ሀ ለ ሐ መ ሠ ረ ሰ ሸ ቀ በ ተ ቸ ኀ ነ ኘ አ ከ ኸ ወ ዐ ዘ ዠ የ ደ ጀ ገ ጠ ጨ ጰ ጸ ፀ ፈ ፐ
ጱዴስ ~ Pudens: ‘ዓይናፋር’
ማለት ነው።
ሮማዊ ክርስቲያን፥ “ከክረምት በፊት እንድትመጣ ትጋ። ኤውግሎስና ጱዴስ ሊኖስም ቅላውዲያም ወንድሞችም
ሁሉ ሰላምታ
ያቀርቡልሃል።”
(2 ጢሞ 4:21)
ጲላጦስ ~ Pilate: ‘ጦረኛ፣ ነፍጠኛ፣ የጦር ልብስ
የለበሰ’
ማለት ነው።
በጌታ ላይ
የፈረደ ሮማዊ ገዥ፥ “አስረውም ወሰዱት፥ ለገዢው ለጴንጤናዊው ጲላጦስም አሳልፈው ሰጡት።” (ማቴ 27:2)
ጲስድያ ~ Pisidia: ‘ሜዳማ’
ማለት ነው።
በታንሽቱ እስያ
የሚገኝ የቦታ
ስም፥ “እነርሱ ግን
ከጴርጌን አልፈው
የጲስድያ ወደምትሆን
ወደ አንጾኪያ
ደረሱ፤ በሰንበትም
ቀን ወደ
ምኵራብ ገብተው
ተቀመጡ።”
(ሐዋ 13:14፥14:21-24)
ጲርአም ~ Piram: ‘መንጋ’
ማለት ነው።
ኢያሱ ከነዓንን
በያዘ ጊዜ፥
የአሞራውያን ንጉሥ፥
“ስለዚህም የኢየሩሳሌም ንጉሥ
አዶኒጼዴቅ ወደ
ኬብሮን ንጉሥ ወደ ሆሃም፥ ወደ የርሙት ንጉሥም ወደ ጲርአም፥ ወደ ለኪሶ ንጉሥም ወደ ያፊዓ፥ ወደ
አዶላም ንጉሥም
ወደ ዳቤር
ልኮ። ወደ
እኔ ውጡ፥” (ኢያ
10:3)
ጲርዓቶን ~ Pirathon: ‘ልዑላዊ’
ማለት ነው
። በኤፍሬም
አገር የነበረ
የቦታ ስም፥
“የጲርዓቶናዊውም የሂሌል ልጅ
ዓብዶን ሞተ፥
በተራራማውም በአማሌቃውያን
ምድር በኤፍሬም
ባለችው በጲርዓቶን ተቀበረ።” (መሣ
12:15)
ጲጥፋራ ~
Potiphar:
‘የአፍሪካ ወይፈን’ ማለት ነው። “ዮሴፍ ግን ወደ ግብፅ ወረደ የፈርዖን ጃንደረባ የዘበኞቹም አለቃ የሚሆን የግብፅ ሰው ጲጥፋራ ወደ ግብፅ ካወረዱት ከእስማኤላውያን እጅ ገዛው።” (ዘፍ 39:1)
ጳስኮር ~ Pashur:
‘የተሻረ፣ የተፈታ፣ ነጻ የሆነ’ ማለት ነው።
1. ከካህናት አለቆች አንዱ፥
የመልኪያ ወገን፥ “የመልኪያ ልጅ የጳስኮር ልጅ የይሮሐም ልጅ ዓዳያ የኢሜር ልጅ የምሺላሚት ልጅ የሜሱላም ልጅ የየሕዜራ
ልጅ የዓዲኤል
ልጅ መዕሣይ” (1 ዜና
9:12፥ 24:9፤ ነህ 11:12)
2. “በእግዚአብሔርም ቤት የተሾመው አለቃ የካህኑ የኢሜር ልጅ ጳስኮር ኤርምያስ በዚህ ነገር ትንቢት ሲናገር ሰማ” (ኤር 20:1)
ጳርሜና ~ Parmenas: ‘ዘላቂ፣ ቀጣይ’ ማለት
ነው። በሐዋርያት
ከተሾሙ ከሰባቱ
ዲያቆናት አንዱ፥
“ይህም ቃል ሕዝብን
ሁሉ ደስ
አሰኛቸው፤ እምነትና
መንፈስ ቅዱስም
የሞላበትን ሰው
እስጢፋኖስን ፊልጶስንም
ጵሮኮሮስንም ኒቃሮናንም ጢሞናንም ጳርሜናንም ወደ ይሁዲነት ገብቶ የነበረውን የአንጾኪያውን ኒቆላዎስንም
መረጡ።”
(ሐዋ 6:5)
ጳትሮስ ~
Pathros:
ባተ ራስ፣ ቤተ ራስ፣ የበላይ አባት... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስም- ጴጥሮስ]
‘ከአርባ ዓመት
በኋላ እስራኤላውያንን፣ ከተበተኑባቸው እሰበስባለሁ’
ብሎ በተናገረው ትንቢት የተጠቀሰ የቦታ ስም፥ “በዚያም ቀን እንዲህ ይሆናል የቀረውን የሕዝቡን
ቅሬታ ከአሦርና
ከግብፅ፥ ከጳትሮስና ከኢትዮጵያ...” (ኢሳ
11:11)
ጳንጦስ ~ Pontus: ‘ባሕር’
ማለት ነው።
የታናሽቱ እስያ
ክፍለ ግዛት፥
“የጳርቴና የሜድ የኢላሜጤም ሰዎች፥ በሁለት ወንዝም
መካከል በይሁዳም
በቀጰዶቅያም በጳንጦስም በእስያም” (ሐዋ 2:9)
ጳውሎስ ~ Paul: ‘ንኡስ፣ ትንሽ’ ማለት ነው። የሳውል
ሌላ ስም፥
“ጳውሎስ የተባለው ሳውል
ግን መንፈስ
ቅዱስን ተሞልቶ
ትኵር ብሎ
...” (ሐዋ 13:9)
ጳጥራ ~
Patara:
ሐዋርያው ጳውሎስ ባደረገው ጉዞ ካለፈባቸው ከተሞች፥ “ከእነርሱም ተለይተን
ተነሣን፤ በቀጥታም
ሄደን ወደ
ቆስ በነገውም
ወደ ሩድ
ከዚያም ወደ
ጳጥራ መጣን፤” (ሐዋ 21:1፣2)
ጳጥሮባ ~
Patrobas:
አባት፣ አባታዊ... ማለት ነው። ጳውሎስ በሰላምታ ደብዳቤው የጠቀሰው፥
በሮም የነበረ
ክርስቲያን፥ “ለአስቀሪጦንና ለአፍለሶንጳ
ለሄሮሜንም ለጳጥሮባም ለሄርማንም ... ሰላምታ
አቅርቡልኝ”
(ሮሜ 16:14)
ጳፉ ~ Paphos: ‘ትኩስ፣ የፈላ፣ የሞቀ’
ማለት ነው።
ጳውሎስና በርናባስ
በጉዟቸው ከጎበኟቸው ቦታዎች፥ የቆጵሮስ ዋና ከተማ፥ “ደሴቲቱንም ሁሉ እስከ ጳፉ በዞሩ ጊዜ፥ በርያሱስ የሚሉትን ጠንቋይና ሐሰተኛ ነቢይ የሆነውን አንድ አይሁዳዊ ሰው አገኙ፤”
(ሐዋ 13:6)
ጴርጋሞን ~
Pergamos:
‘ምጡቅ፣ ዳገት’
ማለት ነው። ከሰባቱ አብያተ ክርስቲያን አንዱ
የሚገኝባት፥ በታናሽቷ
እስያ የምትገኝ
ከተማ፥ “እንዲሁም። የምታየውን
በመጽሐፍ ጽፈህ
ወደ ኤፌሶንና
ወደ ሰምርኔስ
ወደ ጴርጋሞንም
ወደ ትያጥሮንም
ወደ ሰርዴስም
ወደ ፊልድልፍያም
ወደ ሎዶቅያም
በእስያ ወዳሉት
ወደ ሰባቱ
አብያተ ክርስቲያናት
ላክ አለኝ።” (ራእ
1:11፥ 2:17)
ጴርጌ ~
Phrygia:
‘ደረቅ መሬት፣ የገበረ’ ማለት ነው። በታናሽቱ እስያ የምትገኝ አገር፥ “እነርሱ ግን ከጴርጌን አልፈው የጲስድያ ወደምትሆን ወደ አንጾኪያ ደረሱ፤ በሰንበትም ቀን ወደ ምኵራብ ገብተው ተቀመጡ።” (ሐዋ 13:14)
ጴርጌን ~ Perga: ‘ፈራሽ፣ አላፊ፣ ጠፊ፣ ምድራዊ’ ማለት ነው። የጵንፍልያ
ከተማ፥ “ጳውሎስም ከጓደኞቹ ጋር ከጳፉ ተነሥቶ የጵንፍልያ ወደምትሆን ወደ ጴርጌን መጣ፤ ዮሐንስም ከእነርሱ ተለይቶ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ።” (ሐዋ 13:13)
ጴጥሮስ ~
Peter:
ቤተ ራስ፣ የአባት ወገን፣ የበላይ አባት... ማለት ነው። (‘ዓለት ማለት ነው’ ተብሎም ይተረጎማል።) [ተዛማጅ ስም- ጳትሮስ]
የስምዖን ስም፥ “...ሁለት ወንድማማች ጴጥሮስ የሚሉትን ስምዖንን ...” (ማቴ
4:18)
ጵልያጦ ~ Amplias: ትልቅ፣
ጉልህ፣ ደምቆ
የሚታይ፣ ጎልቶ
የሚሰማ... ማለት ነው። በሮም የነበረ ክርስቲያን፥ ጳውሎስ በሰላምታ ደብዳቤው የጠቀሰው፥ “በጌታ ለምወደው ለጵልያጦን ሰላምታ አቅርቡልኝ።” (ሮሜ 16:8)
ጵርስቅላ ~ Prisca, Priscilla: ‘ጥንታዊ’
ማለት ነው። ሐዋርያው ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ በላከው የሰላምታ ደብዳቤ፥ የጠቀሰው፥ “ለጵርስቅላና ለአቂላ ለሄኔሲፎሩም ቤተ ሰዎች ሰላምታ አቅርብልኝ።”
(2 ጢሞ 4:19)
ጵርስቅላ / Priscilla: የአቂላ
ሚስት፥ “በወገኑም የጳንጦስ
ሰው የሚሆን
አቂላ የሚሉትን
አንድ አይሁዳዊ
አገኘ፤ እርሱም
ከጥቂት ጊዜ በፊት
ከሚስቱ ከጵርስቅላ ጋር
ከኢጣልያ መጥቶ
ነበር፥ አይሁድ
ከሮሜ ይወጡ
ዘንድ ቀላውዴዎስ አዞ ነበርና፤ ወደ እነርሱ ቀረበ፥” (ሐዋ 18:2)
ጵሮኮሮስ ~ Prochorus:
‘የመዘምራን አለቃ’
ማለት ነው።
ከሰባቱ ዲያቆናት
ሦስተኛው፥ “ይህም ቃል
ሕዝብን ሁሉ
ደስ አሰኛቸው፤
እምነትና መንፈስ
ቅዱስም የሞላበትን
ሰው እስጢፋኖስን
ፊልጶስንም ጵሮኮሮስንም
ኒቃሮናንም ጢሞናንም
ጳርሜናንም ... የአንጾኪያውን
ኒቆላዎስንም መረጡ።” (ሐዋ
6:5)
ጵኒኤል ~ Peniel: ፕኒኤል፣
ፋና ኤል፣
የአምላክ ፊት፣
የጌታ መልክ፣
የእግዚአብሔር ፊት፣ ብርሃናማ፣ አንጸባራቂ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ፋኑኤል]
ያዕቆብ ከአንድ
ሰው ጋር
እስከ ንጋት
ድረስ ይታገል
የነበረበት ቦታ፥
“ያዕቆብም። እግዚአብሔርን ፊት
ለፊት አየሁ፥
ሰውነቴም ድና
ቀረች ሲል
የዚያን ቦታ
ስም ጵኒኤል ብሎ ጠራው” (ዘፍ 32:30) ፣ “ጵኒኤልንም ሲያልፍ ፀሐይ ወጣችበት፥ እርሱም በጭኑ ምክንያት ያነክስ ነበር።” (ዘፍ 32:31)
ጵኒኤል ~ Penuel: ‘የአምላክ ፊት’ ማለት
ነው። ያዕቆብ
ከእግዚአብሔር ጋር
የታገለበት፥ እስራኤል
ተብሎ የተጠራበት
ሥፍራ፥ “ያዕቆብም። እግዚአብሔርን ፊት ለፊት አየሁ፥ ሰውነቴም ድና ቀረች ሲል የዚያን ቦታ ስም ጵኒኤል ብሎ ጠራው”
(ዘፍ 32:30)
ጵንፍልያ ~ Pamphylia: ‘የተደባለቀ ሕዝብ’ ማለት
ነው። ጳውሎስ
በሐዋርያዊ ጉዞው ካለፈባቸው ቦታዎች፥ “ጳውሎስም ከጓደኞቹ ጋር ከጳፉ ተነሥቶ የጵንፍልያ ወደምትሆን
ወደ ጴርጌን
መጣ፤ ዮሐንስም
ከእነርሱ ተለይቶ
ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ።” (ሐዋ 13:13፣14)
ጶጥፌራ ~ Potipherah: የዮሴፍ
ሚስት፣ የአስናት
አባት፥ የምናሴና
ኤፍሬም አያት፥ “ለዮሴፍም በግብፅ ምድር ምናሴና ኤፍሬም ተወለዱለት የሄልዮቱ ከተማ ካህን የጶጥፌራ ልጅ አስናት የወለደቻቸው ናቸው።” (ዘፍ 41:45፣ 50፥ 46:20)
No comments:
Post a Comment