ወልደአዴር ~ Benhadad: ቤን ሀዳድ፣ የሀዳድ ልጅ፣ የተወደደ ልጅ፣ የአዴር ልጅ... ማለት ነው።

Benhadad- ቤን (ልጅ) እና አዳድ (ውድ) ከሚሉ ሁለት ቃላት የመጣ ስም ነው።

በዚህ ስም የሚታወቁ ሁለት ሰዎች አሉ።

የጠብሪሞን ልጅ የሶርያ ንጉሥ፥ (1 ነገ 15:18) (2 ነገ 8:7)

ወና ~ Halak: እልቅ፣ ባዶ፣ ደልዳላ ማለት ነው። ኢያሱ ከያዛቸው ቦታዎች የደቡባዊ ወሰን፥ እስከ ሴይርም ከሚያወጣው ወና ከሆነው ተራራ ጀምሮ ከአርሞንዔም ተራራ በታች በሊባኖስም ሸለቆ ውስጥ እስካለው እስከ በኣልጋድ ድረስ ነገሥታቶቻቸውንም ሁሉ ይዞ መታቸው፥ ገደላቸውም። (ኢያ

11:17 12:7)

ወንያ ~ Vaniah: ሕያው መና ማለት ነው። ከባኒ ልጆች አንዱ፥ ወንያ ሜሪሞት፥ ኤልያሴብ፥ መታንያ፥” (ዕዝ 10:36)

ወንድም ~ Ahi: አያ፣ ወንድም፣ ወዳጅ፣ ጓደኛ... ማለት ነው። [ተለዋጭ ስም- አኪ]

Ahi- አያከሚለው ቃል የመጣ ስም ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-

. የአብዲኤል ልጅ፥ የአባቶቻቸውም ቤቶች አለቃ የጉኒ ልጅ የአብዲኤል ልጅ ወንድም ነበረ” (1 ዜና 515)

. የሳሜር ልጅ፥ አኪ- (1 ዜና 7:34)

ወይን ~ Vine, Wine: ወይነ፣ ዋይን፣ ወይን ጠጅ... ማለት ነው።

ወይንከሚለው ቃል የተገኘ ስም ነው።

       ወይን / Vine: ኖኅም ገበሬ መሆን ጀመረ፥ ወይን ተከለ። (ዘፍ 9:20)

       ወይን / Wine:

. ወይን ከኖኅ ዘመን ጀምሮ የሚታወቅ ጥንታዊ መጠጥ ነው፥ኖኅም ገበሬ መሆን ጀመረ፥ ወይን ተከለ። (ዘፍ 9:20)

. የሳሌም ንጉሥ መልከ ጼዴቅ ለአብርሃም ያቀረበለት፥ የሳሌም ንጉሥ መልከ ጼዴቅም እንጀራንና ወይን ጠጅን አወጣ እርሱም የልዑል እግዚአብሔር ካህን ነበረ።” (ዘፍ 14:18)

.መልአኩም ማጭዱን ወደ ምድር ጣለው፥ በምድርም ካለው ወይን ዛፍ ቈርጦ ወደ ታላቁ ወደ እግዚአብሔር ቍጣ መጥመቂያ ጣለ።” (ራእ 14:19)

ወደብ ~ Haven: ሒዋን፣ የሕያው ቦታ፣ የዘላለማውያን መኖሪያ ... ማለት ነው። Haven- ሒዋንከሚለው የመጣ ስም ነው።

የመርከብ ማረፊያ፥ (መዝ 10730)

ዋሻ ~ Den: ደን፣ ጫካ፣ ዱር፣ ዋሻ... ማለት ነው።

Den- ደንከሚለው ቃል የተገኘ ስም ነው።

. የአንበሳ ግልገሎች መተኛ፥“...በየዋሻቸውም ይተኛሉ (መዝ 104 22) (ዳን 6:16 17)

. ባህታውያን መኖሪያ፥ ዓለም አልተገባቸውምና በምድረ በዳና በተራራ፥ ዋሻ በምድር ጕድጓድ ተቅበዘበዙ። (ዕብ 11:38)

. ሽፍቶች የሚውሉበት፥ ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች ተብሎ ተጽፎአል፥ እናንተ ግን የወንበዶች ዋሻ አደረጋችኋት አላቸው። (ማቴ 21:13 ማር 11:17)


No comments:

Post a Comment

ማውጫ

    ሀ   ለ   ሐ   መ   ሠ   ረ   ሰ   ሸ   ቀ   በ   ተ   ቸ   ኀ   ነ   ኘ   አ   ከ   ኸ   ወ   ዐ   ዘ   ዠ   የ   ደ   ጀ   ገ   ጠ   ጨ   ጰ   ጸ   ፀ   ፈ   ፐ