ገለዓድ ~ Galeed, Gilead: የምስክር ክምርማለት ነው። ላባ ይጋር ሠሀዱታ ብሎ የጠራት፥ ያዕቆብና አማቱ ላባ ቃል ኪዳን የተገባቡበት ቦታ፥ (ዘፍ 31:4748) ላባም ይጋር ሠሀዱታ ብሎ ጠራት ያዕቆብም ገለዓድ አላት

       ገለዓድ / Gilead:

1. ከዮርዳኖስ በስተምሥራቅ የሚገኝ የተራራ ሰንሰለት፥ እርሱም ያለውን ሁሉ ይዞ ኮበለለ ተነሥቶም ወንዙን ተሻገረ፥ ፊቱንም ወደ ገለዓድ ተራራ አቀና።” (ዘፍ 31:21 3:12-17)

2. የማኪር ልጅ፥ የምናሴ ልጆች ከማኪር የማኪራውያን ወገን ማኪርም ገለዓድ ወለደ ከገለዓድ የገልዓዳውያን ወገን።” (ዘኊ 26:2930)

3. ዮፍታሔን አባት፥ ገለዓዳዊውም ዮፍታሔ ጽኑዕ ኃያል ሰው የጋለሞታ ሴትም ልጅ ነበረ። ገለዓድ ዮፍታሔን ወለደ (መሣ 11:12)

ገሊላ ~ Galilee: የተከለለ፣ የተገለለ፣ የተለየ... ማለት ነው። በጌታ ዘመን፣ ከሦስቱ የፍልስጥኤም ክፍሎች [ይሁዳ፣ ሰማርያ እና ገሊላ] አንዱ፥ በንፍታሌም ባለው በተራራማው አገር ገሊላ ቃዴስን፥ በኤፍሬምም ባለው በተራራማው አገር ሴኬምን፥ በይሁዳም ባለው በተራራማው አገር ኬብሮን የምትባለውን ቂርያትአርባቅን ለዩ።” (ኢያ 20:7 1 ነገ 9:11)

ገላትያ ~ Galatia: ነጭ፣ ወተት የመሰለ ማለት ነው። የቢታንያ አዋሳኝ የሆን የሮማ ግዛት የነበረ፥ በእስያም ቃሉን እንዳይናገሩ መንፈስ ቅዱስ ስለ ከለከላቸው በፍርግያና ገላትያ አገር አለፉ፤” (ሐዋ 16:6)

ገማሊ ~ Gamalli: ገማሊ፣ ግመሊ፣ ግመለኛ፣ ግመሎች ያሉት... ማለት ነው።

Gamalli- ‘ግመልከሚለው ቃል የተገኘ ስም ነው።

ሙሴ እንደ እግዚአብሔር ትእዛዝ ከፋራን ምድረ በዳ ከላካቸው፥ ከዳን ነገድ፥ የዓሚኤል አባት፥ (ዘኁ 13:12)

ገማልኤል ~ Gamaliel: ገማለ ኤል፣ ግመለ ኤል፣ የአምላክ ግመል፣ የአምላክ አገልጋይ... ማለት ነው።

ግመለእና ኤልከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። ከምናሴ ነገድ የሆነ የፍዳሱ ልጅ፥ ገማልኤል (ዘኁ 10:23)

ገማርያ ~ Gemariah: ገማረ ያሕ፣ ገረመ ያሕ፣ የሕያው ድንቅ ሥራ፣ አስገራሚ ክንውንማለት ነው። የኬልቅያስ ልጅ፥ አይሁድ በስደት በነበሩበት ዘመን፥ የኤርሚያስን ደብዳቤ አድራሽ ነበር፥ ኤርምያስ የይሁዳ ንጉሥ ሴዴቅያስ ወደ ባቢሎን ንጉሥ ወደ ናቡከደነፆር ወደ ባቢሎን በላካቸው በሳፋን ልጅ በኤልዓሣና በኬልቅያስ ልጅ ገማርያ እጅ ደብዳቤውን እንዲህ ሲል ላከው።” (ኤር 29:3)

ገሞራ ~ Gomorrah: መስመጥ፣ መጥለቅማለት ነው። ከአምስቱ የሲዶን ከተሞች አንዱ፥ የከነዓናውያንም ወሰን ከሲዶን አንሥቶ ወደ ጌራራ በኩል ሲል እስከ ጋዛ ድረስ ነው ወደ ሰዶምና ወደ ገሞራ ወደ... ነው። (ዘፍ 10:19 13:10 19:2428)

ገሪዛን ~ Gerizim: ገራዥ፣ ቆራጭማለት ነው። አምላክህም እግዚአብሔር ትወርሳት ዘንድ አንተን ወደምትሄድባት ምድር ባገባህ ጊዜ፥ በረከቱን ገሪዛን ተራራ መርገሙንም በጌባል ተራራ ታኖራለህ። (ዘዳ 11:29)

ገበታ ~ Gabbatha Bigthan: ጉብታ፣ ገበታ፣ መድረክ፣ ችሎት፣ አደባባይ... ማለት ነው።

. ማዕድ፣ የምግብ ጠረጴዛ፥ እነዚህም ሁለት ነገሥታት ክፋትን ያደርጉ ዘንድ በልባቸው ያስባሉ፥ በአንድ ገበታ ተቀምጠው ሐሰት ይናገራሉ ...” (ዳን 11:27)

አደባባይ፥ ጲላጦስ በጌታ ላይ ለመፍረድ ችሎት የተቀመጠበት፥ ጲላጦስም ይህን ነገር ሰምቶ ኢየሱስን ወደ ውጭ አወጣው፥ በዕብራይስጥም ገበታ በተባለው ጸፍጸፍ በሚሉት ስፍራ በፍርድ ወንበር ተቀመጠ (ዮሐ 1913)

       ገበታ / Bigthan: በጌታ፣ የአምላክ ስጦታ... ማለት ነው። የንጉሡ በር ከሚጠብቁት የንጉሡ ጃንደረቦች አንዱ፥ በዚያም ወራት መርዶክዮስ በንጉሡ በር ተቀምጦ ሳለ ደጁን ከሚጠብቁት ከንጉሡ ጃንደረቦች ሁለቱ ገበታ ታራ ተቈጡ፥ እጃቸውንም በንጉሡ በአርጤክስስ ላይ ያነሡ ዘንድ ፈለጉ።” (አስ 2:21)

ገባቶን ~ Gibbethon: ት፣ ዳገት፣ ኮረብታ... ማለት ነው። ለነገደ ዳን የተሰጠ፥ የቦታ ስም፥ አቃሮን፥ ኢልተቄ፥ ገባቶን ባዕላት፥” (ኢያ19:44)

ገባዖን ~ Geba, Gibeon: ገብ፣ ጉበን፣ በር፣ የከተማ መግቢያ፣ ኬላ፣ ድንበር፣ ገበያ፣ ግባት፣ ዳገታማ ቦታ... ማለት ነው። [ተዛማች ስሞች- ጊብዓ፣ ጌቤ] ጉበንከሚለው ቃል የተገኘ ስም ነው።

       ገባዖን / Geba: የብንያም ከተማ፥ (2 ሳሙ 525) (2 ነገ 23:8 ነህ 11:31)

       ገባዖን / Gibeon: (ኢያ 93-15)

ገብርኤል ~ Gabriel: ገብረ ኤል፣ የጌታ አገልጋይ፣ የእግዚአብሔር ሠራተኛ፣ ገብረ አምላክ፣ ገብረ እግዚአብሔር ማለት ነው።

Gabriel: ገብረ እና ኤል ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ የመልአክ ስም ነው።

[“የእግዚአብሔር ሰውማለት ነው / መቅቃ]

. ነቢዩ ዳንኤል፥ ገና በጸሎት ሲናገር አስቀድሞ በራእይ አይቶት የነበረው ሰው፥ (ዳን 816) (ዳን 9:21)

. የጌታ ኢየሱስ እና የመጥምቁ ዩሐንስን መፀነስ ያበሠረ፥ መልአኩም መልሶ፦ እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ፥ እንድናገርህም ይህችንም የምሥራች እንድሰብክልህ ተልኬ ነበር፤ (ሉቃ 19)

ገነት ~ Garden: ጋርድ ደን፣ በደን የተጋረደ... ማለት ነው። (ተገን፣ ተገነ፣ ገነት ተብሎም ይተረጎማል።) [ተዛማጅ ስም- ጎናት]

Garden -ጋረደ እና ደን ከሚሉ ቃላት የመጣ ነው።

የአዳምና ዋን መኖሪያ፥ እግዚአብሔር አምላክም በምሥራቅ በዔድን ገነት ተከለ የፈጠረውንም ሰው ከዚያው አኖረው። (ዘፍ 289)

ገንዘብ ~ Mammon: ሀብት፣ ገንዘብማለት ነው። የጣዖት ስም፥ ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚቻለው ማንም የለም፤ ወይም አንዱን ይጠላል ሁለተኛውንም ይወዳል፤ ወይም ወደ አንዱ ይጠጋል ሁለተኛውንም ይንቃል፤ ለእግዚአብሔርና ገንዘብ መገዛት አትችሉም። (ማቴ 6:24 ሉቃ 16:9)

ገዓል ~ Gaal: ጥላቻ፣ ቅያሜማለት ነው። የአቤድም ልጅ፥ የሴኬም ችን አስተባብሮ በአቢመሌክ ላይ ለጦርነት የተነሣ፥ ነገር ግን በውጊያው ተሸንፎ ወደ መጣበት አገር ሸሸ፥ የአቤድም ልጅ ገዓል ከወንድሞቹ ጋር መጥቶ ወደ ሴኬም ገባ የሴኬምም ሰዎች ታመኑበት።” (መሣ 9:1)

ገዓስ ~ Gaash: ውሽንፍር፣ ነጎድጓድ ማለት ነው። ተራራማው የኤፍሬም አገር፥ ኢያሱ የተቀበረበት፥ በተራራማውም በኤፍሬም አገር ገዓስ ተራራ በሰሜን ባለችው በርስቱ ዳርቻ በተምናሴራ ቀበሩት። (ኢያ 24:30 መሣ 2:9)

ጉማሬ ~ Behemoth: ትልቅ አውሬ ማለት ነው። በሬ የመሰለ፥ ትልቅ አውሬ፥ ከአንተ ጋር የሠራሁትን ጉማሬ እስኪ፥ ተመልከት እንደ በሬ ሣር ይበላል።” (ኢዮ 40:15-24)

ጉር ~ Gur: ጎር፣ ጎራ፣ ምሽግ፣ መቀመጫ፣ መኖሪያ... ማለይ ነው። የይሁዳ ንጉሥ አካዝያስ የኢዩ አሽከሮች ወግተው የገደሉበት፥ የይሁዳ ንጉሥ አካዝያስ ያንን ባየ ... ጉር ዐቀበት ላይ ወጉት። ወደ መጊዶም ሸሸ፥ በዚያም ሞተ። (2 ነገ 9:27)

ጉርበኣል ~ Gur-baal: ባለ ጎራ፣ ባለ መኖሪያ... ማለት ነው። ረብ አገር ያለ ቦታ፥ እግዚአብሔርም በፍልስጥኤማውያንና ጉርበኣል በሚኖሩ ዓረባውያን በምዑናውያንም ላይ ረዳው።” (2 ዜና 26:7)

ጉኒ ~ Guni: ገን፣ ተገን፣ ግርጃማለት ነው።

1. የንፍታሌም ልጅ፥ የንፍታሌምም ልጆች ያሕጽኤል፥ ጉኒ ዬጽር፥ ሺሌም።” (ዘፍ 46:24 1 ዜና 7:13)

2. የአብዲኤል፥ የአባቶቻቸውም ቤቶች አለቃ ጉኒ ልጅ የአብዲኤል ልጅ ወንድም ነበረ።” (1 ዜና 5:15)

ጉዲኤል ~ Gaddiel, Geuel: ጋዲ ኤል፣ ገደ ኤል፣ የጌታ ሀብት፣ አምላክ የረዳው... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ጋዲ፣ ጋድ]

ገደእና ኤልከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-

       ጉዲኤል / Gaddiel: ሙሴ አገሩን እንንዲሰልሉ ከላካቸው፣ ከዛብሎን ነገድ፣ የሰዲ ልጅ፥ ጉዲኤል (ዘኁ 13:10)

        ጉዲኤል / Geuel: የማኪ ልጅ፥ ከጋድ ነገድ የማኪ ልጅ ጉዲኤል” (ዘኁ 13:15)

ጉዲኤል ~ Geuel: ገደ ኤል፥ የአምላክ ቸርነት፥ ካሳ፥ ይቅርታ... ማለት ነው። የጋዳዊው ሰላይ፥ የሚልኪ ልጅ፥ (ዘኊ 13:15) ከጋድ ነገድ የማኪ ልጅ ጉዲኤል

ጉድጎዳ ~ Gudgodah: ጓድ፣ ጓዳ ማለት ነው። ከዚያም ወደ ጉድጎዳ ተጓዙ ከጉድጎዳም ወደ ውኃ ፈሳሾች ... ተጓዙ። (ዘዳ 10:7)

ጊላላይ ~ Gilalai: ገሊላዊ፣ ግልል፣ የተገለለ፣ የተለየ... ማለት ነው። የእስራኤልን ቅጥር ካቆሙ ካህናት፥ የአንዱ ልጅ፥ ወንድሞቹም ሸማያ፥ ኤዝርኤል፥ ሚላላይ፥ ጊላላይ መዓይ፥ ናትናኤል፥ ይሁዳ፥ አናኒ የእግዚአብሔርን ሰው የዳዊትን ... ዕዝራ በፊታቸው ነበረ። (ነህ 12:36)

ጊልቦዓ ~ Gilboa: ጋለባ፣ ጋላቢ... ማለት ነው። የተራራ ስም፥ ፍልስጥኤማውያንም ተሰብስበው መጡ በሱነምም ሰፈሩ ሳኦልም እስራኤልን ሁሉ ሰበሰበ፥ ጊልቦዓ ሰፈሩ።” (1 ሳሙ 28:4)

ጊሎ ~ Giloh: ‘ስደተኛማለት ነው። በተራራማው የይሁዳ አገር የሚገኝ ከተማ፥ ዓናብ፥ ኤሽትሞዓ፥ ዓኒም፥ ጎሶም፥ ሖሎን፥ ጊሎ አሥራ አንድ ከተሞችና መንደሮቻቸው።” (ኢያ 15:51)

ጊምዞ ~ Gimzo: ለምማለት ነው። ፍልስጥኤማውያን በይሁዳ ከተሞች አደጋ ጥለው ከተቆጣጠሯቸው ከተሞች አንዱ፥ ደግሞም ... ቤትሳሚስንና ኤሎንን፥ ግዴሮትንም፥ ሦኮንና መንደሮችዋን፥ ተምናንና መንደሮችዋን፥ ጊምዞንና መንደሮችዋን ወስደው በዚያ ተቀምጠው ነበር።” (2 ዜና 28:18)

ጊሽጳ ~ Gispa: ጉሰማ፣ መጎሰም፣ መድቃት መምታት... ማለት ነው። ከምርኮ ከተመለሱ በናታም ከተቀመጡ፥ ናታኒምም በዖፌል ተቀምጠው ነበር ሲሐና ጊሽጳ በናታኒም ላይ ነበሩ።” (ነህ 11:21)

ጊብዓ ~ Gibea, Gibeah: ገበያ፣ መገበያያ ቦታ፣ ከፍ ያለ ቦታ፣ ዳገት፣ ኮረብታማ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ገባዖን፣ ጌቤ]

[ጉብታ ወይም ኮረብታ ማለት ነው / መቅቃ]

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሁለት ሰዎች እና ሁለት ቦታዎች አሉ።

       ጊብዓ / Gibea: የሱሳ ልጅ፥ (1 ዜና 249)

       ጊብዓ / Gibeah:

1. ኢያሱ የባልጩት መቍረጫ ሠርቶ የእስራኤልን ልጆች የገረዘበት ስፍራ ስም፥ ኢያሱም የባልጩት መቍረጫ ሠርቶ የግርዛት ኮረብታ በተባለ ስፍራ የእስራኤልን ልጆች ገረዘ።” (ኢያ 5:3) ዮቅድዓም፥ ዛኖዋሕ፥ ቃይን፥ ጊብዓ ተምና አሥር ከተሞችና መንደሮቻቸው” (ኢያ 15:57)

2. የካሌብ ልጅ፥ (1 ዜና 2:49)

3. (1 ሳሙ 1315)

ጋሊም ~ Gallim: ክምር ማለት ነው። ልጁን ሚላካን፥ የዳዊትን ሚስት፣ የሰጠው ሰው አገር፥ ሳኦል ግን የዳዊትን ሚስት ልጁን ሜልኮልን አገሩ ጋሊም ለነበረው ለሌሳ ልጅ ለፈልጢ ሰጥቶ ነበር። (1 ሳሙ 25:44)

ጋላል ~ Galal: ግልል፣ ግልግል፣ ዕረፍትማለት ነው።

1. ሌዋዊው፥ ከአሳፍ ልጆች አንዱ፥ በቅበቃር፥ ኤሬስ፥ ጋላል የኣሳፍ ልጅ የዝክሪ ልጅ የሚካ ልጅ መታንያ” (1 ዜና 9:15)

2. በቅበቃር፥ ኤሬስ፥ ጋላል የኣሳፍ ልጅ የዝክሪ ልጅ የሚካ ልጅ መታንያ” (1 ዜና 9:16)

3. የኤዶታም ልጅ፥ በጸሎትም ጊዜ ምስጋናን የሚቀነቅኑ ... የነበረ በቅበቃር፥ የኤዶታምም ልጅ ጋላል ልጅ የሳሙስ ልጅ አብድያ። (ነህ 11:17)

ጋሌማት ~ Alameth: አለማት ... [ተዛማጅ ስም- ዓሌሜት] ዓለማት’- ጋሌማት

በዚህ ስም የሚታወቁ ሦስት ሰዎች እና አንድ ቦታ አሉ።

. ለብንያም ነገድ የተሰጠ የቦታ ስም፥ (1 ዜና 6:60)

. የቤኬር ልጅ፥ ዓሌሜት- (1 ዜና 78) የዕራ ልጅ፥ ዓሌሜት- (1 ዜና

9:42) የይሆዓዳ ልጅ፥ ዓሌሜት- (1 ዜና 8:36)

ጋልዮስ ~ Gallio: ባለወተት፣ በወተት ያደገ ማለት ነው። በአካይያ አገረ ገዥ የነበረ፥ ጋልዮስ በአካይያ አገረ ገዥ በነበረ ጊዜ፥ አይሁድ በአንድ ልብ ሆነው በጳውሎስ ላይ ተነሡ፥ ወደ ፍርድ ወንበርም አምጥተው። (ሐዋ 18:12)

ጋሙል ~ Gamul: ልግት፣ ካሳ ክፍያ ማለት ነው። በቤተ መቅደስ ያገለግሉ ከነበሩ ካህናት፥ የሀያ ሁለተኛው ምድብ አለቃ፥ ሀያኛው ለኤዜቄል፥ ሀያ አንደኛው ለያኪን፥ ሀያ ሁለተኛው ጋሙል” (1 ዜና 24:17)

ጋሜር ~ Gomer: ፍጻሜ፣ መጨረሻ ማለት ነው።

1. የያፌት ትልቁ ልጅ፥ የያፌት ልጆች ጋሜር ማጎግ፥ ማዴ፥ ያዋን፥ ይልሳ፥ ቶቤል፥ ሞሳሕ፥ ቴራስ ናቸው።” (ዘፍ 10:23)

2. የሆሴ ሚስት፥ እርሱም ሄዶ የዴቤላይምን ልጅ ጎሜር አገባ እርስዋም ፀነሰች ወንድ ልጅንም ወለደችለት። (ሆሴ1:3)

ጋሴም ~ Gazzam: ማጥፋት፣ ማውደምማለት ነው። ከግዞት ከተመለሱ፥ የጋሴም ልጆች ይገኙበታል፥ ጋሴም ልጆች፥ የዖዛ ልጆች፥ የፋሴሐ ልጆች፥” (ዕዝ 2:48 ነህ 7:51)

ጋሬብ~ Gareb: ገረባ፣ ሽፋን፣ ጋቢ፣ ኩታ፣ ነጠላ ማለት ነው።

1. ከዳዊት ኃያላን አንዱ፥ ጋሬብ ኬጢያዊው ኦርዮ ሁሉ በሁሉ ሠላሳ ሰባት ናቸው።” (2 ሳሙ 23:39)

2. በኢየሩሳሌም አቅራቢያ የነበረ ኮረብታ፥ የተለካበትም ገመድ ወደ ጋሬብ ኮረብታ በቀጥታ ወደ ፊት ይሄዳል፥ ወደ ጎዓም ይዞራል። (ኤር 31:39)

ጋቤር ~ Gibbar: ጊባር፣ ገብር፣ ገባር፣ አገልጋይ፣ ሠራተኛ... ማለት ነው።

[ተዛማጅ ስሞች- ገብርኤል፣ ጋቤር]

የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ወደ ባቢሎን ከማረካቸው ምርኮኞች ወደ ኢየሩሳሌምና ወደ ይሁዳ ወደ እየከተማቸው ከተመለሱት የአገር ልጆች፥ (ዕዝ 2 20)

ጋትሔፍር ~ Gittah-hepher: ቁፋሮማለት ነው። ዳብራትም ወጣ፥ ወደ ያፊዓም ደረሰ ከዚያም በምሥራቅ በኩል ወደ ጋትሔፍር ወደ ዒታቃጺን አለፈ ወደ ሪምንና ወደ ኒዓ ወጣ። (ኢያ 19:13)

ጋዛ ~ Gaza, Gazathites: ገዛ፣ ገዥ፣ ተቆጣጣሪ፣ አስተዳደራዊ ቦታ፣ ጠንካራ ምሽግ ማለት ነው። ጋዛይት፣ ጋዛውያን፣ የጋዛ አገር ሰዎች

ገዛከሚለው ቃል የተገኘ ስም ነው።

[ምሽግ ማለት ነው / መቅቃ]

       ጋዛ /Gaza: የከነዓናውያን ወሰን፥ ከፍልስጤማውያን ከተሞች አንዱ፥ (ገላ 10:19)

       ጋዛ / Gazathites: የጋዛ ነዋሪዎች፥ (ኢያ 133)

ጋዜዝ ~ Gazez: ዔፋ ለካሌብ የወለደችለት፥ (1 ዜና 2:46) የካሌብም ቁባት ዔፋ ሐራንን፥ ሞዳን፥ ጋዜዝ ወለደች

ጋይ ~ Ai, Giah, Ije-abarim, Shaashgaz: የአስከሬን ክምርማለት ነው።

1. በኢየሩሳሌም በስተሰሜን የሚገኝ ከተማ፥ ኢያሱም ከቤቴል በምሥራቅ በኩል በቤትአዌን አጠገብ ወዳለችው ወደ ጋይ ሰዎችን ... (ኢያ 7:2 8:9)

2. የአሞናውያን ከተማ፥ ሐሴቦን ሆይ፥ ጋይ ፈርሳለችና አልቅሺላት እናንተም የረባት ሴቶች ልጆች ሆይ፥ ... መካከል ተርዋርዋጡ። (ኤር 49:3)

       ጋይ / Giah: ፏፏቴማለት ነው። በሳሙኤል መጽሐፍ የተጠቀሰ ቦታ፥ ኢዮአብና አቢሳም አበኔርን አሳደዱ በገባዖንም ምድረ በዳ መንገድ ጋይ ፊት ለፊት እስካለው እስከ አማ ኮረብታ ድረስ ... ፀሐይ ጠለቀች። (2 ሳሙ 2:24)

       ጋይ / Ije-abarim: የአብርሃም ባድማማለት ነው። እስራኤላውያን በምድረ ባዳ ሲንከራተቱ ካረፉባቸው፥ የሞአባውያን አዋሳኝ፥ ከኦቦትም ተጕዘው በሞዓብ ዳርቻ ባለው ጋይ ሰፈሩ። (ዘኊ 33:44)

       ጋይ / Shaashgaz: የውበት ተገዥ ማለት ነው። የንጉሥ አርጤክስ ጃንደረባ፥ ማታም ትገባ ነበር፥ ሲነጋም ተመልሳ ወደ ሁለተኛው ሴቶች ቤት ቁባቶችን ወደሚጠብቅ ወደ ንጉሡ ጃንደረባ ወደ ጋይ ትመጣ ነበር ... (አስ 2:14)

ጋይዮስ ~ Gaius: ባለጠጋ ምድራዊ ጌታ ማለት ነው።

1. መቄዶንያዊው፥ ጳውሎስ በጉዞው ዘንድ አገልጋይ የነበረ፥ ከተማውም በሙሉው ተደባለቀ፥ የመቄዶንያም ሰዎች የጳውሎስን ጓደኞች ጋይዮስንና አርስጥሮኮስን ከእነርሱ ጋር ... ወደ ጨዋታ ስፍራ ሮጡ። (ሐዋ 19:29)

2. ከጳውሎስ ጋር ከቆሮንቶስ ወደ ኢየሩሳሌም የሔደ፥ የደርቤን ሰው፥ የሸኙትም የቤርያው ... አርስጥሮኮስና ሲኮንዱስ የደርቤኑም ጋይዮስ ጢሞቴዎስ የእስያ ሰዎችም ቲኪቆስ ጥሮፊሞስም ነበሩ፤ (ሐዋ 20:4)

ጋይዳድ ~ Irad: ሯጭ ማለት ነው። ከቀደሙ አባቶች አንዱ፥ የሜኤል አባት፥ የቃየን የልጅ ልጅ፥ ሄኖሕም ጋይዳድ ወለደ ጋይዳድም ሜኤልን ወለደ ሜኤልም ማቱሣኤልን ወለደ ማቱሣኤልም ላሜሕን ወለደ። (ዘፍ 4:18)

ጋዲ ~ Gaddi, Gadi: ጋዲ፣ ገዴ፣ ገደኛ፣ ድለኛ፣ እጣ የወጣለት፥ የጋድ ወገን፣ የጋድ አገር ሰው... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ጉዲኤል፣ ጋድ]

ገድከሚለው ቃል የመጣ ስም ነው።

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች: -

       ጋዲ / Gaddi: የሱሲ ልጅ፥ የከነዓን ምድር እንዲሰልሉ ሙሴ ከላካቸው የምናሴ ወገን፥ (ዘኁ 1311)

       ጋዲ / Gadi: የምናሔ አባት፣ የእስራኤል ንጉሥ፥ (2 ነገ 151417)

ጋዴዮን ~ Gideoni: ገደ ዓይኔ፥ ድለኛ ይኖቸ... ማለት ነው። ብንያማዊው፥ የአቢዳን አባት፥ ከብንያም ጋዴዮን ልጅ አቢዳን፥ ከዳን የአሚሳዳይ ልጅ አኪዔዘር፥” (ዘኊ1:11 7:6065 10:24)

ጋድ ~ Gad: ጋድ፣ ጎድ፣ ጉድ፣ ገድ፣ ድል፣ እጣ ፈንታ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ጉዲኤል፣ ጋዲ]

ገድከሚለው ቃል የመጣ ስም ነው።

[መልካም ዕድል ማለት ነው / መቅቃ]

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች: -

1. ልያ ለያቆብ የወለደችለት፥ ልያም። ጉድ አለች ስሙንም ጋድ ብላ ጠራችው” (ዘፍ 3011-13)

2. በንጉሥ ዳዊት ዘመን የነበረ ነቢይ፥ (1 ዜና 29:29) (2 ዜና 29:25) (1 ሳሙ 22:5)

ጌልገላ ~ Gilgal: ግልግል፣ ዕረፍት፣ ሸክምን ማቅለል፣ ከባርነት መላቀቅ፣ ነጻነትን ማግኘት... ማለት ነው።

Gilgal- ግልግል ከሚለው ቃል የተገኘ ስም ነው። የቃሉ ምንጭ ደግሞ ገላገለየሚለው ግስ ነው።

. ከግብፅ ወጥተው ዮርዳኖስን ፈጽመው ሲሻገሩ የሰፈሩበት ቦታ፥ እግዚአብሔርም ኢያሱን። ዛሬ የግብፅን ነውር ከእናንተ ላይ አንከባልያለሁ አለው፤ ስለዚህ የዚያ ስፍራ ስም እስከ ዛሬ ድረስ ጌልገላ ተብሎ ተጠራ። (ኢያ 59)

. (ኢያ 96)

ጌራ ~ Gera: ጎራ፣ ጠበኛ፣ ጠላትማለት ነው።

1. የብንያም ልጅ፣ የቤላ ልጅ፥ (1 ዜና 8:457) “ጌራ አቢሁድ፥ አቢሱ፥ ናዕማን፥ አሖዋ፥ ጌራ

2. ብንያማዊው ፈራጅ፣ የናዖድ አባት፥ የእስራኤልም ልጆች ወደ እግዚአብሔር ጮኹ እግዚአብሔርም ብንያማዊውን ጌራ ልጅ ናዖድን ግራኙን ሰው አዳኝ አስነሣላቸው ...” (መሣ 3:15)

3. ዳዊትን የተሳደበ፣ የሳሚ አማት፥ ንጉሡ ዳዊትም ወደ ብራቂም መጣ እነሆም፥ ሳሚ የሚባል ጌራ ልጅ ከሳኦል ቤተ ዘመድ የሆነ አንድ ሰው ከዚያ ወጣ፥ እየሄደም ይረግመው ነበር።” (2 ሳሙ 16:5 19:1618)

ጌራራ ~ Gerar: የመቆያ ቦታ፣ መኖሪያማለት ነው። ከጋዛ በስተደቡብ የነበረ፥ በጣም ጥንታዊ ከተማ፥ የከነዓናውያንም ወሰን ከሲዶን አንሥቶ ወደ ጌራራ በኩል ሲል እስከ ጋዛ ድረስ ነው ወደ ሰዶምና ወደ ገሞራ፥ ወደ አዳማና ወደ ሰቦይም በኩልም ሲል እስከ ላሣ ድረስ ነው። (ዘፍ 10:19 20:1 26:17)

ጌርሳ ~ Gershom: እንግ መጻተኛማለት ነው።

1. ሙሴ ከሲፖራ የወለደው፥ ወንድ ልጅም ወለደች። በሌላ ምድር መጻተኛ ነኝ ሲል ስሙን ጌርሳ ብሎ ጠራው። (ዘጸ 2:2218:3)

ጌርጌሳውያን ~ Girgashite: ከስግደት የተመለሱማለት ነው። የከነዓን አምስተኛ ልጅ ወገኖች፥ ጌርጌሳውያንንም፥ ኤዊያውያንንም” (ዘፍ 10:17)

ጌርጌሴኖ ~ Gadarenes: የገደራ ሰዎችማለት ነው። ገረራማለት ደግሞ ግድግዳ፣ ግንብ፣ አጥር ማለት ነው። የአገር ስም፥ ወደ ባሕር ማዶም ወደ ጌርጌሴኖ አገር መጡ።” (ማር 5:1 ሉቃ 8:2637)

ጌሹር ~ Geshur: መሻገሪያ፣ ድልድይማለት ነው። በሶርያ በስተሰሜን የምትገኝ፥ ትንሽ ግዛት፥ እኔ ባሪያሕ በሶርያ ጌሹር ሳለሁ። እግዚአብሔር ወደ ኢየሩሳሌም ቢመልሰኝ ለእግዚአብሔር መሥዋዕት አቀርባለሁ ... (2 ሳሙ 15:8)

ጌበር ~ Geber: ገበር፣ ገባር ሠራተኛ፣ አገልጋይ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች - ገብርኤል፣ ጋቤር]

ገበረከሚለው ግስ የመጣ ስም ነው።

የኡሪ ልጅ፣ በገለዓድ አገር ሹም የነበረ፥ (1 ነገ 419)

ጌባል ~ Gebal: ወሰንማለት ነው። የወደብ ከተማ፥ በአንቺ ውስጥ የነበሩ ጌባል ሽማግሌዎችና ጥበበኞችዋ ስብራትሽን ይጠግኑ ነበር ... (ሕዝ 27:9)

ጌቤ ~ Gabbai: ገባይ፣ ገበያ፣ ገቢ የሚያስገኝ፣ አስገባሪ፣ ቀራጭ... ማለት ው። [ተዛማጅ ስሞች- ገባዖን፣ ጊብዓ፣ ጊብዓ]

በነህምያ ዘመን፥ ከግዞት መልስ፥ ከይሁዳና ከብንያም ልጆች በኢየሩሳሌም የተቀመጡ፥ (ነህ 118)

ጌታችንሆይ፥ና ~ Maranatha: ማረን አንተ፣ ምራን አንተ፣ ይቅር በለን፣ ነጻ አውጣን... ማለት ነው።

Maranatha- ‘ምራንእና አንተከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ቃል ነው። ጳውሎስ ወደ ቆሮንጦስ በጻፈው ሰላምታ መደምደሚያ ላይ የተናገረው ቃል፥ ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን የማይወድ ቢኖር የተረገመ ይሁን። ጌታችን ሆይ፥ ” (1 ቆሮ 16:22)

ጌቴም ~ Gittaim: ጋጣም፣ መንታ የወይን መጭመቂያማለትነው። የከተማ ስም፥ ብኤሮታውያንም ወደ ጌቴም ሸሽተው ነበር፥ እስከ ዛሬም ድረስ በዚያ ተጠግተው ነበር።” (2 ሳሙ 4:3 ሳሙ 11:33)

ጌቴሴማኒ ~ Gethseman: ጌታ ስመኒ፣ የጌታ ስም፣ ስመ አምላክ፣ መልካም ስም፣ ቅዱስ ስም... ማለት ነው። (ዘይት ማለት ነው። ተብሎም ይተረጎማል ኪወክ / )

ጌታ እና ስም ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው።

ጌታ የጸለየበት የቦታ ስም፥ የወይን አትክልት ያለበት፥ (ማር 1432)

ጌቴር ~ Gether: ገጠር ማለት ነው። የአራም በሦስተኛ ተራ ያለ ልጅ፥

የአራምም ልጆች ዑፅ፥ ሁል፥ ጌቴር ሞሶሕ ናቸው። (ዘፍ 10:23)

ጌት ~ Gath: ጋት፣ ጋጥ፣ ጓዳ... ማለት ነው። (የወይን መጭመቂያ ተብሎም ይተረማል።)

. የእግዚአብሔር ታቦት በፍላስኤማውያን ተማርኮ የተወሰደበት ከተማ፥ (1 ሳሙ 589)

. የአቢዳራ አገር፥ (2 ሳሙ 6:11)

. (ኢያ 11:22)

ጌትያውን ~ Gittites: ጌታይት፣ ጌታውያን፣ የጌት አገር ሰዎች... ማለት ነው።

ጌትከሚለው የቦታ ስም የመጣ ስም ነው።

ንጉሥ ዳዊትን ከተከተሉ ሰዎች መካከል ጌትያውን ይገኙበታል፥ (2 ሳሙ 1518 19)

ጌንሴሬጥ ~ Gennesaret: ገነተ መሳፍንትማለት ነው። ሻግረውም ወደ ጌንሴሬጥ ምድር መጡ። (ማቴ 14:34 ማር 6:53)

ጌንባት ~ Genubath: ቀማኛማለት ነው። የአዳድ ልጅ፥ እናቱ የቴቄምናስ እኅት ናት፥ ያደገው በፈርዖን ቤተመንግሥት ነው፥ የቴቄምናስ እኅት ጌንባት ወለደችለት፥ ቴቄምናስም በፈርዖን ቤት አሳደገችው ጌንባትም በፈርዖን ቤት በፈርዖን ልጆች መካከል ነበረ” (1 ነገ 11:20)

ጌዝር ~ Gazer: ግዝር፣ ግዝረት፣ ከፋፋይማለት ነው። በዳዊት ዘመን፥ የፍልስኤማውያን የነበረ ቦታ፥ ዳዊትም እግዚአብሔር እንዳዘዘው አደረገ ከገባዖንም እስከ ጌዝር ድረስ ፍልስጥኤማውያንን መታ።” (2 ሳሙ 5:25 1 ዜና 14:16)

ጌዝር ~ Gezer: አፋፍ፣ ኮረብታማለት ነው። ጥንታዊ፥ የከነናውያን መናገሻ፥ በዚያን ጊዜም ጌዝር ንጉሥ ሆራም ለኪሶን ለመርዳት ወጣ ኢያሱም አንድ ስንኳ ሳይቀር እርሱንና ሕዝቡን መታ። (ኢያ 10:33 12:12)

ጌዴል ~ Giddel: ድል ትልቅ፣ ከፍተኛ... ማለት ነው። ከባቢሎን ምርኮ ከተመለሱ የጌዴል ልጆች ይገኙበታል፥ ጌዴል ልጆች፥ የጋሐር ልጆች፥ የራያ ልጆች፥” (ዕዝ 2:47 ነህ 7:49)

ጌዴልያ ~ Igdaliah: ያሕ፣ የሕያው ገድል፣ ያምላክ ታላቅ ሥራ... ማለት ነው። የአንድ ነቢይ ስም፥ ወደ እግዚአብሔርም ቤት በበረኛው በሰሎም ልጅ በመዕሤያ ጓዳ በላይ ባለው በአለቆች ጓዳ አጠገብ ወዳለው ወደ እግዚአብሔር ሰው ወደ ጌዴልያ ልጅ ወደ ሐናን ልጆች ጓዳ አገባኋቸው። (ኤር 35:4)

ጌዴዎን ~ Gideon: ገደ ይን፣ ድለኛ ይኖች... ማለት ነው። የአቢዔዝራዊው፥ የኢዮአስ ትንሹ ልጅ፥ የእግዚአብሔርም መልአክ መጥቶ በዖፍራ ባለችው ለአቢዔዝራዊው ለኢዮአስ በነበረችው በአድባሩ ዛፍ በታች ተቀመጠ ልጁም ጌዴዎን ከምድያማውያን ለመሸሸግ በወይን ... (መሣ 6:15)

ጌድሶን፣ ጌርሳም ~ Gershon: መጻተኛማለት ነው።

1. ጌድሶን፥ የሌዊ ልጆች ጌድሶን ቀዓት፥ ሜራሪ። (1 ዜና 6:1617 20436271 15:7)

2. ከባቢሎን ምርኮ ከተመለሱ፥ ፊንሐስ ልጅ፥ ጌርሶን፥ ከፊንሐስ ልጆች ጌርሶን ከኢታምር ልጆች ዳንኤል፥ ከዳዊት ልጆች ሐጡስ፥ ከሴኬንያ ልጆች፥ (ዕዝ 8:2)

ጌድር ~ Geder: ገደራ፣ ግንብ፣ አጥር፣ ድንበር... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ጌዶር]

ገደረከሚለው ግስ የመጣ ስም ነው። ኢያሱ ርስት አድርጎ ለእስራኤል ነገድ በሰጣት ምድር፥ የእስራኤል ልጆች ከመቱአቸው ሠላሳ አንድ የምድር ነገሥታት፥ (ኢያ 1214)

ጌዶር ~ Geder, Gedor: ገደራ፣ ግንብ፣ አጥር፣ ድንበር... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ጌድር]

ገደረከሚለው ግስ የመጣ ስም ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ:-

       ጌዶር / Geder:

1. በደቡብ በኩል በምድራቸው ዳርቻ አጠገብ እስከ ኤዶምያስ ድንበር ካሉት ከይሁዳ ልጆች ነገድ ከተሞች፥ (1 ዜና 4:39)

2. የፋኑኤል ልጅ፥ (1 ዜና 4:4)

       ጌዶር / Gedor: (ኢያ 15:58)

ግርግም ~ Manger: ግርግም የከብቶች ምግብ የሚቀርብበት ገበታ በረት፣ ጋጥ፣ ማእድ ቤት፣ አጥር... በረት ግርግምን፥ ግርግም በረትን ይገልጻል።

. ጌታ እንደተወለደ የተኛበት ቦታ፥ የበኵር ልጅዋንም ወለደች፥ በመጠቅለያም ጠቀለለችው፤ በእንግዶችም ማደሪያ ስፍራ ስላልነበራቸው ግርግም አስተኛችው” (ሉቃ 2:7 12 16...)

. ጐሽ ያገለግልህ ዘንድ ይታዘዛልን? ወይስ ግርግም አጠገብ ያድራልን?” (ኢዮ 39:9)

. ግርግም፥ የቤት እንስሳ ማደሪያ መሆኑንም ከሚከተለው ጥቅስ እንገነዘባለን:- ጌታም መልሶ፦ እናንተ ግብዞች፥ ከእናንተ እያንዳንዱ በሰንበት በሬውን ወይስ አህያውን ግርግሙ ፈትቶ ውኃ ሊያጠጣው ይወስደው የለምን?” (ሉቃ 13:15)

ግቤር ~ Gebim: የአንበጣ መንጋማለት ነው። በኢየሩሳሌም በስተምሥራቅ የሚገኝ ከተማ፥ መደቤና ሸሽታለች ግቤር የሚኖሩ ቤተ ሰቦቻቸውን አሽሽተዋል።” (ኢሳ 10:31)

ግብዣ ~ Feast: ፌሽታ፣ ፌስታ፣ ደስታ፣ ድግስ፣ ግብዣ፣ በዓል... ማለት ነው። [ተለዋጭ ስሞች- ማዕድ፣ ሰርግ፣ በዓል]

. አብርሃም ያደረገው ድግስ፥ “...አብርሃምም ይስሐቅን ጡት ባስጣለበት ቀን ትልቅ ግብዣ አደረገ። (ዘፍ 21:8) (ሉቃ 15:23)

. ማዕድ- (ዘፍ 193) በዓል- (መሣ 14:10) ሰርግ- (ዘፍ 29:22)

ግብፅ ~ Egypt: ጨቋኝ፣ የመከራ አገርማለት ነው። በስሜን ምሥራቅ አፍሪቃ የሚገኝ አገር፥ የካም አገር፥ እስራኤልም ወደ ግብፅ ገባ፥ ያዕቆብም በካም አገር ተቀመጠ።” (መዝ 105:2327)

ግያዝ ~ Gehazi: ጋዚ፣ ገዛ፣ ገዥ፣ ግዛት፣ አስተዳደር... ማለት ነው።

ገዛከሚለው ቃል የተገኘ ስም ነው። የእግዚአብሔር ሰው የኤልሳዕ ሎሌ፥ ሎሌውንም ግያዝን፦ ይህችን ሱነማዊት ጥራ አለው።” (2 ነገ 431)

ግዮን ~ Gihon: ገዋነ፣ ወደላይ ወጣ... ማለት ነው።

1. ከገነት የሚወጣው ሁለተኛው ወንዝ፥ የሁለተኛውም ወንዝ ስም ግዮን ነው እርሱም የኢትዮጵያን ምድር ሁሉ ይከብባል (ዘፍ 2:13)

2. ጉሡም ... የጌታችሁን ባሪያዎች ይዛችሁ ሂዱ፥ ልጄንም ሰሎሞንን በበቅሎዬ ላይ አስቀምጡት፥ ወደ ግዮን አውርዱት” (1 ነገ 1:333845)

ግዴሮታይም ~ Gederothaim: ወሰን፣ ድንበር፣ ግድብ፣ ግድግዳማለት ነው። በደልዳላው የይሁዳ ክፍል የሚገኝ ከተማ፥ዓዶላም፥ ሰኰት፥ ዓዜቃ፥ ሽዓራይም፥ ዓዲታይም፥ ግዴራ፥ ግዴሮታይም አሥራ አራት ከተሞችና መንደሮቻቸው።” (ኢያ 15:36)

ጎላን ~ Golan: መጻተኛማለት ነው። የባሳን ከተማ፥ ለሌዋውያንም ወገኖች ለጌድሶን ልጆች ከምናሴ ነገድ እኩሌታ ለነፍሰ ገዳይ መማፀኛ ከተማ በባሳን ውስጥ የሆነችውን ጎላንንና መሰምርያዋን፥ በኤሽትራንና መሰምርያዋን ሁለቱን ከተሞች ሰጡአቸው።” (ኢያ 21:27)

ጎልያድ ~ Goliath: ገላት፣ ገላያት፣ ትልቅ አካል፣ ግዙፍ ሰው፣ ትልቅ ሰውነት... ማለት ነው።

ዳዊት በወንጭፍ የገደለው፣ የጌት ሰው፣ የፍልስኤማውያን ጀግና፥ (1 ሳሙ 174)

ጎልጎታ ~ Golgotha: ገለ ጎታ፣ ገላ ጎታ፣ የአካል ክምር የራስ ቅል ክምችት... ማለት ነው።

ገላእና ጎታከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ነው። ጌታን የሰቀሉበት ስፍራ፥ ትርጓሜው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሆን ጎልጎታ ወደሚባለው ስፍራ በደረሱ ጊዜም፥...” (ማቴ 2733)

ጎሶም ~ Goshen: መቅረብማለት ነው።

1. እስራኤላውያን ከግብፅ ወጥተው ከሰፈሩባቸው ቦታዎች፥ ኢያሱም ከቃዴስ በርኔ እስከ ጋዛ ድረስ ጎሶምንም ምድር ሁሉ እስከ ገባዖን ድረስ መታ።” (ኢያ 10:41)

2. ኢያሱም ከቃዴስ በርኔ እስከ ጋዛ ድረስ ጎሶምን ምድር ሁሉ እስከ ገባዖን ድረስ መታ።” (ኢያ 10:41)

ጎብ ~ Gob: ጉድጓድ ማለት ነው። በሳሙኤል መጽሐፍ የተጠቀሰ የቦታ ስም፥ ከዚህም በኋላ እንደ ገና ጎብ ላይ ከፍልስጥኤማውያን ጋር ሰልፍ ሆነ፥ ኩሳታዊውም ሴቦካይ ከራፋይም ሳፍን ገደለ። (2 ሳሙ 21:1819)

ጎቶልያ ~ Athaliah: ያሕ፣ ታላይ፣ እግዚአብሔር የበደለ... ማለት ነው።

1. የእስራኤል ንጉሥ የዘንበሪ ልጅ፥ የንጉሥ አካዝያስ እናት፥ መንገሥ በጀመረ ጊዜ አካዝያስ እናቱም ጎቶልያ የተባለች የእስራኤል ንጉሥ የዘንበሪ ልጅ ነበረች።” (2 ነገ 8:26)

2. ከምርኮ ከተመለሱ፥ የሻያ አባት፥ ከኤላም ልጆች ጎቶልያ ልጅ የሻያ፥ ከእርሱም ጋር ሰባ ወንዶች።” (ዕዝ 8:7)

3. በትውልዶቻቸው አለቆች ከነበሩ በኢየሩሳሌም ከተቀመጡ፥ የሶሴቅ ልጅ፥

ሸሃሪያ፥ ጎቶልያ ያሬሽያ፥ ኤልያስ፥ ዝክሪ፥ የይሮሐም ልጆች። (1 ዜና 8:26)

ጎቶም ~ Gatam: የተቃጠለ ሸለቆ ማለት ነው። ሳው ልጅ፣ የኤልፋዝ አራተኛ ልጅ፥ የኤልፋዝም ልጆች እነዚህ ናቸው ቴማን፥ ኦማር፥ ስፎ፥ ጎቶም ቄኔዝ” (ዘፍ 36:11 1 ዜና 1:36)

ጎቶንያል ~ Othniel: የአምላክ አንበሳ ማለት ነው። የቄኔዝ ልጅ፥ የካሌብ ወንድም፥ የካሌብ ወንድም የቄኔዝ ልጅ ጎቶንያል ያዛት ልጁንም ዓክሳን አጋባው።” (ኢያ 15:17 መሣ 1:13 3:9 1 ዜና 4:13)

ጎናት ~ Ginath: ገነት፣ ተገን፣ ተጋን፣ በአትክልት የተከለለ... ማለት ነው።

ገነትከሚለው ቃል የተገኘ ስም ነው። [ተዛማጅ ስም- ገነት] የታምኒ አባት፥ (1 ነገ 16:21 22)

ጎዓ ~ Goath: _ (ለበሬ)ማለት ነው። የኢየሩሳሌም አጎራባች፥ ከጌበር ኮረብታ ተያይዞ የሚገኝ ቦታ፥ የተለካበትም ገመድ ወደ ጋሬብ ኮረብታ በቀጥታ ወደ ፊት ይሄዳል፥ ወደ ጎዓ ይዞራል። (ኤር 31:39)

ጎዛን ~ Gozan: ግጦሽ፣ ሳር ሜዳ፥ የከብት ምግብማለት ነው። ራኤላውያን በግዞት የተወሰዱበት አገር፥ የአሦር ንጉሥ ሰማርያን ወሰደ፥ እስራኤልንም ወደ አሦር አፈለሰ፥ በአላሔና በአቦር ጎዛን ወንዝ በሜዶንም ከተሞች አኖራቸው። (2 ነገ 17:6 1 ዜና 5:26 2 ነገ 19:12 ኢሳ 37:12)

ጎዶልያስ ~ Gedaliah: ገድለ ዋስ፣ ገድለ ያሕ፣ የሕያው ገድል፣ የእግዚአብሔር ገድል፣ የአምላክ ታላቅ ሥራ፣ የአብ ሥራ... ማለት ነው። Gedaliah- ገድል እና ያሕ (ያሕዌ፣ ዋስ) ከሚሉ ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። [ትርጉሙ እግዚአብሔር ታላቅ ነው ማለት ነው / መቅቃ] በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-

1. የኤዶታም ልጅ፥ ጎዶልያስ (1 ዜና 2539)

2. የአኪቃም ልጅ፥ ጎዶልያስ (2 ነገ 25:22)

3. የጳስኮርም ልጅ፥ በኤርምያስ ሴራ ከጠነሰሱ የአይሁድ ሕግ አዋቂዎች፥ ጎዶልያስ (ኤር 38:1)

4. የአማርያ ልጅ፣ የኵሲ አባት ሁኖ የነቢዩ ሶፎንያስ አያት፥ (ሶፎ 1:1)

ጎግ ~ Gog: ተራራ ማለት ነው። (ሠራዊት፣ መንጋ፣ በዝቶ የሚኼድ የሚንጋጋማለት ነው፥ ተብሎ ይተረጎማል ኪወክ / )

1. የሸሜያ አባት፥ ልጁ ጎግ ልጁ ሰሜኢ፥ ልጁ ሚካ፥ (1 ዜና 5:4)

2. በአራቱም በምድር ማዕዘን ያሉትን አሕዛብ፥ ጎግንና ማጎግን፥ እንዲያስታቸው ለሰልፍም እንዲያስከትታቸው ይወጣል፤ ቍጥራቸውም እንደ ባሕር አሸዋ የሚያሕል ነው።” (ራእይ 20:8)

ጎፈር ~ Gopher: ጎፈር ማለት ነው። ጎፈረ ከሚለው ቃል የተገኘ የእንጨት ስም ነው። [ጥድን የሚመስል ዛፍ / መቅቃ]

ኖኅ መርከብ የሠራበት የእንጨት ስም፣ ጎፈር እንጨት መርከብን ለአንተ ሥራ በመርከቢቱም ጉርጆችን አድርግ፥ በውስጥም በውጭም በቅጥራን ለቅልቃት (ዘፍ 614)


No comments:

Post a Comment

ማውጫ

    ሀ   ለ   ሐ   መ   ሠ   ረ   ሰ   ሸ   ቀ   በ   ተ   ቸ   ኀ   ነ   ኘ   አ   ከ   ኸ   ወ   ዐ   ዘ   ዠ   የ   ደ   ጀ   ገ   ጠ   ጨ   ጰ   ጸ   ፀ   ፈ   ፐ