ሳኡል”
(1 ዜና 4:24)
2.
ካህናቱን ወደ ኢየሩሳሌም እንዲያመጡ ዕዝራ ከላካቸው አለቆች አንዱ፥ “ወደ አለቆቹም
ወደ አልዓዛር፥
ወደ አርኤል፥
ወደ ሸማያ፥
ወደ ኤልናታን፥
ወደ ያሪብ፥
ወደ ኤልናታን፥
ወደ ናታን፥
ወደ ዘካርያስ፥
ወደ ሜሱላም፥
ደግሞም ወደ አዋቂዎቹ ወደ ዮያሪብና ወደ ኤልናታን ላክሁ።” (ዕዝ 8:16)
3.
ከባቢሎን ምርኮ ከተመለሱ፥ ካህናቱም ወገን ልጆች እንግዶቹን ሴቶች ካገቡ፥
“...ከኢዮሴዴቅ ልጅ
ከኢያሱ ልጆችና
ከወንድሞቹ፥ መዕሤያ፥
አልዓዛር፥ ያሪብ፥
ጎዶልያስ።”
(ዕዝ 10:18)
ያራሕ ~ Jerah: ‘ጨረቃ’ ማለት ነው። የዮቅጣን አራተኛ ልጅ፥ “ያራሕንም፥ ሀዶራምንም፥ አውዛልንም፥” (ዘፍ 10:27፤ 1 ዜና 1:20)
ያሬሽያ ~ Jaresiah: ‘ያርስ ያሕ፣ ሕያው ያረሰው፣ አምላክ የመገበው’ ማለት ነው። ብንያማዊ፥ “ሸሃሪያ፥ ጎቶልያ፥ ያሬሽያ፥ ኤልያስ፥ ዝክሪ፥ የይሮሐም ልጆች” (1
ዜና 8:17)
ያሬድ ~ Jared: ወሪድ፣ ይወርድ፣ የወረደ፣ ከላይ የመጣ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ዬሬድ]
‘ወረደ’
ከሚለው ግስ
የመጣ ስም ነው።
የመላልኤል ልጅ ሆኖ፣ የሄኖክ አባት፥ (ዘፍ 5፡15-20)
ያሻር ~ Jasher: ‘ጻድቅ’
ማለት ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ
ስብስብ ውስጥ
ያልተጨመረ፥ ነገር
ግን በኢያሱ
መጽሐፍ የተጠቀሰ
ቅዱስ መጽሐፍ፥
“ሕዝቡም ጠላቶቻቸውን እስኪበቀሉ
ድረስ ፀሐይ
ቆመ፥ ጨረቃም
ዘገየ። ይህስ
በያሻር መጽሐፍ
የተጻፈ አይደለምን? ፀሐይም
በሰማይ መካከል
...” (ኢያ 10:13)
ያሾቢአም ~ Jashobeam: ‘መንደርተኛ፣ ነዋሪ’ ማለት
ነው። በጺቅላግ ከቂስ ልጅ ከሳኦል በተሸሸገ ጊዜ ወደ ዳዊት ከመጡ፥ “ቆርያውያን ሕልቃና፥ ይሺያ፥ አዛርኤል፥
ዮዛር፥ ያሾቢአም” (1 ዜና 12:6)
ያቂም ~ Jakim: ያቂም፣ ያቁም፣ የቆመ፣ የጸና፣ የበረታ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ቀሙኤል፣ ቁሚ፣ አኪቃም፣ አዶኒቃም፣ ኢዮአቄም፣ ዓዝሪቃም፣ ኤልያቄም፣ ዮቂም፣ ዮአቂም]
‘አቆመ’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
በኢየሩሳሌም የተቀመጡ
በትውልዶቻቸው አለቆች የነበሩ ከአባቶቻቸው ቤቶች አለቆች፥ የኤልፍዓል ልጆች፥ (1 ዜና 8:19)
2.
ዳዊት ከአልዓዛር ልጆች ከሳዶቅ ጋር፥ ከኢታምርም ልጆች ከአቢሜሌክ ጋር ሆኖ
እንደ አገልግሎታቸው
ሥርዓት ከፍሎ
ከመደባቸው፥ (1 ዜና 24፡12)
ያቆብ ~ Jacob: ያቅብ፣
ያስቀር፣ ይጠብቅ፣
ያግድ፣ ይከልክል... ማለት
ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ያዕቆባ፣ ያዕቆብ]
‘አቀበ’
ከሚለው ግስ
የተገኘ ስም ነው።
[ትርጉሙ “ተረከዝን ይይዛል” ማለት
ነው /
መቅቃ]
. የይስሐቅ ልጅ፥ “ራሔልም ለያዕቆብ ልጆችን እንዳልወለደች ባየች ጊዜ በእኅትዋ ቀናችባት
ያቆብንም።”
(ዘፍ 31:1)
. ያዕቆብ ፥ (ዘፍ 25፡26)
ያቢ ~
Vophsi:
‘ሀብታም’
ማለት ነው። የናቢ አባት፥ “ከንፍታሌም ነገድ የያቢ ልጅ ናቢ” (ዘኊ 13:14)
ያባል ~ Jabal: ‘ምንጭ፣ ወንዝ፣ ጎርፍ’ ማለት ነው። የላሜሕ እና የዓዳ ልጅ፥ “ዓዳም ያባልን ወለደች እርሱም በድንኳን የሚቀመጡት የዘላኖች አባት ነበረ።” (ዘፍ 4:20)
ያቤጽ ~ Jabez:
‘ሐዘን፣ መከራ፣ ችግር፣ ጣር’ ማለት ነው።
1.
የይሁዳ ወገን የሆነ፥ “...እናቱም። በጣር ወልጄዋለሁና ብላ ስሙን፦ ያቤጽ ብላ ጠራችው።”
(1 ዜና 4:9፣10)
2.
የቦታ ስም፥
“በያቤጽም የተቀመጡ የጸሐፊዎች ወገኖች ቲርዓውያን፥ ሺምዓታውያን፥
...” (1 ዜና 2:55)
ያቦቅ ~ Jabbok: ‘ባዶ፣ ማድረግ’ ማለት ነው። በአሞን ልጆች ድንበር ያለ ወንዝ፥ “በሐሴቦን የተቀመጠው፥ በአርኖንም ሸለቆ አጠገብ ካለችው ከአሮዔር፥ ... እስከ ያቦቅ ወንዝ እስከ አሞን ልጆች ዳርቻ ድረስ፥” (ኢያ 12:2፣5)
ያትራይ ~
Jeaterai:
የሌዊያዊው፥ የጌድሶን ልጅ፥ “ልጁ ዮአክ፥ ልጁ አዶ፥ ልጁ ዛራ፥ ልጁ ያትራይ”
(1 ዜና 6:21)
ያኒም ~ Janum:
‘ማንቀላፋት፣ እንቅልፍ’
ማለት ነው።
በይሁዳ ተራራዎች
ላይ ያለ ከተማ፥ “አራብ፥ ዱማ፥ ኤሽዓን፥ ያኒም፥ ቤትታጱዋ፥” (ኢያ 15:53)
ያናይ ~ Jaanai: ‘የአምላክ መልስ፣ የሆነ፣ የተደረገ’
ማለት ነው።
ከጋድ ነገድ አለቃ፥
“አንደኛው ኢዮኤል፥ ሁለተኛው ሳፋም፥ ያናይ፥ ሳፋጥ በበሳን ተቀመጡ።” (1 ዜና
5:12)
ያኖዋ ~ Janoah: ‘የኖህ፣ ኖኃዊ፣ ዕረፍት’
ማለት ነው።
የአሦር ንጉሥ ቴልጌልቴልፌልሶር ወርሮ
ከወሰዳቸው፥ “በእስራኤልም ንጉሥ
በፋቁሔ ዘመን
የአሦር ንጉሥ
ቴልጌልቴልፌልሶር መጥቶ
ዒዮንና አቤልቤትመዓካን፥ ያኖዋንም፥ ቃዴስንና
አሶርንም፥ ገለዓድንና ገሊላንም፥ የንፍታሌምን አገር ሁሉ ወሰደ ...” (2 ነገ 15:29)
ያዕቃን ~
Jaakan:’መክበብ’ ማለት ነው። “የእስራኤልም ልጆች ከብኤሮት ብኔያዕቃን ወደ
ሞሴራ ተጓዙ
በዚያም አሮን
ሞተ በዚያም
ተቀበረ በእርሱም
ፋንታ ልጁ አልዓዛር ካህን ሆነ። “(ዘዳ 10:6)
ያዕቆባ ~
Jaakobah:
ያቅባህ፣ አቃቢ፣ ጠባቂ፣ ቆጣቢ... ማለት ነው።
[ተዛማጅ ስሞች- ያቆብ፣ ያዕቆብ]
‘አቀበ’
ከሚለው ግስ
የተገኘ ስም
ነው። በወገኖቻቸው
ላይ አለቆች
የነበሩ፥ (1 ዜና 4፡36)
ያዕቆብ ~
Jacob, James: ያቆብ፣ ያቅብ፣ ያስቀር፣ ይጠብቅ፣ ያግድ፣ ይከልክል... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ያቆብ፣ ያዕቆባ]
‘አቀበ’
ከሚለው ግስ
የተገኘ ስም ነው።
[ትርጉሙ “ተረከዝን ይይዛል” ማለት
ነው /
መቅቃ]
የይስሐቅ ልጅ፥ “ከዚያም በኋላ ወንድሙ ወጣ፥ በእጁም የዔሳውን ተረከዝ ይዞ ነበር
ስሙም ያዕቆብ ተባለ። እርስዋ ልጆችን
በወለደቻቸው ጊዜ
ይስሐቅ ስድሳ
ዓመት ሆኖት
ነበር:”
(ዘፍ 25፡26)
የማርያም እጮኛ፣ የዮሴፍ አባት፥ "ያዕቆብም ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስን የወለደች የማርያምን እጮኛ ዮሴፍን ወለደ።" (ማቴ 1:16)
ያዕቆብ / James:
ሐዋርያው ያዕቆብ፥ “ከዚያም እልፍ ብሎ ሌሎችን ሁለት ወንድማማች የዘብዴዎስን ልጅ ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ከአባታቸው
ከዘብዴዎስ ጋር
በታንኳ መረባቸውን
ሲያበጁ አየ፤
ጠራቸውም።”
(ማቴ4:21)
1.
የዘብዴዎስና የሰሎሜ
ልጅ፥ የዮሐንስ ታላቅ ወንድም፥ “ከስድስት ቀንም በኋላ ኢየሱስ ጴጥሮስንና ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ይዞ ወደ ረጅም ተራራ ብቻቸውን አወጣቸው።” (ማቴ 20:20፥ 27:56)
2.
የጌታ ወንድም፥ “ነገር ግን ከጌታ ወንድም ከያዕቆብ በቀር ከሐዋርያት ሌላ
አላየሁም።”
(ገላ 1:18፣19)
ያእዛንያ ~ Jaazaniah:
ያዝን ያሕ፣ አምላክ ያዘነለት፣ እግዚአብሔር ጸሎቱን የሰማው ማለት ነው።
‘አዘነ’ እና ‘ያሕ’(ያሕዌ ፣ ሕያው) ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
የኤርምያስ ልጅ፥
(ኤር 35፡3)
2.
የሆሻያ ልጅ፥
(ኤር 42፡1)
3.
የማዕካታዊው ልጅ፥
(2 ነገ 25:23)
4.
የሳፋን ልጅ፥
(ሕዝ 8:11)
5.
የዓዙርን ልጅ፥
(ሕዝ 11:1)
ያኪን ~ Jachin: ‘አበረታች’ ማለት ነው።
1.
የስምዖን አራተኛ
ልጅ፥ “የስምዖን ልጆች ይሙኤል፥ ያሚን፥ ኦሃድ፥ ያኪን፥ ጾሐር፥ የከነዓናዊት ልጅ ሳኡል” (ዘፍ 46:10)
2.
የሀያ አንደኛው ምድብ፥ የካህናትአለቃ፥ “ሀያኛው ለኤዜቄል፥ ሀያ አንደኛው ለያኪን፥ ሀያ ሁለተኛው ለጋሙል” (1 ዜና 24:17)
3.
ከግዞት ከተመለሱ ካህናት አንዱ፥ “ከካህናቱም ዮዳሄ፥ ዮአሪብ፥ ያኪን” (1 ዜና 9:10)
ያካን ~
Jachan:
‘በጥባጭ’ ማለት ነው። ከሰባቱ የጋድ ነገድ አለቆች አንዱ፥ “የአባቶቻቸውም ቤቶች ወንድሞች ሚካኤል፥ ሜሱላም፥ ሳባ፥ ዮራይ፥ ያካን፥ ዙኤ፥ ኦቤድ
ሰባት ነበሩ።” (1 ዜና 5:13)
ያዋን ~ Javan: ‘አታላይ’ ማለት ነው።
1.
የያፌት ልጅ፥ “የያፌት ልጆች ጋሜር፥ ማጎግ፥ ማዴ፥ ያዋን፥ ይልሳ፥
ቶቤል፥ ሞሳሕ፥
ቴራስ ናቸው።” (ዘፍ 10:2፣4)
2.
የዓረባውያን ከተማ፥ “ዌንዳንና ያዋን ስለ አንቺ ሸቀጥ ይነግዱ ነበር ከኦሴል
የተሠራ ብረትና
ብርጕድ ቀረፋም
ሸቀጥሽ ነበረ።” (ሕዝ
27:19)
ያዚዝ ~ Jaziz: ‘ያዝዝ፣ ይምራ፣ ያስሂድ’
ማለት ነው።
አጋራዊው ሰው፥
የዳዊት እረኞች አለቃ፥ “በመንጎቹም ላይ አጋራዊው ያዚዝ ሹም ነበረ። እነዚህ ሁሉ በንጉሡ በዳዊት ሀብት ላይ ሹሞች ነበሩ” (1 ዜና 27:31)
ያዝኤል ~
Jaaziel:
ያዘ ኤል፣ አምላክ የጠበቀው፣ በጌታ ያለ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ያዝያ]
‘ያዘ’ እና ‘ኤል’
ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው ።
ዳዊት በዜማ
ዕቃ በመሰንቆና
በበገና በጸናጽልም
እንዲያዜሙ፥ ድምፃቸውንም
በደስታ ከፍ እንዲያደርጉ መዘምራኑን ወንድሞቻቸውን ይሾሙ ዘንድ ከተናገራቸው የሌዋውያን
ኣለቆች፥ (1 ዜና 15፡15)
ያዝያ ~
Jaaziah:
ያዘ ያሕ፣ በጌታ የተያዘ፣ አምላክ የጠበቀው... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ያዝኤል]
Jaaziah- ‘ያዘ’
እና ‘ያሕ’ (ያሕዌ ፣ ሕያው) ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። የሜራሪ ወገን፥ (1 ዜና 24፡26፣27) ፣ (1
ዜና 15:18)
ያዱአ ~ Jaddua: ውዱ፣ የተወደደ፣ ተወዳጅ ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ዩዳሄ፣ ዮዳሄ፣ ያሕዳይ፣ ያዳ፣ ያዳይ፣ ዬዳይ፣ ይሆዓዳ፣ ይዲዳ፣ ይዲድያ፣ ዮአዳ፣ ዮዓዳን፣ ዮዳሄ]
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
ከነህምያ ጋር
የቃል ኪዳኑን
ደብዳቤ ካተሙት
አለቆ ች
አንዱ፥ (ነህ 10፡21)
2.
የዮናታን ልጅ፥
(ነህ 112:11፣ 22)
ያዳ ~
Jada:
ውድ፣ የተወደደ፣ ተወዳጅ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ዩዳሄ፣ ዮዳሄ፣ ያሕዳይ፣ ያዱአ፣ ያዳይ፣ ዬዳይ፣ ይሆዓዳ፣ ይዲዳ፣ ይዲድያ፣ ዮአዳ፣ ዮዓዳን፣ ዮዳሄ]
የኦናም ልጅ፥
(1 ዜና 2:28)
ያዳይ ~
Jadau:
ውዱ፣ የተወደደ፣ ተወዳጅ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ዩዳሄ፣ ዮዳሄ፣ ያሕዳይ፣ ያዱአ፣ ያዳ፣ ዬዳይ፣ ይሆዓዳ፣ ይዲዳ፣ ይዲድያ፣ ዮአዳ፣ ዮዓዳን፣ ዮዳሄ]
በዕዝራ ዘመን እንግዳ ሚስቶችን ካገቡ፥ የናባው ልጅ፥ (ዕዝ 10:43)
ያዶን ~
Jadon:
የዳን፣ የዳኝ፣ ይዳኝ፣ ይፈርድ፣ ይበይን... ማለት ነው።
‘ዳኝ’
ከሚለው ቃል
የመጣ ስም ነው።
የኢየሩሳሌምን ቅጥር
በመጠገን የተባበረ፣
ሜሮኖታዊው ሰው፥
(ነህ 3:7)
ያጉር ~
Jagur:
‘አጉር፣ አገር፣ መኖሪያ’ ማለት ነው። የኤዶም አዋሳኝ፥ በደቡብ ጫፍ የሚገኝ የይሁዳ ከተማ፥ “ቀብስኤል፥ ዔዴር፥ ያጉር፥ ቂና፥” (ኢያ 15:22)
ያፊዓ፣ ያፍያ ~ Japhia:
‘ግርማዊ፣ መልካም’ ማለት ነው።
1.
ከኢያሱ ጋር ለጦርነት ከተባበሩ፥ የኪሶ ንጉሥ፥ “ስለዚህም የኢየሩሳሌም ንጉሥ አዶኒጼዴቅ ወደ ... ለኪሶ ንጉሥም ወደ ያፊዓ፥ ወደ አዶላም ንጉሥም ወደ ዳቤር ልኮ። ወደ እኔ ውጡ፥” (ኢያ 10:3)
2.
የዳዊት ልጅ፥ ያፍያ፥ “ናፌቅ፥ ያፍያ፥ ኤሊሳማ፥ ኤሊዳሄ፥ ኤሊፋላት።” (2 ሳሙ 5:16)
3.
በዛብሎን ደቡባዊ ድንበር የሚገኝ ከተማ፥ “ወደ ዳብራትም ወጣ፥
ወደ ያፊዓም
ደረሰ። ከዚያም በምሥራቅ
... ወጣ።”
(ኢያ 19:12)
ያፌት ~
Japhet:
ያፈት፣ ይፍታ፣ ይፈታ፣ የተፈታ፣ የተለቀቀ፣ የተስፋፋ... ማለት ነው።
‘ፈታ’ ከሚለው ቃል የመጣ ስም ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ኤፍታህ፣ ይፍታሕ፣ ይፍታሕኤል፣ ዮፍታሔ፣ ፈታያ]
. የኖኅ
ልጅ፥ (ዘፍ 5፡32)
. “እግዚአብሔርም ያፌትን ያስፋ፥ በሴምም ድንኳን ይደር ከነዓንም ለእነርሱ ባሪያ
ይሁን”
(ዘፍ 9፡27)
ያፍሌጥ ~ Japhlet:
‘የዳነ፣ የተፈታ፣ ነጻ የወጣ’
ማለት ነው። በበረያ በኩል፥ የአሴር ወገን፥ “ሔቤርም ያፍሌጥን፥ ሳሜንር፥ ... ሶላን ወለደ።” (1 ዜና 7:32፣33)
ዬሕድያ ~ Jehdeiah: ያሕድ ያሕ፣ በጌታ የተወደደ፣ ለአምላክ የቀረበ፣ የተመሰገነ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ዩዳሄ፣ ዮዳሄ፣ ያሕዳይ፣ ያዱአ፣ ያዳ፣ ያዳይ፣ ዬዳይ፣ ይሆዓዳ፣ ይዲዳ፣ ይዲድያ፣ ዮአዳ፣ ዮዓዳን፣ ዮዳሄ]
‘ውደ’ እና ‘ያሕ’ (ያሕዌ ፣ ሕያው) ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። የሱባኤል
ልጅ፥ (1 ዜና 24፡20)
ዬሬድ ~
Jered:
ያሬድ፣ ከላይ የወረደ፣ ከላይ የመጣ ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም-
ያሬድ]
‘ወረደ’
ከሚለው ግስ
የመጣ ስም ነው።
. የጌዶር
አባት፥ (1 ዜና 4:18)
. “ያሬድ፥
ሄኖክ፥ ማቱሳላ፥
ላሜሕ”
(1 ዜና 1፡3)
ዬቴር ~ Jether, Ithra:
ዬቴር፣ የተከበረ፣ ግርማዊ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ዮቶር]
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ዬቴር / Ithra:
የይሁዳን ሠራዊት
አለቃ፣ የይስማኤላዊ የአሜሳይ አባት፥
(2 ሳሙ 17:25)
ዬቴር / Jether:
1.
የጌዴዎን ልጅ፥
(መሣ 8፡20)
2.
የሙሴ አማት፥
(ዘኁ 4:18)
3.
“... የይሁዳንም ሠራዊት አለቃ የዬቴርን ልጅ አሜሳይን፥ በሰይፍ ገድሎአልና እግዚአብሔር ደሙን በራሱ ላይ ይመልሰው።” (1 ነገ 2:32)
4.
የያዳ ልጅ፥
(1 ዜና 2:32)
5.
የዕዝራ ልጅ፥
(1 ዜና 4:17)
6.
የአሴር ልጆች፥ የአባቶቻቸው ቤቶች አለቆች፥ ከተመረጡ ጽኑዓን ኃያላን ሰዎች፥ ከመኳንንቱ አለቆች፥ (1 ዜና 7:38)
ዬዳይ ~
Jahdo:
ያሕዶ፣ ይሆዳ፣ ውህድ፣ ተዋሃደ፣ አንድ የሆነ... ማለት ነው።
‘ውህድ’
ከሚለው ቃል
የመጣ ስም
ነው። የኢዬሳይ
አባት፣ የቡዝ ልጅ፥
(1 ዜና 5፡14)
ዬጽር ~ Jezer:
ጾር፣ ጦር፣ ፈተና... ማለት ነው። የንፍታሌም ልጅ፥ (ዘፍ 46፡24)
ይሃሌልኤል ~
Jehalelel:
ያሃልለ ኤል፣ ለሕያው አምላክ እልል፣ ሃሌሉያ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ሃሌሉያ፣ ሂሌል፣ ማህለህ፣ ማህለት]
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
የዓዛርያስ አባት፥
(2 ዜና 29:12)
2.
የይሁዳ ወገን፥
(1 ዜና 4፡16)
ይሑባ ~ Jehubbah:
‘የተጠበቀ’ ማለት ነው። የአሴር ወገን፥ የሳሜር ልጅ፥ “የሳሜርም ልጆች አኪ፥ ሮኦጋ፥ ይሑባ፥ አራም ነበሩ።” (1 ዜና 7:34)
ይሁዲ ~ Jehudi: ይሁዲ፣ አይሁዳዊ፣ ውህድ፣ ተዋሃደ፣ አንድ የሆነ፣ ያይሁድ ወገን ማለት ነው።
‘ይሁዳ’
ከሚለው ስም
የመጣ ስም ነው።
የናታንያ ልጅ፥ ወደ ባሮክ የተላከ፥ (ኤር 36፡14፣21)
ይሁዳ ~ Juda, Judah, Judas, Jude, Judea:
ዩዳ፣ ይሁዳ፣ ውህድ፣ ተዋሃደ፣ አንድ የሆነ፣ አይሁዳዊ... ማለት ነው። (ውድ፣ የተወደደ፣ የተመሰገነ፣የቀረበ ተብሎም ይተረጎ ማል)
‘ዋሐደ’ ከሚለው ግስ የመጣ
ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ይሁዳ / Juda:
1.
በጌታ የዘር ሐረግ የተጠቀሰ፣ የዮሴፍ ልጅ፥ (ሉቃ 3:30)
2.
በጌታ የዘር ሐረግ፥ የያዕቆብ ልጅ፥ (ሉቃ 3:33፣34) ፣ የአይሁድ ዘር፥ “ጌታችን ከይሁዳ ነገድ እንደወጣ የተገለጠ
ነውና፥ …” (ዕብ 7:14) (ራእ 5:5፣ 7:5)
3.
የጌታ ወንድም በመባል የሚታወቀው፥ “ይህስ ጸራቢው የማርያም ልጅ የያቆብም የዮሳም
የይሁዳም የስምዖንም
ወንድም አይደለምን? እኅቶቹስ
...” (ማር 6:3)
ይሁዳ / Judah:
1.
ከሊያ የተወለደው፣ የያዕቆብ ልጅ፥ “ደግሞም ፀነስች፥ ወንድ ልጅንም ወለደች በዚህም ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ አለች ስለዚህም ስሙን ይሁዳ ብላ
ጠራችው...”
(ዘፍ 29:35)
2.
“ይሁዳም ባያት ጊዜ ጋለሞታን መሰለችው ፊትዋን ተሸፍና ነበርና።”
(ዘፍ 38፡15)
ይሁዳ / Judas:
1.
የያዕቆብ ልጅ፥ ይሁዳ፥ (ማቴ 1:2 ፣ 3)
2.
ጌታን አሳልፎ የሰጠው፣ የስምዖን ልጅ የአስቆሮቱ፥ ይሁዳ፥ (ዮሐ
6:71፣ 13:2፣ 26) ፣ (ሥራ 1:25)
3.
ከይሁዳ ወገን፥
(ሥራ 9:11)
4.
ሐዋርያው በርስያን፥ (ሥራ 15:22፣ 27፣ 32)
ይሁዳ / Jude:
ሐዋርያው፥ የያዕቆብ ወንድም፥ ይሁዳ፥ (ይሁ 1:1)
ይሁዳ / Judea:
በዮርዳኖስ በስተምዕራብ የፍልስጥኤም ምድር፣ ጌታ የተወለደበት ቦታ፥ (ማቴ 2:1፣ 5)
ይሁዳ ካለች ከበኣል ~ Baale of
Judah:
ባለ ይሁዳ፣ በዓለ ይሁዳ፣ የአይሁድ በዓል፣ የይሁዳ ጌታ... ማለት ነው።
Baale of Judah- ‘ባለ’ እና ‘ይሁዳ’ ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
የእግዚአብሔር ታቦት ተቀምጦበት የነበረ፣ የቦታ ስም፥ (2 ሳሙ 6፡2)
ይሁድ ~ Jehud: ውሕድ ማለት ነው። ከዳን ነገድ ከተሞች አንዱ፥ (ኢያ 19:45)
ይሒኤል ~
Jehiel:
ያሕ ኤል፣ ሕያው አምላክ፣ ሕያው ኃይል፣ ዘላለማዊ ጌታ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ይዑኤል፣ ይዒኤል]
‘ያሕ’ እና ‘ኤል’
ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
በእግዚአብሔር ቤተ
መቅደስ እንዲያገለግሉ በዳዊት ከተሾሙ ሌዋውያን፥ (1 ዜና 15:18 ፣ 20)
2.
የኢዮሣፍጥ ልጅ፥
(2 ዜና 21:2)
3.
በንጉሥ ኢዮስያስ
ዘመን፥ ከእግዚአብሔር
ቤት አለቆች
አንዱ፥ (2 ዜና
35:8)
4.
የለአዳን ልጅ፥
(1 ዜና 23:8)
5.
የሐክሞኒ ልጅ፥
(1 ዜና 27:32)
6.
የአብድዩ አባት፥ የኢዮአብ ልጅ፥ (ዕዝ 8:9)
7.
የኤላም ልጅ፥ (ዕዝ 10:2)፣ (ዕዝ 10:26)
8.
የካሪም ልጅ፥
(ዕዝ 10:21)
. የንጉሥ ሕዝቅያስ መንግሥትን ለመመለስ ከተባበሩ አንዱ፣ ሌዊያዊው፥ ይዒኤል- (2 ዜና 29:14)
ይሒዝቅያ ~ Jehizkiah:
ያሕ ሕዝቂያ፣ የአምላክ ኃይል፥ የሕያው ብርታት፣ የሕያው አምላክ ቃል... ማለት ነው።
‘ሕዝቅ’ እና ‘ያሕ’ (ያሕዌ) ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። የሰሎም
ልጅ፥ (2 ዜና 28፡12)
ይህዌህ ንሲ ~ Jehovah-nissi: ያሕ ነሥአ፣ አምላክ አነሣ፣ ሕያው ተሸከመ... ማለት
ነው። ሙሴ፥ እስራኤል ከአማሌቃውያን ጋር ሲዋጉ፥ እጁን ዘርግቶ ኃይልን ባገኙበት ኮረብታ፥ ላቆመው መቅደስ የሰጠው ስም፥ “ሙሴም መሠዊያ ሠራ፥ ስሙንም
ይህዌህ ንሲ ብሎ
ጠራው”
(ዘጸ 17:15)
ይሆሐናን ~ Johanan, Jehohanan: የሐናን፣ የጌታ የሆነ፣ እግዚአብሔር የማረው፣ የሕያው ስጦታ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም-
ዮሐናን] ‘ያሕ’ (ያሕዌ) እና ‘አናን’ (ሐና) ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። [ትርጉሙ “እግዚአብሔር ጸጋ ሰጭ ነው” ማለት ነው / መቅቃ]
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
የቤባይ ልጅ፥
(ዕዝ 10:28)
2.
የጦብያ ልጅ፥
(ነህ 6:18)
3.
በዮአቂም ዘመን የአባቶች ቤቶች አለቆች፥ (ነህ 12:14)
4.
“ዘካርያስ፥ ሐናንያ መለከት ይዘው፥ መዕሤያ፥ ሸማያ፥ አልዓዛር፥ ኦዚ፥ ይሆሐናን፥
...” (ነህ 12:42)
. የሜሱላም ልጅ፥ “ሰባተኛው ኤሊኤል፥ ስምንተኛው ዮሐናን” (1 ዜና
12:12)
ይሆሐናን / Jehohanan: ‘አምላክ የሰጠው’ ማለት ነው።
1.
የመቅደሱ በር
ጠባቂ የነበረ፥ “አራተኛው የትኒኤል፥ አምስተኛው ኤላም፥ ስድስተኛው ይሆሐናን፥ ሰባተኛው ኤሊሆዔናይ።” (1 ዜና 26:3)
2.
የኢዮሣፍጥ ሹማምንት
አንዱ፥ “ከእርሱም በኋላ አለቃው ይሆሐናን፥
ከእርሱም ጋር
ሁለት መቶ
ሰማንያ ሺህ
ሰዎች ነበሩ” (2 ዜና
17:15)
3.
የይስማኤል አባት፥ “በሰባተኛውም ዓመት ዮዳሄ በረታ፥ የመቶ አለቆቹንም፥
የይሮሐምን ልጅ
ዓዛርያስን፥ የይሆሐናንንም ልጅ ይስማኤልን፥ የዖቤድንም ልጅ ... ወስዶ ከእነርሱ ጋር ቃል ኪዳን አደረገ።” (2 ዜና 23:1)
4.
እንግዳ ሚስቶቻቸውን
እንዲፈቱ ከታዘዙ፥ “ከቤባይ ልጆችም፤ ይሆሐናን፥ ሐናንያ፥
ዘባይ፥ አጥላይ” (ዕዝ 10:28)
5.
ካህን፥ “ከአማርያ ይሆሐናን፥
ከመሉኪ ዮናታን፥” (ነህ 12:14)
6.
የኢየሩሳሌምን ቅጥር በመጠገን ከተባበሩ ካህናት፥ (ነህ 12:42)
“ዘካርያስ፥ ሐናንያ
መለከት ይዘው፥
መዕሤያ፥ ሸማያ፥
አልዓዛር፥ ኦዚ፥
ይሆሐናን፥ መልክያ፥ ኤላም፥ ... አለቃቸውም ይዝረሕያ ነበረ።” (ነህ 12:14)
ይሆዓዳ ~
Jehoadah:
ያሕ ዓድ፣ ሕያው ውድ፣ በጌታ የተወደደ፣ የአምላክ ወዳጅ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ዩዳሄ፣ ዮዳሄ፣ ያሕዳይ፣ ያዱአ፣ ያዳ፣ ያዳይ፣ ዬሕድያ፣ ዬዳይ፣ ይዲዳ፣ ይዲድያ፣ ዮአዳ፣ ዮዓዳን፣ ዮዳሄ]
‘ያሕ’ (ሕያው)
እና ‘ውድ’ ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። የአካዝ
ልጅ፥ (1 ዜና 8፡36)
ይሙኤል ~ Jemuel: ‘የአምላክ ቀን’ ማለት
ነው። የስሞዖን
ትልቁ ልጅ፥
“የስሞዖን ልጆች ይሙኤል፥
ያሚን፥ ... ልጅ
ሳኡል።”
(ዘፍ 46:10፤ ዘጸ
6:15)
ይሚማ ~ Jemima: ‘የዋህ፣ ሰላማዊ’ ማለት ነው። ከመከራው
በኋላ ለኢዮብ
ከተወለዱለት ሦስት
ሴቶች፥ ትልቋ
ልጅ፥ “የመጀመሪያይቱንም ስም
ይሚማ፥ የሁለተኛይቱንም ስም ቃስያ፥ የሦስተኛይቱንም ... ብሎ ሰየማቸው።” (ኢዮ 42:14)
ይምራ ~ Imrah: ‘ይምር፣ ይቅር
ይል’
ማለት ነው።
ከአሴር ነገድ፥
የጾፋ ቤተሰብ፥
“ሦጋል፥ ቤሪ፥ ይምራ፥
ቤጼር፥ ሆድ፥
ሳማ፥ ሰሊሳ፥
ይትራን፥ ብኤራ
ነበሩ።”
(1 ዜና 7:36)
ይምና ~
Imnah:
ያመነ፣ የታመነ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ዪምና፣ ያሚን፣ ይምና]
Imnah-
‘እሙን’ ከሚለው ቃል የተገኘ
ስም ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1. የኤላ ልጅ፥
(1 ዜና 7: 5)
2.
“የሌዋዊውም የይምና ልጅ የምሥራቁ ደጅ በረኛ ቆሬ የእግዚአብሔርን መባና ...” (2 ዜና 31:14)
3.
የአሴር ልጅ፥
(1 ዜና 7:30)
ይሳኮር ~
Issachar:
‘ስጦታ፣ ካሳ’ ማለት ነው። የያዕቆብ ዘጠነኛ ልጅ፥” ልያም፥ ባሪያዬን ለባሌ ስለ ሰጠሁ እግዚአብሔር ዋጋዬን ሰጠኝ አለች ስሙንም ይሳኮር ብላ ጠራችው”
(ዘፍ 30:18).
ይስሐቅ ~
Isaac:
ይሳቅ፣ ይስሐቅ፣ መሳቅ፣ ፈገግታ ማሳየት፣ ጥርስን መግለጥ... ማለት ነው።
‘ሳቀ’
ከሚለው ግስ
የመጣ ስም ነው። [ትርጉሙ “ይስቃል”
ማለት ነው
/ መቅቃ]
የአብርሃም እና ሣራ ልጅ ፥ “አብርሃምም የተወለደለትን ሣራ የወለደችለትን የልጁን ስም
ይስሐቅ ብሎ
ጠራው።”
(ዘፍ 21፡1-3)
፥ “ሣራም፦ እግዚአብሔር
ሳቅ አድርጎልኛል ይህንንም የሚሰማ ሁሉ በእኔ ምክንያት ይስቃል አለች።” (ዘፍ 21፡6)
ይስማኤላዊ ~ Israelite: እስማኤላውያን፣ የእስራኤል ወገን፣ የያቆብ
ወገኖች፣ የአብርሃም
ልጆች... ማለት ነው።
‘እስማኤል’
ከሚለው ስም
የመጣ የነገድ
ስም ነው።
የእስማኤል ወገን፥ (2 ሳሙ 17፡25)
፣ (1 ዜና 2:17)
ይስዓር ~
Izehar:
‘ግልጽነት’
ማለት ነው። የቀዓት ልጅ፥ “የቀዓትም ልጆች በየወገናቸው እንበረም፥ ይስዓር፥ ኬብሮን፥ ዑዝኤል።”
(ዘኊ 3:19) ይረሕምኤል ~ Jerahmeel: ‘ይምሕረ ኤል፣ መሓሪ አምላክ’ ማለት ነው።
1.
የካሌብ ወንድም፥
የሔዝሮን ልጅ፥ “ለኤስሮም የተወለዱለት ልጆች ይረሕምኤል፥ አራም፥
ካልብ ነበሩ” (1 ዜና 2:9፣25፣26)
2.
የሌዋዊው፥ የቂስ ልጅ፥ “ከቂስ የቂስ ልጅ ይረሕምኤል የሙሲም ልጆች ሞሖሊ፥
ዔዳር፥ ኢያሪሙት” (1 ዜና 24:29)
3.
“ንጉሡም ጸሐፊውን ባሮክንና ነቢዩን ኤርምያስን ይይዙ ዘንድ የንጉሡን ልጅ
ይረሕምኤልንና የዓዝርኤልን
ልጅ ሠራያን
የዓብድኤልንም ልጅ
ሰሌምያን አዘዘ፥
እግዚአብሔር ግን ሰወራቸው” (ኤር 36:26)
ይሩበኣል ~ Jerubbaal: ‘አየረ በዓል’
ማለት ነው።
ጌዴዎን የተጠራበት ስም፥ (መሣ 6:32፥ 7:1፥ 8:29፤ 1 ሳሙ 12:11) “ስለዚህም በዚያ ቀን፦
መሠዊያውን አፍርሶአልና
በኣል ከእርሱ
ጋር ይምዋገት
ብሎ ጌዴዎንን፦
ይሩበኣል ብሎ ጠራው”
ይሩኤል ~
Jeruel:
አየረ ኤል፣ ታላቅ ገዥ፣ ታላቅ አምላክ፣ የሰማዩ ጌታ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ይሪኤል]
‘አየረ’ እና ‘ኤል’
ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ነው።
የቦታ ስም፥ “...
በሸለቆውም መጨረሻ በይሩኤል ምድረ በዳ ...” (2 ዜና 20፡16፣ 20)
ይሪኤል ~
Jeriel: አየረ ኤል፣ ታላቅ ገዥ፣ ታላቅ አምላክ፣ የሰማዩ ጌታ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም-
ይሩኤል]
‘አየረ’ እና ‘ኤል’
ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ነው። የቶላ
ልጅ፥ (1 ዜና 7:2)
ይሪዖት ~
Jerioth:
ከካሌብ ሚስቶች አንዷ፥ “የኤስሮምም ልጅ ካሌብ ከሚስቱ ከዓዙባ ከይሪዖትም ልጆች ወለደ ልጆቹዋም ... ነበሩ።” (1 ዜና 2:18)
ይሬማይ ~ Jeremai: ‘የራማዊ፣ የላይ
ቤት፣ ሰማያዊ’ ማለት
ነው። ከምርኮ
ሲመለሱ፥ እንግዳ
ሴቶችን አግብተው
ከነበሩ እና
ከፈቷቸው፥ የሐሱም
ልጅ፥ “ከሐሱም ልጆችም፤ መትናይ፥
መተታ፥ ዛባድ፥
ኤሊፋላት፥ ይሬማይ፥
ምናሴ፥ ሰሜኢ።” (ዕዝ 10:33)
ይሬምት ~
Jeremoth:
ያረ ሞት፣ አየረ ሞት፣ ታላቅ ሞት፣ ከፍተኛ... ሞት ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ኢያሪሙት፣ ይሬሞት]
‘አየረ’ እና ‘ሞት’
ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:
-
. በሪዓ ልጅ፥ “አሒዮ፥ ሻሻቅ፥ ይሬምት፥” (1 ዜና 8:14)
. የቤላ ልጅ፥ ኢያሪሙት- (1 ዜና 7:7)
የቤኬርም ልጅ፥ ኢያሪሙት- (1 ዜና 7:8)
የኤማን ልጅ፥ ኢያሪሙት - (1
ዜና 25:4)
የሙሲ ልጅ፥ ኢያሪሙት-
(1 ዜና 23:23)
የሔማን ልጅ፥ ኢያሪሙት- (1 ዜና 25:22)
ይሬሞት ~
Jeremoth:
የረ ሞት፣ አየረ ሞት፣ ታላቅ ሞት፣ ከፍተኛ ሞት... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ኢያሪሙት፣ ይሬምት]
‘አየረ’ እና ‘ሞት’
ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። በመጽሐፍ
ቅዱስ ውስጥ
በዚህ ስም
የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
የኤላ ልጅ፥
(ዕዝ 10:26፣ 27)
2.
የዛቱዕ ልጅ፥
(ዕዝ 10:27)
ይርጵኤል ~ Irpeel: ‘የአምላክ ፈውስ’ ማለት ነው። ከብንያም ከተሞች አንዱ። “ሬቄም፥ ይርጵኤል፥ ተርአላ፥ ጼላ፥ ኤሌፍ፥ ኢየሩሳሌም የምትባል የኢያቡስ
ከተማ፥ ቂርያትጊብዓት አሥራ ሦስት ከተሞችና መንደሮቻቸው። የብንያም ልጆች ርስት
በየወገኖቻቸው ይህ
ነበረ”
(ኢያ 18:27)
ይሺያ ~ Ishiah, Ishijah, Isshiab, Jesiah:
የሺህ ያሕ፣ የሺህ ሕያው፣ የብዙዎች ጌታ፣ የሽዎች አምላክ... ማለት ነው።
‘ሺህ’ እና ‘ያሕ’(ያሕዌ ፣ ሕያው) ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:
-
ይሺያ / Ishiah:
የይዝረሕያ ልጅ፥ (1
ዜና 7፡3)
ይሺያ / Ishijah:
በዕዝራ ዘመን እንግዳ ሚስቶችን እንዲፈቱ ከተደረጉት፥ (ዕዝ 10፡31)
ይሺያ / Isshiah:
1.
የረዓብያ ልጅ፥
(1 ዜና 24:21-22)
2.
የሚካ ወንድም፥
(1 ዜና 24:26)
ይሺያ / Jesiah:
የዑዝኤል ልጅ፥ “የዑዝኤል ልጆች አለቃው ሚካ፥ ሁለተኛው ይሺያ ነበሩ”
(1 ዜና 23:20)
1.
የዳዊትን ሠራዊት
በጺቅላግ ከተቀላቀሉ፥ “ቆርያውያን ሕልቃና፥ ይሺያ፥ አዛርኤል፥
ዮዛር፥ ያሾቢአም” (1 ዜና 12:6)
2.
የዑዝኤል ልጅ፥ “የዑዝኤል ልጆች አለቃው ሚካ፥ ሁለተኛው ይሺያ ነበሩ።” (1 ዜና 23:20)
ይሽማ ~
Ishma:
ይሽማ፣ እሽም፣ ስም፣ ዝና... ማለት ነው።
‘ስም’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው።
በይሁዳ የዘር ሐረግ፣ የኤጣ አባት ልጅ፥ (1 ዜና 4፡3)
ይሽማያ ~
Ishmaiah:
ሰማ ያሕ፣ አምላክ ሰማ፣ ሕያው ሰማ... ማለት ነው።
‘ሰማ’
እና ‘ያሕ’
(ያሕዌ ፣
ዋስ)
ከሚሉ ቃላት
የተመሠረተ ስም
ነው። በዳዊት ዘመን በዛብሎን አለቃ የነበረ፣ የአብድዩ ልጅ፥ (1 ዜና 27:
19)
ይሽምራይ ~
Ishmerai:
የሺህ መሪ፣ የሽዎች መሪ፣ የብዙዎች መሪ፣ የሺህ አለቃ፣ የሽዎች ጠባቂ... ማለት ነው።
የበሪዓ ልጅ፥
(1 ዜና 8:18)
ይሽቢብኖብ ~ Ishbi-benob: ‘በኔቦ የተቀመጠ’ ማለት ነው። ከራፋይ ወገን የሆነ፥ ሦስት መቶ ሰቅል ናስ የጦር መሣሪያ የታጠቀ፥ “ከራፋይም ወገን የነበረው ይሽቢብኖብ ዳዊትን ይገድል ዘንድ አሰበ ...አዲስም የጦር መሣሪያ ታጥቆ
ነበር።”
(2 ሳሙ 21:16፣17)
ይሽባ ~
Ishbah:
የሺህ አባ፣ የሺህ አባት፣ የብዙዎች ጌታ፣ ታላቅ አባት፣ የተከበረ... ማለት ነው።
የኤሽትምዓ አባት፣ የዬቴር ልጅ፥ (1
ዜና 4፡17)
ይሽዒ ~
Ishi:
የሺህ፣ የሺ፣ ሺህ፣ ብዙ ሀብት ማለት ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
የሶሳን አባት፣ የአፋይም ልጅ፥ (1
ዜና 2:31)
2.
የዞሔት አባት፥
(1 ዜና 4:20)
3.
ከስምዖን ልጆች
አለቆች፥ (1 ዜና 4:42)
4.
ከምናሴ ነገድ
አለቆች፥ (1 ዜና 5:24)
ይሽጳ ~
Ispah:
‘በራ’ ማለት ነው። ከብንያም ወገን፥ የበሪዓውያን አለቃ፥ “ዝባድያ፥ ዓራድ፥ ዔድር፥ ሚካኤል፥ ይሽጳ፥ ዮሐ፥ የበሪዓ ልጆች” (1 ዜና 8:16)
ይቀብጽኤል ~ Jekabzeel:
ያቅብ ዘኤል፣ በአምላክ የተጠበቀ፣ ለእግዚአብሔር የተለየ... ማለትነው።
Jekabzeel- ‘ያቅብ’
፣ ‘ዘ’ እና ‘ኤል’
ከሚሉ ሦስት ቃላት የተመሠረተ ነው። በይሁዳ በስተደቡብ የነበረ ከተማ፥ (ነህ 11፡25)
ይቁቲኤል ~ Jekuthiel:
‘ያምላክ ተስፈኞች’
ማለት ነው።
በይሁዳ የዘር
ሐረግ የተጠቀሰ፥
“አይሁዳዊቱም ሚስቱ የጌዶርን
አባት ዬሬድን፥
የሦኮንም አባት
ሔቤርን፥ የዛኖዋንም አባት ይቁቲኤልን ወለደች ...” (1 ዜና 4:18)
ይቃምያ ~ Jecamiah:
ያቆም ያሕ፣ በሕያው የቆመ፣ በእግዚአብሔር የተመሠረተ... ማለት ነው።
‘ያቆመ’
እና ‘ያሕ’ (ያሕዌ፣
ሕያው)
ከሚሉ ቃላት
የተመሠረተ ስም
ነው። የምርኮኛው የኢኮንያን ልጅ፥ “ፈዳያ፥ ሼናጻር፥ ይቃምያ፥ ሆሻማ፥ ነዳብያ ነበሩ።”
(1 ዜና 3:8)
ይቅምዓም ~
Jakamean:
ያቀመን፣ ያቆም፣ ያስነሳ፣ ያጸና... ማለት ነው። የኬብሮን ልጅ፥ (1
ዜና 23:19)
ይብለዓም ~
Ibleam: ‘የብሉይ ሰዎች፣ የጥንት ሰዎች’
ማለት ነው።
የምናሴ ከተማና
የመንደሩ ሰዎች፥
“ምናሴም የቤትሳንንና የመንደሮችዋን፥ የታዕናክንና የመንደሮችዋን፥ የዶርንና
የመንደሮችዋን፥ የይብለዓምንና የመንደሮችዋን፥ የመጊዶንና የመንደሮችዋን ሰዎች አላወጣቸውም ነገር ግን ከነዓናውያን በዚያ አገር በመቀመጥ
ጸኑ።”
(መሣ 1:27)
ይብሣም ~ Jibsam: ‘አስደሳች’
ማለት ነው።
የይሳኮር ወገን፥
የቶላ ልጅ፥
“የቶላም ልጆች፥ ኦዚ፥ ራፋያ፥ ይሪኤል፥ የሕማይ፥ ይብሣም፥ ሽሙኤል፥ የአባታቸው የቶላ
ቤት አለቆች፥
በትውልዳቸው ጽኑዓን
ኃያላን ሰዎች
ነበሩ በዳዊት
ዘመን ቍጥራቸው ሀያ ሁለት ሺህ ስድስት መቶ ነበረ።” (1 ዜና 7:2)
ይትላ ~
Jethlah:
‘ቆጥ፣ ሰገነት’
ማለት ነው። በዳን ግዛት ዳርቻ የነበረ ከተማ፥ “ሸዕለቢን፥
ኤሎን፥ ይትላ፥
ኤሎን፥ ተምና፥” (ኢያ 19:42)
ይትማ ~
Ithmah:
‘ጽኑ’ ማለት ነው። ከዳዊት ኃያላን አንዱ፥ “መሐዋዊው ኤሊኤል፥
ይሪባይ፥ ዮሻዊያ፥
የኤልናዓም ልጆች፥
ሞዓባዊው ይትማ፥” (1 ዜና
11:46)
ይትረኃም ~ Ithream:
‘ብዙ ሕዝብ፣ የተትረፈረፈ’ ማለት ነው። ስድስተኛው፥
የዳዊት ልጆች፥
በኬብሮን ከተወለዱ፥
“ስድስተኛውም የዳዊት ልጅ
ሚስት የዔግላ
ልጅ ይትረኃም ነበረ ...”
(2 ሳሙ 3:5፤ 1 ዜና 3:3)
ይትራን ~ Ithran:
የተከበረ ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም-
ዮቶር] በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
የዲሶን ልጅ፥ (ዘፍ 36፡26) ፣ (1
ዜና 1:41)
2.
ከአሴር ነገድ፣ የጾፋ ልጅ፥ (1 ዜና 7:30-40)
ይዑኤል ~
Jeiel, Jeuel: የኤል፣ የአምላክ፣ የጌታ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ይሒኤል፣ ይዒኤል]
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ይዑኤል / Jeiel:
የአዶኒቃ ልጅ፥ (ዕዝ 8:13)
ይዑኤል / Jeuel:
የዛራ ልጅ፥ (1
ዜና 9፡6)
ይዒኤል ~
Jehiel:
ያሕ ኤል፣ ሕያው አምላክ፣ ዘላለማዊ ጌታ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ይሒኤል፣ ይዑኤል]
‘ያሕ’ እና ‘ኤል’
ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
የሚስቱ ስም መዓካ የነበረው የገባዖን አባት ይዒኤል፥ (1 ዜና 9፡35)
2.
የአሮኤራዊው የኮታ
ልጅ፥ (1 ዜና 11:44)
3.
የኤሊጸፋን ልጅ፥
(2 ዜና 29:14)
4.
ለፋሲካ መሥዋዕት እንዲሆን ካቀረቡ፥ (2 ዜና 35:8፣ 9)
ይዓሪም ~
Jearim:
‘ጫካ’
ማለት ነው። በይሁዳ ድንበር ላይ ያለ ተራራ፥ “ድንበሩም ከበኣላ በምዕራብ በኩል ወደ ሴይር ተራራ ዞረ ክሳሎን ወደምትባል ወደ ይዓሪም ተራራ ወገን በሰሜን በኩል አለፈ ወደ ቤትሳሚስ ...”
(ኢያ 15:10)
ይኮልያ ~ Jecholiah, Jecoliah: የቃለ ያሕ፣ የአምላክ ቃል፣ ቃለ ሕይወት፣ ሕገ እግዚአብሔር ማለትነው።
‘የቃለ’ እና ‘ያሕ’(ሕያው)
ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
ይኮልያ / Jecholiah: የንጉሡ የዖዝያ እናት፥ (2
ነገ 15:2)
ይኮልያ / Jecoliah:
(2 ዜና 26፡3)
ይዝረሕያ ~ Izrahiah, Jezrahiah:
እዝር ያሕ፣ የሕያው ዘር፣ የጌታ ወገን፣ የአምላክ ቤተሰብ... ማለት ነው።
‘ዘረ’ እና ‘ያሕ’(ሕያው ፣ ያሕዌ) ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ይዝረሕያ / Izrahiah: የኦዚ ልጅ፥ (1 ዜና 7፡3)
ይዝረሕያ / Jezrahiah: በነህምያ ዘመን፣ የመዘምራኑ አለቃ፥ (ነህ 12፡42)
ይዝረሕያ ~
Jezrahiah:
‘የዘረ ያሕ፣ የሕያው ዘር’ ማለት ነው። በነህምያ ዘመን ለኢየሩሳሌም
ቅጥር ጥገና
በተረገ ክብረ
በዓል ከዘመሩ፥
“ዘካርያስ፥ ሐናንያ መለከት
ይዘው፥ መዕሤያ፥
ሸማያ፥ ... ዘመሩ፥
አለቃቸውም ይዝረሕያ ነበረ።” (ነህ 12:42)
ይዝራዊ ~ Izrahite: ዕዝራያት፣ ዕዘራውያን፣ የዕዝራ
ወገኖች... ማለት ነው።
“ለአምስተኛው ወር አምስተኛው
አለቃ ይዝራዊው
ሸምሁት ነበረ
በእርሱም ክፍል
ሀያ አራት ሺህ ጭፍራ ነበረ።” (1 ዜና 27፡8)
ይዝኤል ~
Jeziel:
እዝ ኤል፣ የአምላክ እዝ፣ ሕዝበ እግዚአብሔር፣ የጌታ ታዛዥ... ማለት ነው።
‘ያዝ’
እና ‘ኤል’
ከሚሉ ቃላት
የተመሠረተ ስም
ነው። የዳዊትን ሠራዊት የተቀላቀለ፣ የሸማዓ ልጅ፥ (1 ዜና 12፡3)
ይዝያ ~
Jeziah:
‘ያዚ ያሕ፣ የሕያው ዘር’ ማለት ነው። ከምርኮ ከተመለሱ፥ እንግዳ
ሚስቶችን ካገቡ፥
የፋሮስ ልጅ፥
“ከእስራኤልም ከፋሮስ ልጆች፤
ራምያ፥ ይዝያ፥
መልክያ፥ ሚያሚን፥
አልዓዛር፥ መልክያ፥
በናያስ”
(ዕዝ 10:25)
ይዲኤል ~ Jediael: ‘በአምላክ የታወቀ’ ማለት ነው።
1.
የብንያም ልጅ፥ ያባቶች ቤት አለቃ፥ “የብንያም ልጆች ቤላ፥ ቤኬር፥
ይዲኤል ሦስት
ነበሩ።”
(1 ዜና 7:6፣11)
2.
የሌዋዊው፥ የሜሱላም ሁለተኛ ልጅ፣ “ሜሱላም ልጆች ነበሩት በኵሩ ዘካርያስ፥ ሁለተኛው ይዲኤል፥ ሦስተኛው ዮዛባት” (1 ዜና 26:1፣2)
3.
ከዳዊት ኃያላን አንዱ፥ የሽምሪ ልጅ፥ ይድኤል፥ “የሽምሪ ልጅ ይድኤል፥ ወንድሙም
ይድኤል፥ ወንድሙም
ቲዳዊው ዮሐ፥” (1 ዜና
11:45)
4.
“ወደ ጺቅላግም ሲሄድ ከምናሴ ወገን የምናሴ ሻለቆች የነበሩ ዓድና፥ ዮዛባት፥ ይዲኤል፥ ሚካኤል፥ ... እርሱ ከዱ።” (1 ዜና 12:20)
ይዲዳ ~ Jedidah: የውድ፣ የተወደደ፣ ለአምላክ የቀረበ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ዩዳሄ፣ ዮዳሄ፣ ያሕዳይ፣ ያዱአ፣ ያዳ፣ ያዳይ፣ ዬሕድያ፣ ዬዳይ፣ ይሆዓዳ፣ ይዲድያ፣ ዮአዳ፣ ዮዓዳን፣ ዮዳሄ]
‘ይወድድ’
ከሚል ቃል
የተገኘ ስም
ነው። የኢዮስያስ እናት፣ የአዳያ ልጅ፥ (2
ነገ 22:1)
ይዲድያ ~ Jedidiah: ያሕ ውድ፣ የሕያው ወዳጅ፣ በጌታ የተወደደ፣ ለአምላክ የቀረበ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ዩዳሄ፣ ዮዳሄ፣ ያሕዳይ፣ ያዱአ፣ ያዳ፣ ዬዳይ፣ ይሆዓዳ፣ ይዲዳ፣ ዮአዳ፣ ዮዓዳን፣ ዮዳሄ]
‘ይወድድ’ እና ‘ያሕ’(ያሕዌ)
ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
እግዚአብሔር የንጉሥ ዳዊትን ልጅ፣ ሰሎሞንን፣ የጠራበት ስም፥ “ደግሞም በነቢዩ በናታን እጅ ልኮ ስሙን ስለ እግዚአብሔር ይዲድያ ብሎ ጠራው።” (2 ሳሙ 12፡ 25)
ይዳላ ~ Idalah:
‘ዕድለ ያሕ፣ የአምላክ መታሰቢያ’ ማለት
ነው። ከዛብሎን
ከተሞች አንዱ፥
“ቀጣት፥ ነህላል፥
ሺምሮን፥ ይዳላ፥ ቤተ
ልሔም አሥራ
ሁለት ከተሞችና
መንደሮቻቸው።” (ኢያ
19:15)
ይዳያ ~ Jedaiah: ‘ውደ ያሕ፣ ሕያውን ወደድ፣ አምላክን ማመስገን’ ማለት ነው።
1.
የስምዖንውያን አለቃ፥ የሺምሪ ልጅ፥ “የሺፊ ልጅ ዚዛ፥ የአሎን ልጅ የይዳያ ልጅ የሺምሪ ልጅ የሸማያ ልጅ” (1 ዜና 4:37)
2.
ከባቢሎን ምርኮ
መልስ፥ የኢየሩሳሌምን ቅጥር በመጠገን ከተባበሩ፥ “በአጠገባቸውም የኤርማፍ ልጅ ይዳያ በቤቱ አንጻር ያለውን አደሰ። በአጠገቡም
የአሰበንያ ልጅ
ሐጡስ አደሰ።” (ነህ 3:10)
3.
ከካህናቱ ምድብ፥ የአንዱ አለቃ፥ ዮዳኤ፥ “መጀመሪያውም ዕጣ ለዮአሪብ ወጣ፥
ሁለተኛው ለዮዳኤ” (1 ዜና 24:7)
4.
ዮዳሄ፥ “ከካህናቱም ዮዳሄ፥ ዮአሪብ፥ ያኪን” (1 ዜና 9:10)
ይድባሽ ~
Idbash:
‘ጀግና’
ማለት ነው። ከይሁዳ ወገን፥ የኤጣም ልጅ፥ “እነዚህም የኤጣም
አባት ልጆች
ናቸው ኢይዝራኤል፥
ይሽማ፥ ይድባሽ፥
እኅታቸውም ሃጽሌልፎኒ።” (1 ዜና 4:3)
ይጋር ሠሀዱታ ~ Jegar-sahadutha: ‘የቃል ኪዳን ምልክት፣ የምስክር ሐውልት’ ማለት ነው። የያቆብ አማት፥ ላባ በእሱና በያዕቆብ መካከል ለተደረገ ቃልኪዳን፥ መታሰቢያ እንዲሆን ያስቀመጠው የድንጋይ ክምር፥ “ላባም ይጋር ሠሀዱታ ብሎ ጠራት ያዕቆብም ገለዓድ አላት።” (ዘፍ 31:47)
ይግአል ~ Igal: ‘መርገም፥ አምላካዊ ቅጣት’
ማለት ነው።
1.
የይሳኮር ወገን የሆነ፥ ከሰላዮች አንዱ፥ የዮሴፍ ልጅ፥ “ከይሳኮር ነገድ የዮሴፍ ልጅ
ይግአል”
(ዘኊ 13:7)
2.
“የሱባ ሰው
የናታን ልጅ
ይግዓል፥ ጋዳዊው”
(2 ሳሙ 23:36)
ይግኣል ~ Igeal: ‘በቀል፣ ቅጣት’ ማለት ነው። ከይሁዳ
ንጉሣዊ ወገን፥
የነህምያ ልጅ፥ “የሴኬንያም ልጅ ሸማያ ነበረ። የሸማያም ልጆች ሐጡስ፥ ይግኣል፥ ባርያሕ፥
ነዓርያ፥ ሻፋጥ
ስድስት ነበሩ።” (1 ዜና 3:22)
ይጽሐር ~
Jezoar:
የሔላ ልጅ፥ ከአሴር ሚስቶች አንዷ፥ “የሔላም ልጆች ዴሬት፥ ይጽሐር፥ ኤትናን ናቸው።” (1 ዜና 4:7)
ይጽሪ ~ Izri:
ይዝሬ፣ ዘሬ፣ ወገኔ... ማለት ነው።
በእግዚአብሔር ቤት በጸናጽልና በበገና በመሰንቆም ይዘምሩ፥ በእግዚአብሔርም ቤት ያገለግሉ
ከነበሩ፥ (1 ዜና 25፡11)
ይፍታሕ ~
Jiphtah:
ይፍታሕ፣ የተፈታ፣ ያልታሰረ፣ የተለቀቀ፣ የተስፋፋ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ኤፍታህ፣ ያፌት፣ ይፍታሕኤል፣ ዮፍታሔ፣ ፈታያ] ከይሁዳ ነገድ ከተሞች፥ የቦታ ስም፥ (ኢያ 15፡43)
ይፍታሕኤል ~ Jiphthahel: ይፍታህ ኤል፣ በጌታ የተፈታ፣ በአምላክ ነጻ የወጣ፣ እግዚአብሔር የማረው... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ኤፍታህ፣ ያፌት፣ ይፍታሕ፣ ዮፍታሔ፣ ፈታያ]
‘ይፍታህ’
እና ’ኤል’
ከሚሉ ሁለት
ቃላት የተመሠረተ
የቦታ ስም
ነው። ዛብሎን እና የአሴር ልጆች በየወገኖቻቸው የርስታቸው ድንበር፥ (ኢያ 19፡14)
ይፍዴያ ~ Iphedeiah: ‘ሕያው የፈታው፣ አምላክ ነጻ ያወጣው’ ማለት
ነው። ከብንያም ነገድ፥ ከሻሻቅ ልጆች አንዱ፥ “ሐናን፥ ሐናንያ፥ ኤላም፥ ዓንቶትያ፥ ይፍዴያ፥
ፋኑኤል፥ የሶሴቅ
ልጆች”
(1 ዜና 8:25)
ዮሐ ~
Joha:
ዬሃ፣ የሕያው፣ የዘለዓለም፣ አምላካዊ... ማለት ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
የብንያማዊው የበሪዓ
ልጅ፥ (1 ዜና 8:16)
2.
ከዳዊት ወታደሮች
አንዱ፥ (1 ዜና 11:45)
ዮሐና ~
Joanna:
የሐና፣ ጸጋ፣ ለጌታ የሆነ፣ ለአምላክ የተሰጠ፣ እግዚአብሔር የማረው... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- የዮና]
‘የሐና’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው። በዚህ ስም የሚታወቁ ሁለት ሰዎች አሉ።
. የሄሮድስ አዛዥ የኩዛ ሚስት፥ ዮሐና፥ (ሉቃ 8:3) ፣ (ሉቃ 24:10)
. በጌታ
የዘር ሐረግ፣
የሬስ ልጅ
የዮናን፥ (ሉቃ 3፡27)
ዮሐናን ~
Johanan:
የሐናን፣ ያሕ አናን፣ የጌታ የሆነ፣ የሕያው በረከት... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም-
ይሆሐናን]
‘ያሕ’ (ያሕዌ)
እና ‘ሐናን’ (አናን)
ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። [ትርጉሙ “እግዚአብሔር ጸጋ
ሰጭ ነው” ማለት
ነው / መቅቃ]
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
ከጋድ ልጆች የጭፍራ አለቆች ዳዊት ወደነበረባት ወደ አምባይቱ ከመጡ፣ የሜሱላም
ልጅ፥ (1 ዜና 12:12)
2.
የዓዛርያስ ልጅ፥ የዓዛርያስ አባት፥ (1 ዜና 6:9፣ 10)
፣ (2 ዜና 28:12)
3.
የኤልዮዔናይ ልጅ፥
(1 ዜና 3:24)
4.
የቃሬያ ልጅ፥
(ኤር 41:11-16)
5.
የኢዮስያስ ልጅ፥
(1 ዜና 3:15)
6.
ዳዊት ከሳኦል ሸሽቶ ወደ ነበረባት ወደ አምባይቱ ከመጡ፥ (1 ዜና 12:4)
7.
ከኤፍሬም ልጆች
አለቆች፥ (2 ዜና 28:12)
8.
ከዕዝራ ጋር
ከግዞት ከተመለሱ፣
የሃቃጣን ልጅ፥
(ዕዝ 8:12)
9.
ከሌዋውያን አለቆች አንዱ፣ የኤልያሴብ ልጅ፥ (ነህ 12:23)
. ይሆሐናን- (ነህ 6:18)
ዮሐንስ ~
John:
የሕያዋን ዋስ፣ የሕያዋንዋስ ፣ ሕያው ዋስ፣ ዘላለማዊ አዳኝ... ማለት ነው።
‘ሕያው’
እና ‘ዋስ’
ከሚሉ ቃላት
የተመሠረተ ስም
ነው። [ትርጉሙ “እግዚአብሔር ጸጋ ነው” ማለት ነው / መቅቃ]
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1.
መጥምቁ ዮሐንስ፥
(ማቴ 3:1-2)
2.
የዘብዴዎስ ልጅ የያዕቆብ ወንድም፣ ሐዋርያው ዮሐንስ፥ (ማር 1:19)
3.
“በነገውም አለቆቻቸውና ሽማግሌዎች ጻፎችም ሊቀ ካህናቱ ሐናም ቀያፋም
ዮሐንስም እስክንድሮስም
የሊቀ ካህናቱም
ዘመዶች የነበሩት
ሁሉ በኢየሩሳሌም
ተሰበሰቡ”
(ሥራ 4:6) ፣ (ሥራ 6:6)
4.የሐዋርያው የማርቆስ ሌላ ስም፥ “...ማርቆስ ወደ ተባለው ወደ ዮሐንስ እናት ወደ ማርያም ቤት መጣ።” (ሥራ 12:12፣ 25፣ 13:5፣ 13፣ 15:37)
ዮሲፍያ ~
Josiphiah:
ያሰፍ ያሕ፣ ሕያው ያስፋ፣ አምላክ ያስፋፋው፣ እግዚአብሔር ያበዛው… ማለት ነው።
‘ያስፋ’ እና ‘ያሕ’ (ሕያው) ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። ከዕዝራ ጋር ከግዞት ከተመለሱ፣ የሰሎሚት ልጅ፥ (ዕዝ 8:10)
ዮሳ ~
Joses:
የሺህ፣ ብዙ ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም-
ዮሴዕ]
. የጌታ ወንድም ተብሎ የተጠራ፥ “ይህ የጸራቢ ልጅ አይደለምን? እናቱስ ማርያም ትባል የለምን? ወንድሞቹስ
ያዕቆብና ዮሳ ስምዖንም ይሁዳም አይደሉምን?” (ማቴ
13:55፣ ማር 6:3)
. ዮሴዕ - (ሉቃ 3:29)
ዮሳቤት ~
Jehosheba:
ያሕ ሳባ፣ ያሕ ሰብ፣ የጌታ ሰው፣ ሕያው ሰው፣ የቃል ኪዳን ልጅ… ማለት ነው።
Jehosheba- ‘ያሕ’
(ሕያው) እና ‘ሳባ’
ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
የንጉሡ የኢዮራም ልጅ፥ የአካዝያስ እኅት ዮሳቤት፥ (2 ነገ 11፡2)
ዮሴዕ ~
Jose:
የሺህ፣ የብዙ… ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም-
ዮሳ]
. በጌታ የዘር የተጠቀሰ፥ የኤልዓዘር ልጅ ዮሴዕ፥ (ሉቃ 3:29)
. ዮሳ -
(ማቴ 13:55፣ ማር 6:3)
ዮሴፍ ~
Joses, Joseph: ያስፋ፣ ዘርን ያብዛ፣ ወገንን ያበርክት፣ ይስፋፋ… ማለት ነው።
‘ሰፋ’
ከሚለው ግስ
የመጣ ስም ነው።
[ትርጉሙ “ይጨምር”
ማለት ነው
/ መቅቃ]
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ዮሴፍ / Joses: ትውልዱ የቆጵሮስ ሰው የነበረ አንድ ሌዋዊ፥ ባርናባስ
በመባል የሚታወቀው፥
(ሥራ 4:36)
ዮሴፍ / Joseph:
1.
የያቆብ ልጅ፥ “ስሙንም። እግዚአብሔር ሁለተኛ ወንድ ልጅን ይጨምርልኝ ስትል ዮሴፍ ብላ ጠራችው” (ዘፍ 30:23፣ 24)
2.
ምድሪቱን ይሰልሉ ዘንድ ሙሴ ከላካቸው የይግአል ልጅ፥ (ዘኁ 13:7)
3.
እንግዶቹን ሚስቶች አግብተው ከነበሩ፥ (ዕዝ 10: 41፣42)
4.
በነህምያ ዘመን
ከግዞት ከተመለሱ፥
(ነህ 12:14፣15)
5.
በጌታ የዘር ሐረግ የተጠቀሰ፥ (ሉቃ 3:30)
6.
ሌላ በጌታ የዘር ሐረግ የተጠቀሰ፥ የዮዳ ልጅ፥ (ሉቃ 3:26)
7.
ሌላ በጌታ የዘር ሐረግ የተጠቀሰ፥ የማታትዩ ልጅ፥ (ሉቃ 3:25)
8.
የማርያም እጮኛ፥
(ሉቃ 3:23)
9.
ወደ ጲላጦስ ቀርቦ የኢየሱስን ሥጋ የለመነ እና የቀበረ፥ (ሉቃ 23:50)
10.
በርስያን የተባለው፥
(ሥራ 1:23)
ዮስካ ~ Iscah: ‘ቀጣይ፣ የወደፊቱን
የሚያይ፣ አስተዋይ’
ማለት ነው።
የአብርሃም ወንድም፣
የናኮር ልጅ፥
የሚልካ እኅት
፥ “አብራምና ናኮርም
ሚስቶችን አገቡ
የአብራም ሚስት ስምዋ ሦራ ነው የናኮር ሚስት የሐራን ልጅ ሚልካ ናት። ሐራንም የሚልካና
የዮስካ አባት
ነው።”
(ዘፍ 11:29)
ዮራ ~
Jorah:
‘የበልግ ዝናብ’ ማለት ነው። ከግዞት ከተመለሱ፥ የዩራ ልጆች ይገኙበታል፥ “የዮራ ልጆች፥ መቶ አሥራ ሁለት” (ዕዝ 2:18)
ዮራም ~
Jorim:
‘የራማ፣ ከፍተኛ፣ የተከበረ’ ማለት ነው። በጌታ የዘር ሐረግ፥ የማጣት ልጅ፥ “የዮሴዕ ልጅ፥
የኤልዓዘር ልጅ
የዮራም ልጅ፥
የማጣት ልጅ፥
የሌዊ ልጅ፥” (ሉቃ
3:29)
ዮርማሮዴቅ ~ Evil-merodach: ‘ክፉ መርዶ፣ መጥፎ
ዜና’
ማለት ነው።
የንጉሥ ናቡከደነፆር
ልጅና አልጋ
ወራሽ፥ “እንዲህም ... የባቢሎን
ንጉሥ ዮርማሮዴቅ በነገሠ በአንደኛው ዓመት የይሁዳ ንጉሥ ዮአኪንን ከወህኒ አወጣው”
(2 ነገ 25:27 ኤር 52:31፣34)
ዮርዳኖስ ~
Jordan:
ይወርድ ዳኝ፣ የወርደነ ዋስ፣ ከላይ የወረደ ዋስ፣ ከላይ የመጣ አዳኝ፣ ከላይ የመጣ ዳኛ… ማለት ነው።
‘ወረደ’
ከሚለው ግስ
የተገኘ ስም ነው።
[ወራጅ ማለት
ነው / መቅቃ]
. የፍልስጥኤም አገር
ወንዝ፥ (ዘፍ 13:10)
. “ያን ጊዜ ኢየሩሳሌም ይሁዳም ሁሉ በዮርዳኖስም ዙሪያ ያለ አገር ሁሉ ወደ
እርሱ ይወጡ ነበር” (ማቴ 3:5)
ዮሻብሒሴድ ~ Jushabhesed: ‘መኖሪያ ቦታ’ ማለት ነው። የዘሩባቤል ልጅ፥ “ሐሹባ፥ ኦሄል፥ በራክያ፥ ሐሳድያ፥ ዮሻብሒሴድ አምስት ናቸው” (1 ዜና 3:20)
ዮሻዊያ ~ Joshaviah: ‘ህይወት ሰጪ’ ማለት ነው። ከዳዊት ዘበኞች አንዱ፥ “መሐዋዊው ኤሊኤል፥ ይሪባይ፥ ዮሻዊያ፥ የኤልናዓም ልጆች፥ ሞዓባዊው ይትማ፥”
(1 ዜና 11:46)
ዮቂም ~
Jokim:
ያሕ ቁም፣ አምላክ ያቆመው፣ በጌታ የጸና፣ ብርቱ… ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ቀሙኤል፣ ቁሚ፣ አኪቃም፣ አዶኒቃም፣ ኢዮአቄም፣ ዓዝሪቃም፣ ኤልያቄም፣ ያቂም፣ ዮአቂም]
‘ቆመ’
ከሚለው ግስ
የተገኘ ስም ነው።
ከይሁዳ ነገድ፣ ከአሽቤዓ ቤት የሴሎ ልጅ፥ (1
ዜና 4:22)
ዮቅምዓም ~
Jokmeam:
ዮቂም፣ ቁም፣ ያቆመው፣ የጸና፣ ብርቱ… ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም-
ዮቂም]
‘የቆመ’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው።
በተራራማው በኤፍሬም
አገር ካሉት
የመማፀኛ ከተሞች፥
(1 ዜና 6:68)
ዮቅሳን ~ Jokshan: አብርሃም
ከኬጡራ ከወለዳቸው ልጆች አንዱ፥ “እርስዋም ዘምራንን፥ ዮቅሳንን፥ ሜዳንን፥ ምድያምን፥ የስቦቅን፥ ስዌሕን ወለደችለት።” (ዘፍ 25:2፣3፤ 1 ዜና 1:32)
ዮቅንዓም ~
Jokneam:
ያቀንያም፣ አምላክ ያቀናው፣ አምላክ ያቆመው፣ በጌታ የተሠራ… ማለት ነው።
‘የቀና’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው።
ለዛብሎን ልጆች
በየወገኖቻቸው ከወጣ
የርስታቸው ድንበር፥
(ኢያ 19:11)
ዮቅድዓም ~ Jokdeam: ያቀድም፣
የቀደመ፣ ቀዳማዊ፣ ጥንታዊ… ማለት ነው። በይሁዳ
ተራሮች ላይ የነበረ ከተማ፥ “ዮቅድዓም፥ ዛኖዋሕ፥ ቃይን፥ ጊብዓ፥ ተምና አሥር ከተሞችና
መንደሮቻቸው።”
(ኢያ 15:57)
ዮቅጣን ~ Joktan: ቅንጣት፣
ትንሽ፣ ቀጭን… ማለት
ነው። ከዔቦር
ሁለት ልጆች አንዱ፥ “ለዔቦርም ሁለት ልጆች ተወለዱለት የአንደኛው ስሙ ፋሌቅ ነው፥ ... የወንድሙም ስም ዮቅጣን ነው” (ዘፍ 10:25፤ 1
ዜና 1:19)
ዮብ ~
Job:
ያብ፣ ኢዮብ፣ የአብ፣ የእግዚአብሔር ሰው፣ የአምላክ የሆነ… ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ኢዮብ፣ ያሱብ ሺምሮ]
‘አብ’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው።
. የይሳኮር ልጅ፥ “የይሳኮርም ልጆች ቶላ፥ ፉዋ፥ ዮብ፥ ሺምሮን” (ዘፍ 46፡13)
. ኢዮብ-
(ሕዝ 14:14፣ 20)
፣ ያሱብ ሺምሮ- (1 ዜና 7:1)
ዮቶር ~ Jether, Jethro:
ክቡር፣ ግርማዊ… ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ዬቴር] የሙሴ አማት፥ ካህኑ ዮቶር፥ “ሙሴም ሄደ፥ ወደ አማቱ ወደ ዮቶር ተመለሰ...” (ዘጸ 4:18፣ 18:1)
ዮና ~
Jona:
ዋና፣ ዋኖስ፣ ርግብ፣ ትሑት፣ ቅን ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ዮናስ]
[ትርጉሙ “ርግብ”
ማለት ነው
/ መቅቃ]
የስምዖን አባት፥ “ወደ ኢየሱስም አመጣው። ኢየሱስም ተመልክቶ። አንተ የዮና ልጅ ስምዖን
ነህ፤ አንተ
ኬፋ ትባላለህ
አለው፤ ትርጓሜው
ጴጥሮስ ማለት
ነው።”
(ዮሐ 1:42፣ 43)
ዮና ልጅ ~ Bar-jona: በር ዮና፣ የዮና ልጅ፣ የየዋሁ ልጅ… ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ዮና፣ ዮናስ]
Bar-jona- ‘በር’
(ቤት ፣ ልጅ) እና ‘ዮና’
ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
. ሐዋርያው
ጴጥሮስ፥ (ማቴ 16፡17)
. “ወደ ኢየሱስም አመጣው። ኢየሱስም ተመልክቶ። አንተ የዮና ልጅ ስምዖን ነህ...” (ዮሐ 1:42)
ዮና ~ Janna: ‘ፍካት’
ማለት ነው።
በጌታ የዘር
ሐረግ፥ የዮሴፍ
ልጅ፥ የመልኪ አባት፥ “የዮና ልጅ፥ የዮሴፍ ልጅ፥ የማታትዩ ልጅ፥ የአሞጽ ልጅ፥ የናሆም ልጅ፥
የኤሲሊም ልጅ” (ሉቃ 3:25)
ዮናስ ~
Jonah, Jonas: ዋኖስ፣ ርግብ፣ የዋህ፣ ትሑት፣ ቅን… ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ዮና]
[ትርጉሙ “ርግብ”
ማለት ነው
/ መቅቃ]
ዮናስ / Jonah: የአማቴ ልጅ፥ ነቢዩ ወደ ዮናስ፥ (2 ነገ 14:25-27) ፣ (ዮናስ 1:1)
ዮናስ / Jonas: ነቢዩ ዮናስ፥ (ማቴ 12:39፣ 40፣ 41...)
ዮናታን ~ Jehonathan, Jonathan: ያሕ ናታን፣ ዮናታን፣ የአምላክ ስጦታ፣ የሕያው ሀብት… ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም-
ዮናትን] ‘ያሕ’(ያሕዌ) እና ‘ናታን’ ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
[ትርጉሙ “እግዚአብሔር ሰጥቷል”
ማለት ነው /
መቅቃ]
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ዮናታን /
Jehonathan:
. በንጉሥ ዳዊት ልዩ ልዩ መዝገቦች ላይ የተሾመ፣ የዖዝያ ልጅ፥ (1 ዜና
27፡25)
. በዮአቂም ዘመን ከአባቶች ቤቶች አለቆች፣ ካህን፥ “ፈልጣይ፥ ከቢልጋ ሳሙስ፥
ከሸማያ ዮናታን” (ነህ 12:18)
ዮናታን /
Jonathan:
1.
ከሙሴ ወገን፣ የጌርሳም ልጅ፥ (መሣ 18:30)
2.
የአብያታር ልጅ ዮናታን፥ (2
ሳሙ1:23)
፣ (2
ሳሙ15:36፣ 17:15-
21)
፣ (1 ነገ 1:42፣ 43)
3.
የዳዊት ወታደር፣
የአሳን ልጅ፥
(2 ሳሙ 23:32፣33)
4.
የሻጌ ልጅ፥
(1 ዜና 11:34)
5.
ከዓዲ ልጅ፥
(ዕዝ 8:6)
6.
በዕዝራ ዘመን
የነበረ ካህን፣
የአሣሄል ልጅ፥
(ዕዝ 10:15)
7.
በዮአቂም ዘመን ከአባቶች ቤቶች አለቆች፥ ከመሉኪ ወገን፥ (ነህ
12:14)
8.
የቃሬያ ልጅ፥
(ኤር 40:8)
9.
የዮአዳ ልጅ፥ (ነህ 12:11፣ 22፣ 23)
10.
በቅጥሩ የእድሳት በዓል ላይ ጥሩንባ የሚነፋ፣ የሸማያ ልጅ፥ (ነህ
12:35)
ዮናትን ~
Jehonathan:
ያሕ ናታን፣ ዮናታን፣ ያምላክ ስጦታ፣ የሕያው ሀብት… ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ዮናታን]
‘ያሕ’(ያሕዌ) እና ‘ናታን’
ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
በንጉሥ ኢዮሳፍጥ ዘመን የሕጉን መጽሐፍ ይዘው በይሁዳ ያስተምሩ ከነበሩ፥ (2 ዜና 17:8)
ዮናን ~ Joanna, Jonan:
ያሐናን፣ ጸጋ፣ ከጌታ የሆነ፣ ከአምላክ የተሰጠ፣ እግዚአብሔር የማረው… ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም-
ዮሐና]
‘የሐና’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ነው።
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
ዮናን / Joanna:
በጌታ የዘር ሐረግ የተጠቀሰ፣ የሬስ ልጅ፥ (ሉቃ 3፡ 27)
. የኩዛ ሚስት፥ ዮሐና- (ሉቃ 8:3) ፣ ዮሐና- (ሉቃ 24:10)
ዮናን / Jonan: (ሉቃ 3:30፣ 31)
ዮአስ ~ Joah:
‘የ አያ፣ የወንድም’ ማለት ነው።
1.
የአሳፍ ልጅ፥ የኤልያቄም መዝገብ ቤት ሐላፊ፥ “የቤቱም አዛዥ የኬልቅያስ ልጅ ኤልያቄም ጸሐፊውም ሳምናስ ታሪክ ጸሐፊም የአሳፍ ልጅ ዮአስ ወደ እርሱ ወጡ” (ኢሳ 36:3፣11፣22)
2.
ዮአክ፥ “ልጁ ዮአክ፥ ልጁ አዶ፥ ልጁ ዛራ፥ ልጁ ያትራይ።”
(1 ዜና 6:21)
3.
የዖቤድኤዶም ልጅ፥
ኢዮአስ፥ “እግዚአብሔርም ባርኮታልና ዖቤድኤዶም ልጆች ነበሩት። በኵሩ ሸማያ፥ ሁለተኛው ዮዛባት፥ ሦስተኛው ኢዮአስ፥ አራተኛው
ሣካር፥ አምስተኛው
ናትናኤል፥”
(1 ዜና 26:4)
4.
የዛማት ልጅ፥ ዩአክ፥ “ሌዋውያኑም፥ ከቀዓት ልጆች የአማሢ ልጅ መሐትና
የዓዛርያስ ልጅ
ኢዮኤል፥ ከሜራሪም
ልጆች የአብዲ
ልጅ ቂስና
የይሃሌልኤል ልጅ ዓዛርያስ፥ ከጌድሶንም ልጆች የዛማት ልጅ ዩአክና የዩአክ ልጅ ዔድን፥” (2 ዜና 29:12)
5.
የኢዮአካዝ ልጅ፥ ኢዮአክ፥ “... የኤዜልያስ ልጅ ሳፋን፥ የከተማይቱም
አለቃ መዕሤያ፥
ታሪክ ጸሐፊም
የኢዮአካዝ ልጅ
ኢዮአክ የእግዚአብሔርን የአምላኩን ቤት ይጠግኑ
ዘንድ ሰደዳቸው።” (2 ዜና
34:8)
ዮአሪብ ~ Jehoiarib:
‘አምላክ የጠበቀው’
ማለት ነው።
ከሃያ አራቱ
የካህናት ምድብ፥ የመጀመሪያው አለቃ፥ “መጀመሪያውም ዕጣ ለዮአሪብ ወጣ፥ ሁለተኛው
ለዮዳኤ”
(1 ዜና 24:7)
ዮአቂም ~
Joiakim:
ያሕ ቁም፣ ሕያው ያቆመው፣ አምላክ ያቆመው፣ በጌታ የጸና... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ቀሙኤል፣ ቁሚ፣ አኪቃም፣ አዶኒቃም፣ ኢዮአቄም፣ ዓዝሪቃም፣ ኤልያቄም፣ ያቂም፣ ዮቂም]
‘ያሕ’ (ሕያው)
እና ‘ቆመ’ ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። የኢያሱ ልጅ፥ ሊቀ ካህኑ ዮአቂም፥ (ነህ 12:10፣ 12 እና 26)
ዮአኪን ~
Jehoiachin:
ያሕ አቅን፣ ጌታ ያቃናው፣ የአምላክ ሥራ፣ በእግዚአብሔር የተሾመ፣ ሕያው ያከናወነው... ማለት ነው።
[ትርጉሙ “እግዚአብሔር ያቆማል” ማለት
ነው /
መቅቃ]
በአባቱ እግር ተተክቶ ለመቶ ቀን በኢየሩሳሌም የነገሠ፣ የኢዮአቄም ልጅ፥ (2 ዜና 36፡9)
ዮአዳ ~
Joaada:
የወዳ፣ በሕያው የተወደደ፣ ለአምላክ የቀረበ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ዩዳሄ፣ ዮዳሄ፣ ያሕዳይ፣ ያዱአ፣ ያዳ፣ ያዳይ፣ ዬሕድያ፣ ዬዳይ፣ ይሆዓዳ፣ ይዲዳ፣ ይዲድያ፣ ዮዓዳን፣ ዮዳሄ]
ከኤልያሴብ ልጅ፣ ሊቀ ካህኑ ዮአዳ፥ (ነህ 13:28)
ዮዓዳን ~ Jehoaddan: ያሕ ወደን፣ በጌታ የተወደደ፣ ለአምላክ የቀረበ፣ የሕያው ወዳጅ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ዩዳሄ፣ ዮዳሄ፣ ያሕዳይ፣ ያዱአ፣ ያዳ፣ ያዳይ፣ ዬሕድያ፣ ዬዳይ፣ ይሆዓዳ፣ ይዲዳ፣ ይዲድያ፣ ዮአዳ፣ ዮዳሄ]
የዮአኪን ልጅ፣ የንጉሥ አሜስያስ እናት፥ (2 ነገ 14፡2)
ዮእድ
~ Joed:
‘የእድ፣ የእጅ፣ ምስክር’ ማለት ነው። የፈድያ ልጅ፥
“የብንያምም ልጆች እነዚህ ናቸው የየሻያ ልጅ የኢቲኤል ልጅ የመዕሤያ ልጅ የቆላያ ልጅ የፈዳያ ልጅ የዮእድ ልጅ የሜሱላም ልጅ ሰሉ።” (ነህ 11:7)
ዮካል ~
Jucal:
የቃል ማለት ነው። የሰሌምያ ልጅ፥ (ኤር 38፡1) ፣ (ኤር 37:3)
ዮካልን ~ Jehucal: ያሕ ቃል፣ ሕያው ቃል’ ማለት ነው። ሴዴቅያስ
ወደ አምላኩ
እንዲጸልይለት ወደ ነቢዩ ኤርምያስ ከላካቸው ሁለት ሰዎች አንዱ፥ የሴለምያ ልጅ፥ “ንጉሡም ሴዴቅያስ።
ወደ አምላካችን
ወደ እግዚአብሔር
ስለ እኛ
ጸልይ ብሎ
የሰሌምያን ልጅ
ዮካልንና ካህኑን
የመዕሤያን ልጅ
ሶፎንያስን ወደ
ነቢዩ ወደ ኤርምያስ ላከ።” (ኤር 37:3)
ዮካብድ ~
Jochebed:
ያከብድ፣ ከፍ ያደርግ፣ ከባድ፣ የተከበረ... ማለት ነው።
[ትርጉሙ “እግዚአብሔር ክብር” ማለት
ነው / መቅቃ]
የነቢዩ ሙሴ እናት፣ የሌዊ ልጅ፥ የእንበረም ሚስት፥ ዮካብድ፥ (ዘኁ 26፡59)
ዮዘካር ~
Jozachar:
የዝክር፣ የተዘከረ፣ የታሰበ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ዮዛባት]
‘ያሕ’(ያሕዌ ፣ ሕያው) እና ‘ዝክር’
ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። የሰምዓት
ልጅ፥ (2 ነገ 12:21)
ዮዛባት ~ Zabad: ‘ሥጦታ’ ማለት ነው። …
[ተዛማጅ ስም- ዮዘካር]
የሞዓባዊቱ የሰማሪት ልጅ ዮዛባት፥ (2
ዜና 24:26)
ዮዛር ~
Joezer:
‘የዘር፣ የወገን፣ የረዳት’ ማለት ነው። ከዳዊት ዘበኞች አንዱ፥ ቆርያዊው፥
“ቆርያውያን ሕልቃና፥ ይሺያ፥
አዛርኤል፥ ዮዛር፥
ያሾቢአም”
(1 ዜና 12:6)
ዮዛባት ~ Jehozabad, Josabad, Jozabad, Jozabad:
የአምላክ ስጦታ፣ የሕያው ጸጋ፣ ጥሎሽ፣ ማጫ፣ ካሳ... ማለት ነው።
1.
ከከሌዊያውያን በር
ጠባቂዎች አንዱ፥ የዖቤኤዶም ልጅ፥ “እግዚአብሔርም ባርኮታልና ዖቤድኤዶም ልጆች ነበሩት በኵሩ ሸማያ፥ ሁለተኛው ዮዛባት፥ ሦስተኛው ኢዮአስ፥ ... አምስተኛው ናትናኤል” (1 ዜና 26:4)
2.
የሰምዓት ልጅ፥ “ባሪያዎቹም የሰምዓት ልጅ ዮዘካርና የሾሜር ልጅ ዮዛባት መቱት፥ ሞተም በዳዊትም ከተማ ... ነገሠ” (2 ነገ 12:21)
3.
“ከእርሱም በኋላ ዮዛባት፥ ከእርሱም ጋር ለሰልፍ የተዘጋጁ መቶ ሰማኒያ ሺህ
ሰዎች ነበሩ።” (2 ዜና 17:18)
ዮዛባት / Josabad: ‘ጥሎሽ፣ ስጦታ፣ ሽልማት ማግኘት’
ማለት ነው።
ከብንያም ጦረኞች
አንዱ፥ ከዳዊት
ሠራዊት የተቀላቀለ፥
(1 ዜና 12:5)
“ገድሮታዊው ዮዛባት፥
ኤሉዛይ፥ ኢያሪሙት፥
በዓልያ፥ ሰማራያ፥
ሀሩፋዊው ሰፋጥያስ፥”
ዮዛባት / Jozabad: ‘አምላክ ያበለጸገው’ ማለት ነው።
1.
ከጊልቦ ውጊያ
በፊት፥ ወደ
ዳዊት ከተቀላቀሉ የምናሴ ሠራዊት፥ የሺህ
አለቃ፥ “ወደ ጺቅላግም
ሲሄድ ከምናሴ
ወገን የምናሴ
ሻለቆች የነበሩ
ዓድና፥ ዮዛባት፥ ይዲኤል፥ ... ወደ እርሱ ከዱ” (1 ዜና 12:20)
2.
ሌላ፥ ከጊልቦ
ውጊያ በፊት፥
ወደ ዳዊት ከተቀላቀሉ የምናሴ ሠራዊት፥ የሺህ አለቃ፥ “ወደ ጺቅላግም ሲሄድ ከምናሴ ወገን የምናሴ ሻለቆች የነበሩ ዓድና፥
ዮዛባት፥ ይዲኤል፥
ሚካኤል፥ ዮዛባት፥
ኤሊሁ፥ ... ከዱ።” (1 ዜና
12:20)
3.
በንጉሡ ሕዝቅያስ
ዘመን የነበረ፥ “በንጉሡም በሕዝቅያስና በእግዚአብሔር ቤት አለቃ
... ዮዛባት፥ ኤሊኤል፥
ሰማኪያ፥ መሐት፥
በናያስ፥ ከኮናንያና ከወንድሙ ከሰሜኢ እጅ በታች ተቈጣጣሪዎች ነበሩ።” (2 ዜና 31:13)
4.
የሌዋውያን አለቃ የነበረ፥ “የሌዋውያኑም አለቆች ...ይዒኤል፥ ዮዛባት ለፋሲካው መሥዋዕት እንዲሆን
አምስት ሺህ
በጎችና ፍየሎች፥
አምስት መቶም
በሬዎች ለሌዋውያን
ሰጡ።”
(2 ዜና 35:9)
5.
በዕዝራ ዘመን
የነበረ፥ የኢያሱ
ልጅ፥ “በአራተኛውም ቀን ... ጋር ሌዋውያን የኢያሱ ልጅ ዮዛባትና የቢንዊ ልጅ ኖዓድያ ነበሩ።” (ዕዝ 8:33)
6.
በግዞት እንግዳ ሚስቶችን ካገቡ ካህናት፥ ፋስኩር ልጅ፥ “ከፋስኩር ልጆችም፤ ኤልዮዔናይ፥ መዕሤያ፥ ይስማኤል፥ ናትናኤል፥ ዮዛባት፥ ኤልዓሣ” (ዕዝ 10:22)
7.
ሌላ፥ በግዞት እንግዳ ሚስቶችን ካገቡ፥ “ደግሞ ኢያሱና ባኒ፥ ... ዮዛባት፥ ሐናን፥ ፌልያ፥ ሌዋውያኑም ሕጉን ያስተውሉ ዘንድ ሕዝቡን ያስተምሩ ነበር ሕዝቡም
በየስፍራቸው ቆመው
ነበር።”
(ነህ 8:7)
ዮያሪብ ~ Joiarib: ‘ይራባ፣ መርባት፣ መራባት፣ መባዛት’ ማለት ነው።
1.
ከካህናት ምድብ መሥራቾች አንዱ፥ “ከካህናቱ የዮያሪብ ልጅ ዮዳኤ፥ ያኪን” (ነህ 11:10)
2.
የዘካርያስ ልጅ፥ “የሴሎናዊውም ልጅ የዘካርያስ ልጅ የዮያሪብ ልጅ የዓዳያ
ልጅ የዖዛያ
ልጅ የኮልሖዜ
ልጅ የባሮክ
ልጅ መዕሤያ።” (ነህ
11:5)
3.
“መዓድያ፥ ቢልጋ፥
ሸማያ፥ ዮያሪብ፥
ዮዳኤ፥”
(ነህ 12:6)
4.
“ወደ አለቆቹም ወደ አልዓዛር፥ ወደ አርኤል፥ ... ወደ ሜሱላም፥ ደግሞም ወደ አዋቂዎቹ ወደ ዮያሪብና ወደ ኤልናታን ላክሁ።” (ዕዝ 8:16)
ዮዲት ~ Judith: ዮዲት፣ ይሁዲት፣
ውሕድ፣ ተዋሐደ፣ አንድ
የሆነ፣ አይሁዳዊት... ማለት ነው። (ውዲት፣ ውድ፣ የተወደደች፣ የተፈቀረች ተብሎም ይተረጎማል።)
‘ይሁዲት’
ከሚለው የመጣ
ስም ነው።
የኬጢያዊው የብኤሪ
ልጅ፥ (ዘፍ 26:34)
ዮዳሄ ~
Jehoiada:
እግዚአብሔር ያወቀው፣ የሕያው ወዳጅ ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ዩዳሄ፣ ዮዳሄ፣ ያሕዳይ፣ ያዱአ፣ ያዳ፣ ያዳይ፣ ዬሕድያ፣ ዬዳይ፣ ይሆዓዳ፣ ይዲዳ፣ ይዲድያ፣ ዮአዳ፣ ዮዓዳን]
ከዳዊት ወታደሮች፣ የበናያስ አባት፥ “የዮዳሄ ልጅ በናያስ ...” (2 ሳሙ 8:18) ፣ (1 ዜና 18:17)
ዮግሊ ~ Jogli: ‘መሰደድ’ ማለት ነው። የዳናውያን አለቃ፥ የቡቂ አባት፥
“ከዳን ልጆች ነገድ አንድ አለቃ የዮግሊ ልጅ ቡቂ” (ዘኊ 34:22)
ዮግብሃ ~ Jogbehah: ‘ከፍተኛ፣ ታላቅ፣
የተከበረ’
ማለት ነው።
በጋድ ነገድ
የተገነባና የተመሸገ፥ ከዮርዳኖስ በስተምሥራቅ የሚገኝ ከተማ፥ “ዓጥሮትሽፋንን፥ ኢያዜርን፥
ዮግብሃን”
(ዘኊ 32:35)
ዮፍታሔ ~ Jephthae, Jephthah: የፌት፣ የፈታ፣ የተለቀቀ፣ ያልታሰረ፣ ፍትሕ የተሰጠው... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ኤፍታህ፣ ያፌት ፣
ይፍታሕ፣ ይፍታሕኤል፣ ፈታያ]
‘ይፍታ’ ከሚለው ቃል የመጣ ስም ነው። የቃሉ ምንጭ ‘ፈታ’ የሚለው ነው። [ትርጉሙ “እግዚአብሔር ይከፍታል” ማለት
ነው /
መቅቃ]
ዮፍታሔ / Jephthae: ሐዋርያው ጳውሎስ ለአይሁዳውያን በላከው ደብዳቤ የጠቀሰው፣ የገለዓድ ልጅ፥ ዮፍታሔ ፥ (ዕብ 11፡32)
ዮፍታሔ / Jephthah: የገለዓድ ልጅ፥ (መሣ 11፡1-33)
ዮፎኒ ~ Jephunneh: ‘መንገዱ የቀና’ ማለት ነው።
1.
የኢያሱ ተባባሪ የነበረው፥ የካሌብ አባት፥ “ከይሁዳ ነገድ የዮፎኒ ልጅ ካሌብ” (ዘኊ 13:6)
2.
የዬቴር ልጅ፥ ዮሮኒ፥ “የዬቴር ልጆች ዮሮኒ፥ ፊስጳ፥ አራ ነበሩ።”
(1 ዜና 7:38)
No comments:
Post a Comment