ሀ ለ ሐ መ ሠ ረ ሰ ሸ ቀ በ ተ ቸ ኀ ነ ኘ አ ከ ኸ ወ ዐ ዘ ዠ የ ደ ጀ ገ ጠ ጨ ጰ ጸ ፀ ፈ ፐ
ፐራሲም ~ Perazim: ‘ክፍተት’
ማለት ነው።
የተራራ ስም፥
“እግዚአብሔርም ሥራውን ማለት እንግዳ ሥራውን ይሠራ ዘንድ፥ አድራጎቱንም ማለት
ያልታወቀውን አድራጎቱን
ያደርግ ዘንድ
በፐራሲም ተራራ
እንደ ነበረ
ይነሣል፥ በገባዖንም ሸለቆ እንደ ነበረ ይቈጣል።” (ኢሳ 28:21)
ፑቲዮሉስ ~
Puteoli:
ሐዋርያው ጳውሎስ ካረፈባቸው ቦታዎች፥ “ከዚያም እየተዛወርን
ወደ ሬጊዩም
ደረስን። ከአንድ
ቀን በኋላም
የደቡብ ነፋስ
በነፈሰ ጊዜ
በሁለተኛው ቀን ወደ ፑቲዮሉስ መጣን።” (ሐዋ 28:13፣14)
ፑፕልዮስ ~ Publius:
‘የጋራ’ ማለት ነው። መርከባቸው
በተሰባበረች ጊዘ፥
ጳውሎስንና ደቀመዛሙቱን
ተቀብሎ ያስተናገደ
የመላጥያ ሰው፥
“በዚያም ስፍራ አጠገብ
ፑፕልዮስ የሚሉት
የደሴት አለቃ
መሬት ነበረ፥
እርሱም እንግድነት
ተቀብሎን ሦስት
ቀን በፍቅር
አሳደረን።”
(ሐዋ 28:7)
ፒላቲ ~
Peulthai:
‘ዋጋዬ፣ ድርሻዬ’
ማለት ነው። የኦብዲ ኤዶም ስምንተኛ ልጅ፥ “ስድስተኛው ዓሚኤል፥ ሰባተኛው ይሳኮር፥ ስምንተኛው ፒላቲ” (1
ዜና 26:5)
ፒቶን ~
Pithon:
“አበረታች፣ አንደበተ ርቱዕ’ ማለት ነው። “የሚካም ልጆች ፒቶን፥ ሜሌክ፥ ታሬዓ፥ አካዝ ነበሩ”
(1 ዜና 8:35፥ 9:41)
ፕሮፊሞና ~ Tryphena: ‘አስደሳች’
ማለት ነው።
በሮም የነበሩ
እኅትማማች ክርስቲያኖች፥
ጳውሎስ በሰላምታ
ከጠቀሳቸው አንዷ፥
“በጌታ ሆነው ለሚደክሙ ለፕሮፊሞናና ለጢሮፊሞሳ ሰላምታ አቅርቡልኝ። በጌታ እጅግ ለደከመች ለተወደደች
ለጠርሲዳ ሰላምታ
አቅርቡልኝ”
(ሮሜ 16:1)
No comments:
Post a Comment