ሀ ለ ሐ መ ሠ ረ ሰ ሸ ቀ በ ተ ቸ ኀ ነ ኘ አ ከ ኸ ወ ዐ ዘ ዠ የ ደ ጀ ገ ጠ ጨ ጰ ጸ ፀ ፈ ፐ
ደኅንነት ~
Shalem:
ሸላም፣ ሰላም፣ በደኅና፣ በአማን... ማለት ነው።
Shalem- ‘ሰላም’ ከሚለው ቃል የተገኘ ስም ነው።
ያዕቆብ ከስደት ሲመለስ ያለፈበት፣ የቦታ ስም፥ “ያዕቆብም ከሁለት ወንዞች መካከል በተመለሰ
ጊዜ በከነዓን
ምድር ወዳለችው
ወደ ሴኬም
ከተማ በደኅንነት መጣ
በከተማይቱም ፊት
ሰፈረ።”
(ዘፍ 33:18-20)
ደሊላ ~ Delilah:
ደላላ፣ መደለል፣ ማባበል፣ ማግባባት፣ ማስማማት፣ ማደራደር... ማለት ነው።
‘ደለለ’
ከሚለው ግስ
የተገኘ ስም ነው።
በሶሬቅ ሸለቆ
የነበረች ፍልስጤጥኤማዊት ሴት፥
ሶምሶን የወደዳት፥
(መሣ 16:4)
ደላያ ~ Dalaiah: ድለ ያሕ፣ ድለ ሕያው፥
በአምላክ ያሸነፈ.. ማለት
ነው። የኤልዮዔናይም ልጅ፥ “የኤልዮዔናይም ልጆች ሆዳይዋ፥ ኤልያሴብ፥ ፌልያ፥ ዓቁብ፥ ዮሐናን፥
ደላያ፥ ዓናኒ
ሰባት ነበሩ” (1 ዜና 3:24)
ደልፎን ~
Dalphon:
‘ፈጣን’
ማለት ነው። ከአሥሩ የሐማ ልጆች ሁለተኛው፥ “ፈርሰኔስ፥ ደልፎን፥ ፋስጋ፥ ፋረዳታ፥” (አስ 9:7)
ደማስቆ ~ Damascus: የደም ከረጢት ማለት ነው።
ከቀደሙት የምሥራቅ አገር
ከተሞች፥ የሶሪያ
ዋና ከተማ፥
“የሶርያ ራስ ደማስቆ ነው፥ የደማስቆም ራስ
ረአሶን ነው
... ኤፍሬም ይሰባበራልና
ሕዝብ አይሆንም” (ኢሳ
7:8፥ 17:3)
ደማሪስ
~ Damaris:
‘ልጃገረድ’ ማለት ነው። በጳውሎስ
ስብከት ክርስትናን
ከተቀበሉ የአቴን
ሰዎች፥ “አንዳንዶች ወንዶች
ግን ተባብረው አመኑ፤
ከእነርሱ ደግሞ
በአርዮስፋጎስ ያለው
የፍርድ ቤት
ፈራጅ ዲዮናስዮስ
ደማሪስ የሚሉአትም አንዲት ሴት ሌሎችም ከእነርሱ ጋር ነበሩ።” (ሐዋ 17:34)
ደራል ~ Darda: ‘ዕንቁ’ ማለት ነው። ከሰለሞን ጥበብ
ጋር ከተነጻጸሩ፥
በጥበበኛነታቸው ከታወቁት
አራት ሰዎች፥
“ከሰውም ሁሉ ይልቅ
ከኢይዝራኤላዊው ከኤታንና
ከማሖል ልጆች ከሄማንና ከከልቀድ ከደራልም ይልቅ ጥበበኛ ነበረ...” (1 ነገ 4:31)
ደርቆን ~
Darkon:
‘ትውልድ’ ማለት ነው። ከባቢሎን ምርኮ ከተመለሱ፥ የንጉሥ ሰሎሞን አገልጋይ ከነበሩ፥ አባት፥ “የየዕላ ልጆች፥ የደርቆን ልጆች፥ የጌዴል ልጆች፥” (ዕዝ
2:56፤ ነህ7:58)
ደርቤ ~
Derbe:
ደራቢ፣ ደርብ፣ ድርብ፣ የተደረበ፣ የተደገመ... ማለት ነው።
‘ደረበ’
ከሚለው ግስ
የመጣ ስም ነው።
ሐዋርያት በርናባስና ጳውሎስ የሸሹበት አገር፥ (ሥራ 16:1)
ደቅላ ~ Diklah: ‘ዲቃላ፣ ደቃቃ፣ ልጅ፣ ትንሽ’ ማለት ነው። የዮቅጣን ልጅ፥ “ደቅላንም፥ ዖባልንም፥ አቢማኤልንም፥”
(ዘፍ 10:27፤ 1
ዜና 1:21)
ደባሼት ~ Dabbasheth: ‘ደብረ ሰጥ፥ ዳገታማ ቦታ’ ማለት ነው። የዛብሎን አዋሳኝ ከተማ፥ “ድንበራቸውም በምዕራብ በኩል ወደ መርዓላ ወጣ፥ እስከ ደባሼትም ደረሰ በዮቅንዓም ፊት ለፊት ወዳለው ወንዝ ደረሰ” (ኢያ 19:11)
ደብራይ ~ Dibri: ደብሪ፣ ደብሬ፣ ደብር፣ ተራራ ቦታ፣ ርስት አምባ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ዲቦራ፣ ዳቤር፣ ዳብራት]
‘ደብር’
ከሚለው ቃል
የመጣ ስም ነው። የሰሎሚት አባት፥
(ዘሌ 24፡11)
ደና ~
Dannah:
ዳና፣ ዳኘ፣ ዳኝ፣ ዳኝነት፣ ዳኛ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች -
ዲና፣ ዳን]
የይሁዳ ልጆች ነገድ ርስት፣ የከተማ ስም፥ (ኢያ 15፡49)
ዱራ ~
Dura:
‘ክብ፥ ዙሪያ ጥምጥም’ ማለት ነው። ናቡከደነፆር የጣዖቱን ምስል
ያስቀመጠበት መስክ፥
“ንጉሡ ናቡከደነፆር ቁመቱ
ስድሳ ክንድ
ወርዱም ስድስት ክንድ የሆነውን የወርቁን ምስል አሠራ በባቢሎንም አውራጃ በዱራ ሜዳ አቆመው።” (ዳን 3:1)
ዱዲ ~ Dodai, Dodo: ውዴ፥
ወዳጄ... ማለት ነው።
ከዳዊት አለቆች
አንዱ፥ “በሁለተኛውም ወር ክፍል ላይ አሆሃዊው ዱዲ ነበረ በእርሱም ክፍል ሀያ አራት
ሺህ ጭፍራ
ነበረ።”
(1 ዜና 27:4)
ዱዲ ~ Dodo: ውድ፥ ወዳጅ... ማለት ነው።
1. የይሳኮር ወገን፥ “ከአቤሜሌክም በኋላ ከይሳኮር ነገድ የሆነ የዱዲ ልጅ
የፎሖ ልጅ
ቶላ እስራኤልን
ለማዳን ተነሣ
... ነበር።”
(መሣ 10:1)
2. ከሦስቱ የዳዊት ኃያላን አንዱ፥ የኤልያናን (Eleazar) አባት፥
“ከእርሱም በኋላ የአሆሃዊው የዱዲ ልጅ ኤልያናን ነበረ፤ ለሰልፍ የተሰበሰቡትን ፍልስጥኤማውያንን በተገዳደሩ ጊዜ ከዳዊት ጋር ከሦስቱ ኃያላን አንዱ እርሱ ነበረ፤ የእስራኤልም ሰዎች ተመለሱ።” (2 ሳሙ 23:9፤ 1
ዜና 11:12)
3.ከሠላሳዎቹ የዳዊት ኃያላን አንዱ፥ ኤልያናን (Elhanan) አባት፥
“የኢዮአብም ወንድም አሣሄል
በሠላሳው መካከል
ነበረ፥ የቤተ
ልሔም ሰው
የዱዲ ልጅ
ኤልያናን”
(2 ሳሙ 23:24)
ዲልዓን ~ Dilean: ‘ጠባቂ፣ ጋራጅ’ ማለት
ነው። በታችኛው
ደልዳላ የይሁዳ መሬት ከሚገኙ ከተሞ ች አንዱ፥ “ጽናን፥ ሐዳሻ፥ ሚግዳልጋድ፥ ዲልዓን፥”
(ኢያ 15:38)
ዲሞና ~
Dimonah:
በይሁዳ የሚገኝ ከተማ፥ “ዲሞና፥ ዓድዓዳ፥ ቃዴስ፥ ሐጾር፥ ዪትናን፥” (ኢያ 15:23)
ዲሞን ~
Dimon:
ደመኛ፣ ዲመን፣ ደምነ፣ ደማዊ፣ ደም፣ ቀይ... ማለት ነው።
‘ደም’
ከሚለው ቃል
የተገኘ ስም ነው።
ስለ ሞዓብ
በተነገረ ሸክም፣
የነቢዩ የኢሳይያስ
ትንቢት፥ “የዲሞንም ውኃ
ደም ተሞልታለች
በዲሞንም ላይ
ሥቃይን እጨምራለሁ፥
ከሞዓባውያንም በሚያመልጡ፥
ከምድርም በሚቀሩ
ላይ አንበሳን
አመጣለሁ።”
(ኢሳ 15:9)
ዲሳን ~
Dishan:
‘አጋዘን’ ማለት ነው። የሴይር የመጨረሻ ልጅ፥ “በዚያች አገር የተቀመጡ የሖሪው የሴይር ልጆች እነዚህ ናቸው፤ ሎጣን፥ ሦባል፥ ፅብዖን፥ ዓና፥ ዲሶን፥
ኤጽር፥ ዲሳን” (ዘፍ
36:20፣28፣30፤ 1
ዜና 1:38፣42)
ዲሶን ~ Dishon: ‘አጋዘን’
ማለት ነው።
የሴይር አምስተኛ
ልጅ፥ “በዚያች አገር የተቀመጡ የሖሪው የሴይር ልጆች እነዚህ ናቸው ሎጣን፥ ሦባል፥ ፅብዖን፥ ዓና፥ ዲሶን፥
ኤጽር፥ ዲሳን” (ዘፍ
36:20፣28፣30፤ 1
ዜና 1:38፣42)
ዲብያ ~
Zibia:
ዘበ ያሕ፣ ዘብ፣ የተጠበቀ፣ ታላቅ፣ የተከበረ... ማለት ነው።
Zibia- ‘ዘብ’
እና ‘ያሕ’ (ያሕዌ ፣ ሕያው) ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። የሸሐራይም ልጅ፣ ከአባቶች ቤቶች አለቆች የነበረ፥ ዲብያ ፥ (1 ዜና 8:9)
ዲቦራ ~
Deborah:
ደቦራህ፣ ደብርህ፣ ደብር፣ ተራራ፣ ርስት፣ አምባ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ደብራይ፣ ዳቤር፣ ዳብራት]
[ትርጉሙ “ንብ”
ማለት ነው
/ መቅቃ]
በዚህ ስም
የሚታወቁ ሁለት
ሰዎች አሉ።
1. የርብቃ ሞግዚት፥ (ዘፍ 35፡8)
2. በእስራኤል ላይ ዳኛ
የነበረች፣ ነቢይቱ
ዲቦራ፥ (መሣ 4:4)
ዲና ~
Dinah:
ዳኛ፣ ዳኘ፣ ፈረደ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ደና፣ ዳን]
[ትርጉሙ “ፈረደ”
ማለት ነው
/ መቅቃ]
ልያ ለያዕቆብ የወለደችለት ሴት ልጅ፥ (ዘፍ 30፡21)
ዲንሃባ ~
Dinhabah:
ደነ አባ፣ አባት ደን፣ ትልቅ ዱር፣ ጫካ... ማለት ነው።
‘ደን’ እና ‘አባ’
ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።
በእስራኤልም ልጆች
ላይ ገና
ንጉሥ ሳይነግሥ
በኤዶምያስ ምድር
የነገሠ፥ ባላቅ
የነገሠባት ከተማ፥ “በኤዶምም የቢዖር ልጅ ባላቅ ነገሠ የከተማውም ስም ዲንሃባ ናት።” (ዘፍ
36፡32) ፣ (1
ዜና 1:43)
ዲያቆናት ~
Deacon:
ዲያቆን፣ ድያቆን፣ ድቁና፣ ደቋና፣ ጉዳይ፣ ክንውን፣ አግልግሎት... ማለት ነው።
‘ደቆነ’
ከሚለው ግስ
የመጣ ስም ነው።
[አገልጋይ ማለት
ነው
/ መቅቃ]
በጳውሎስ መልእክት የተጠቀሰ የቤተ ክርስቲያን ሹመት፥ (ፊሊ 1:1)
ዲዮናስዮስ ~
Dionysius: ‘ፈውስ ያገኘ’ ማለት
ነው። በጳውሎስ
ስብከት ክርስትና
ከተቀበሉ የግሪክ
ሰዎች፥ “አንዳንዶች ወንዶች
ግን ተባብረው
አመኑ፤ ከእነርሱ
ደግሞ በአርዮስፋጎስ
ያለው የፍርድ
ቤት ፈራጅ
ዲዮናስዮስ ደማሪስ
የሚሉአትም አንዲት
ሴት ሌሎችም
ከእነርሱ ጋር
ነበሩ።”
(ሐዋ 17:34)
ዲዮጥራጢስ ~ Diotrephes: በዮሐንስ
መልእክት የተጠቀሰ
ክርስቲያን፥ “ወደ ቤተ
ክርስቲያን ጻፍሁ፤
ዳሩ ግን
ዋናቸው ሊሆን
የሚወድ ዲዮጥራጢስ አይቀበለንም።” (3 ዮሐ 1:9)
ዲዲሞስ ~ Didymus: ‘መንታ፣ ጥንድ፣ እጥፍ’ ማለት
ነው። የሐዋርያው
ቶማስ የክብር
ስም፥ “ስለዚህ ዲዲሞስ የሚሉት ቶማስ ለባልንጀሮቹ
ለደቀ መዛሙርት።
ከእርሱ ጋር እንሞት ዘንድ እኛ ደግሞ እንሂድ አለ” (ዮሐ 11:16፥ 20:24፥ 21:2)
ዳልማኑታ ~ Dalmanutha: ‘ገንዳ’
ማለት ነው።
በገሊላ በስተምዕራብ የሚገኝ
ከተማ፥ “አሰናበታቸውም። ወዲያውም
ከደቀ መዛሙርቱ
ጋር ወደ ታንኳይቱ ገብቶ ወደ ዳልማኑታ አገር መጣ።” (ማር 8:10)
ዳርዮስ ~ Darius: ‘ደራሽ፣ ንቁ’
ማለት ነው።
1. “ዳርዮስም በመንግሥቱ ሁሉ ዘንድ እንዲሆኑ መቶ ሀያ መሳፍንት በመንግሥቱ ላይ ይሾም ዘንድ ወደደ።” (ዳን 6:1፥ 11:1)
2. “በዚያ ጊዜም ንጉሡ ዳርዮስ መዛግብት ባሉበት በባቢሎን ቤተ መጻሕፍት እንዲመረመር አዘዘ።” (ዕዝ 5:1)
3. “ከሌዋውያኑም
በኤልያሴብና በዮአዳ፥
በዮሐናንና በያዱአ ዘመን የአባቶች ቤቶች አለቆች ተጻፉ ካህናቱም በፋርሳዊው በዳርዮስ መንግሥት ዘመን ተጻፉ።” (ነህ 12:22)
ዳቤር ~
Debir:
ደብር፣ ተራራ፣ ቦታ፣ ርስት፣ ጉልት፣ አምባ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ደብራይ፣ ዲቦራ፣ ዳብራት]
‘ደብር’
ከሚለው ቃል
የመጣ ስም ነው።
. የንጉሥ አዶላም
አገር፥ (ኢያ 10:3)
. “ሶኮ፥ ደና፥ ዳቤር የምትባለው ቂርያትሰና፥”
(ኢያ 15፡49)
ዳብራት ~ Dabareh, Daberath: ደብራ፣ ደብራት፣ ደብሮች፣ ቦታዎች፣ ርስታት... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ደብራይ፣ ዲቦራ፣ ዳቤር] ‘ደብር’ ከሚለው ቃል የመጣ ስም ነው።
ዳብራት / Dabareh:
ለሌዋውያን ወገኖች ለጌድሶን ልጆች ርስት እንዲሆን የተሰጠ፥ (ኢያ 21፡28)
ዳብራት / Daberath:
(ኢያ 19፡12)
ዳታን ~ Dathan: ‘ሕጋዊ ባለመብት’ ማለት
ነው። ከሮቦል
ነገድ፥ ፈራጅ
የነበረ፥ በቆሬ ሙሴን ከተቃዎሙት፥ “የሌዊም ልጅ የቀዓት ልጅ የይስዓር ልጅ ቆሬ ከሮቤልም ልጆች የኤልያብ ልጆች ዳታንና አቤሮን የፋሌትም ልጅ ኦን በሙሴ ላይ ተነሡ።” (ዘኊ16:1፥
26:9፥ 11:6፤ መዝ 106:17)
ዳን ~
Dan:
ዳኝ፣ ዳኛ፣ ዳኘ፣ ፈረደ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች-
ደና፣ ዲና]
‘ዳኝ’ ከሚለው
ቃል የተገኘ
ስም ነው።
[ትርጉሙ “ዳኛ” ማለት ነው / መቅቃ]
በዚህ ስም
የሚታወቁ አንድ
ሰውና አንድ
ቦታ አሉ።
1. የቦታ ስም፥ ሌሳ ዳን ተባለች፥ “አብራምም ወንድሙ እንደ ተማረከ በሰማ
ጊዜ ... ፍለጋቸውንም ተከትሎ
እስከ ዳን ድረስ ሄደ።”
(ዘፍ 14፡14)
፣ “ከተማይቱንም ከእስራኤል በተወለደው በአባታቸው በዳን ስም ዳን ብለው ጠሩአት የከተማይቱም ስም አስቀድሞ ሌሳ ነበረ።” (መሣ 18:29)
2. የራሔል ባሪያ ባላ ለያቆብ የወለደችለት፥ “ራሔልም። እግዚአብሔር ፈረደልኝ፥ ቃሌንም ደግሞ ሰማ፥ ወንድ ልጅንም ሰጠኝ አለች ስለዚህ ስሙን ዳን ብላ
ጠራችው:”
(ዘፍ 30፡6)
፣ “ዳን በወገኑ ይፈርዳል፥ ከእስራኤል ነገድ
እንደ አንዱ።” (ዘፍ 49:16)
ዳንኤል ~
Daniel:
ዳኝ ኤል፣ አምላክ ዳኘ፣ እግዚአብሔር ፈረደ... ማለት ነው።
‘ዳኝ’ እና ’ኤል’
ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። [ትርጉሙ “እግዚአብሔር ፈራጅ ነው ማለት ነው” / መቅቃ]
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-
1. ከቀርሜሎሳዊቱ ከአቢግያ የተወለደው፣ የዳዊት ልጅ፥ (1 ዜና 3፡1)
2. የኢታምር ልጅ ፥
(ዕዝ 8:2)
3. ነቢዩ ዳንኤል፥ “እነዚህ ሦስት ሰዎች፥ ኖኅና ዳንኤል ኢዮብም፥ ቢኖሩባት በጽድቃቸው የገዛ ነፍሳቸውን ብቻ ያድናሉ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር”
(ሕዝ 14:14) ፣ (ዳን 1:6) ፣ (ዳን 1:3፣ 6)
4. ከነህምያ ጋር የቃል
ኪዳን ደብዳቤ
ካተሙት፥ (ነህ 10:6)
ዳኤል ~
Lael:
ለኤል፣ ለአምላክ፣ ለጌታ፣ ለእግዚአብሔር... ማለት ነው።
Lael- ‘ለ ‘ኤል’
ከሚለው ቃል የተገኘ ስም ነው።
የኤሊሳፍ አባት፥
(ዘኁ 3:24)
ዳዊት ~
David:
ደውድ፣ ዘ ውድ፣ ዘውድ፣ የተወደደ ማለት ነው። የእሴይ ልጅ፥ የእስራኤል ንጉሥ፥ (ሩት 4፡22) ፣ (2
ሳሙ 17፡25)
ዳጎን ~ Dagon:
‘ዓሣ’ ማለት ነው። የፍልስጤማውያን አምላክ፥ ጣዖት፥ “በነጋውም የአዛጦን
ሰዎች ማለዱ፥
እነሆም፥ ዳጎን በእግዚአብሔር ታቦት ፊት በምድር ላይ በግምባሩ ወድቆ ነበር ዳጎንንም አንሥተው ወደ ... (1
ሳሙ 5:3፣4)
ዴሬት ~
Zereth:
ዘራት፣ ዘር፣ ወገናት፣ ዘመዶች... ማለት ነው።
Zereth-
‘ዘር’
ከሚለው ቃል
የመጣ ስም ነው። የአሽሑር ልጅ፣
ከሔላ የተወለደ፥
(1 ዜና 4:7)
ዴቀር ~ Dekar: ‘ጦረኛ፣ ቀስተኛ...’ ማለት ነው። የዴቀር ልጅ፣
የንጉሥ ሰሎሞን
አማካሪና ሹም
ነበር፥ “በማቃጽና በሸዓልቢም በቤትሳሚስና በኤሎንቤትሐናን የዴቀር ልጅ” (1 ነገ 4:9)
ዴቤላይም ~ Diblaim: ‘ደባል፣ ድርብ፣ ድርብርብ...’ ማለት
ነው። የሆሴዕ
ሚስት፣ የጎሞር
እናት፥ “እርሱም ሄዶ
የዴቤላይምን ልጅ
ጎሜርን አገባ
እርስዋም ፀነሰች
ወንድ ልጅንም
ወለደችለት።”
(ሆሴ 1:3)
ዴብላታ ~ Diblath: ‘ደባላት’
ማለት ነው።
የቦታ ስም፥
“እጄንም እዘረጋባቸዋለሁ፥ በሚኖሩበትም ስፍራ ሁሉ ምድሪቱን ከዴብላታ ምድረ በዳ ይልቅ ውድማና
በረሃ አደርጋታለሁ
እኔም እግዚአብሔር
...” (ሕዝ 6:14)
ዴቦን ~ Dibon: ‘ሊቅነት’ ማለት ነው።
1. የሞዓባውያን ከተማ፥ “ገተርናቸው ከሐሴቦን እስከ ዴቦን ድረስ ጠፉ ኖፋም እስኪደርሱ እስከ ሜድባ አፈረስናቸው።” (ዘኊ 21:30)
2. ከግዞ ት መልስ፥ የይሁዳ ነገድ መቀመጫ፥ (ነህ 11:25)
ድላያ ~
Delaiah:
ድለ ያሕ፣ ድለ ሕያው፥ በአምላክ ያሸነፈ... ማለት ነው።
1. በንጉሥ ዳዊት ዘመን የነበረ ካህን፥ የሀያ ሶሥተኛው የመቅደሱና የእግዚአብሔር ቤት አለቃ፥ “ሀያ ሦስተኛው ለድላያ፥ ሀያ አራተኛው ለመዓዝያ።”
(1 ዜና 24:18)
2. ከባቢሎን ምርኮ ከተመለሱ፥
ዳላያ፥ “የዳላያ ልጆች፥ የጦብያ ልጆች፥ የኔቆዳ ልጆች፥ ስድስት መቶ አምሳ ሁለት ነበሩ።” (ዕዝ 2:60፤ ነህ 7:62)
3. የመሔጣብኤል ልጅ፥ “እኔም ወደ መሔጣብኤል ልጅ ወደ ድላያ ልጅ ወደ ሸማያ ቤት ገባሁ እርሱም ተዘግቶ ነበርና ...” (ነህ 6:10)
4. “ነገር ግን ኤልናታንና ድላያ ገማርያም ክርታሱን እንዳያቃጥል ንጉሡን ለመኑት፥ እርሱ
ግን አልሰማቸውም።” (ኤር 36:12፥25)
ድልማጥያ ~ Dalmatia: ‘ድንግዝግዝ’ ማለት ነው። ጳውሎስ፥
ቲቶን የላከበት፥ ተራራማ ቦታ፥ “ዴማስ የአሁኑን ዓለም ወዶ ትቶኛልና፥ ወደ ተሰሎንቄም ሄዶአል፤
ቄርቂስም ወደ
ገላትያ ቲቶም
ወደ ድልማጥያ ሄደዋል” (2 ጢሞ 4:10)
ድሩሲላ ~ Drusilla: ‘በጤዛ የራሰ፥
የረሰረሰ፣ ርጥብ’
ማለት ነው።
የሄሮድ ሴት ልጅ፥
“ከጥቂት ቀንም በኋላ
ፊልክስ አይሁዳዊት
ከነበረች ድሩሲላ ከሚሉአት ከሚስቱ ጋር
መጥቶ ጳውሎስን
አስመጣ፥ በኢየሱስ
ክርስቶስም ስለ
ማመን የሚናገረውን
ሰማው።”
(ሐዋ 24:24)
ድብ ~ Arcturus: ‘ክምችት፣ ጥርቅም፣
ስብስብ’
ማለትነው። የኮከብ
ስም፥ “ድብ የሚባለውን
ኮከብና ኦሪዮን
የሚባለውን ኮከብ፥
ሰባቱንም ከዋክብት፥
በደቡብም በኩል ያሉትን የከዋክብት ማደርያዎች ሠርቶአል።” (ኢዮ 9:9፣ 38:32)
ድያ ~ Jupiter: ‘ረጅ አባት’ ማለት
ነው። የግሪክ
የጣዖት ስም፥
“በርናባስንም ድያ አሉት፤
ጳውሎስንም እርሱ
በመናገር ዋና
ስለ ነበረ
ሄርሜን አሉት።” (ሐዋ 14:12፣ 13)
ድዳናውያ ~ Dedanim: የድዳን ወገኖች፥ “ስለ ዓረብ የተነገረ ሸክም። የድዳናውያን ነጋዴዎች ሆይ፥ በዓረብ ዱር ውስጥ ታድራላችሁ።” (ኢሳ 21:13)
ድዳን ~
Dedan:
ደልዳላ፣ ዝቅተኛ ቦታ... ማለት ነው።
1. የኩሽ ልጅ፥ የራዕማ ልጅ፥ “ኩሽም ልጆች ሳባ፥ ኤውላጥ፥ ሰብታ፥ ራዕማ፥ ሰበቃታ
ናቸው። የራዕማ
ልጆችም ሳባ፥
ድዳን ናቸው።” (ዘፍ
10:7፤ 1
ዜና 1:9)
2. (ዘፍ
25:3፤ 1
ዜና 1:32)
ዶሎሕያ ~
Chileab:
ቻለ አብ፣ ቃለ አብ፣ ቃለ ሕያው፣ ቃለ እግዚአብሔር... ማለት ነው።
የዳዊት ልጅ፣ የናባል ሚስት ከነበረች ከአቢግያ የተወለደው፥ (2 ሳሙ 3፡3)
. ዳንኤል- (1
ዜና 3:1)
ዶር ~ Dor: ‘ትውልደ ትውልድ’ ማለት
ነው። የከነናውያን
ጥንታዊ፥ መናገሻ
ከተማ፥ “በይሳኮርና በአሴር
መካከል ቤትሳንና
መንደሮችዋ፥ ይብልዓምና
መንደሮችዋ፥ ዶርና
የመንደሮችዋ ሰዎች፥
... ነበሩ።”
(ኢያ 17:11 1 ነገ 4:11)
ዶርቃ ~ Dorcas: ‘ጮርቃ፣ ለጋ፣
እንቡጥ፣ ቀንበጥ’ ማለት
ነው። በኢዮጴ፥ ጴጥሮስ
ከሞት ያስነሣት
ክርስቲያን፥ “በኢዮጴም ጣቢታ
የሚሉአት አንዲት
ደቀ መዝሙር
ነበረች፥ ትርጓሜውም
ዶርቃ ማለት
ነው፤ እርስዋም
መልካም ነገር
የሞላባት ምጽዋትም
የምታደርግ ነበረች።” (ሐዋ 9:36-41)
ዶታይ ~
Dothan:
ሁለት ጉድጓዶች ማለት ነው። ዮሴፍ ወንድሞቹን ፍለጋ ከሄደባቸው
ቦታዎች፥ “ሰውዮውም። ከዚህ
ተነሥተዋል ወደ
ዶታይን እንሂድ
ሲሉም ሰምቼአቸዋለሁ አለው። ዮሴፍም ወንድሞቹን ተከታትሎ ሄደ፥ በዶታይንም አገኛቸው።” (ዘፍ 37:17)
ዶይቅ ~
Doeg:
ደግ፣ ትሑት፣ ለጋስ፣ ርኁሩኅ፣ አምላክን የሚፈራ... ማለት ነው።
Doeg-
‘ደግ’ ከሚለው ቃል የተገኘ
ስም ነው። የሳኦል የእረኞቹ አለቃ የነበረ፥ (1 ሳሙ 21፡7)
ዶዳያ ~
Dodavah:
ውደ ያሕ፣ የሕያው ወዳጅ፣ ወደ አምላክ የቀረበ... ማለት ነው።
መሪሳ በተባለው
የይሁዳ ግዛት
የነበረ፥ ኢዮሣፍጥን
ከአካዝያስ ጋር
በመተባበር የተቃወመ፥
የአልዓዛር አባት፥
“የመሪሳም ሰው የዶዳያ ልጅ አልዓዛር። ከአካዝያስ
ጋር ተባብረሃልና
እግዚአብሔር ሥራህን
አፍርሶታል ብሎ
በኢዮሣፍጥ ላይ
ትንቢት ተናገረ
...” (2 ዜና 20:37)
No comments:
Post a Comment