ሠምላ ~ Samlah: መጎናጸፊያማለት ነው። ከኤዶም ነገሥታት አንዱ፥ ከሃዳድ ቀጥሎ የነገሠ፥ ሃዳድም ሞተ፥ በስፍራውም የመሥሬቃው ሠምላ ነገሠ።(ዘፍ 36:36371 ዜና 1:4748)

ሠራያ ~ Seraiah: ራያሕ፣ የአምላክ ሠራተኛ፣ የጌታ አገልጋይ፣ የአምላክ ሠራዊት... ማለት ነው።

ሥራ እና ያሕ’(ያሕዌ ) ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በዚህ ስም የሚታወቁ ሰዎች:-

1. የዮብ አባት፥ የቄኔዝ ልጅ፥ (1 ዜና 4:13 14)

2. የዮሺብያ ልጅ፥ (1 ዜና 4:35)

3. የንጉሥ ዳዊት ጸሐፊ የነበረ፥ (2 ሳሙ 8:17)

4. በሴዴቅያስ ዘመን የነበረ ካህን፥ (2 ነገ 25:18, 23)

5. የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ወደ ባቢሎን ከማረካቸው ምርኮኞች ወደ ኢየሩሳሌምና ወደ ይሁዳ ወደ እየከተማቸው ከተመለሱ የአገር ልጆች፥ (ዕዝ 2:2)

6. በነህምያ ዘመን፣ የቃል ኪዳኑ ደብዳቤ ከፈረሙ ካህናት፥ (ነህ

10:2)

7. የጸሐፊው የዕዝራ አባት፥ “...በአርጤክስስ መንግሥት ዕዝራ ሠራያ ልጅ፥” (ዕዝ 7:1)

8. የቤተ መቅደሱ ላፊ፥ የኪልቅያስ ልጅ፥ (ነህ 11:11)

9. በዮአቂም ዘመን የአባቶች ቤቶች አለቃ፣ ካህን፥ (ነህ 12:1 12)

10. የኔርያ ልጅ፥ (ኤር 51:59)

ሠርሰኪም ~ Sarsechim: እጩ መኮንንማለት ነው። ናቡከደነፆር ኢየሩሳሌምን በወረረ ጊዜ የነበረ የጦር መሪ፥ የባቢሎንም ንጉሥ አለቆች ሁሉ፥ ኤርጌል ሳራስር፥ ሳምጋርናቦ፥ ሠርሰኪም ራፌስ ...” (ኤር 39:3)

ሠጉብ ~ Segub: ሰገባ፣ መሸሸጊያ፣ የተመሸገ፣ የተገነባማለት ነው።

1. ኢያሪኮን ያደሰው፣ የአኪኤል ትንሹ ልጅ፥ በእርሱም ዘመን የቤቴል ሰው አኪኤል ኢያሪኮን ሠራ ... በታናሹ ልጁም ሠጉብ በሮችዋን አቆመ።” (1 ነገ 16:34)

2. የኤስሮ ልጅ፥ ከዚያም በኋላ ኤስሮም ስድሳ ዓመት በሆነው ጊዜ ወዳገባት ወደ ገለዓድ አባት ወደ ማኪር ልጅ ገባ ሠጉብንም ወለደችለት። ሠጉብም ኢያዕርን ወለደ” (1 ዜና 2:2128)

ሣሌፍ ~ Sheleph: ሰልፍ ማለት ነው። የዮቅጣን ሁለተኛ ልጅ፥ ሣሌፍን፥ ሐስረሞትን፥ ያራሕን፥ ሀዶራምን፥” (ዘፍ 10:26 1 ዜና 1:20)

ሣሪድ ~ Sarid: አልሞት ባይ፣ ጠንካራማለት ነው። ብሎን ግዛት ውስጥ የነበረ ጉልህ ሥፍራ፥ ሦስተኛውም ዕጣ ለዛብሎን ልጆች በየወገኖቻቸው ወጣ የርስታቸውም ድንበር ወደ ሣሪድ ደረሰ (ኢያ 19:1012)

ሣራ ~ Sarah: ር፣ ዘሬ፣ ወገኔ... ማለት ነው። ልዕልት፣ የብዙ እመቤት ማለት ነው ተብሎም ይተረጎማል። የአብርሃም ሚስት፥ የቀድሞ ስሟ ሦራ ነበር፥

እግዚአብሔርም አብርሃምን አለው፦ የሚስትህን የሦራን ስም ሦራ ብለህ አትጥራ፥ ስምዋ ሣራ ይሆናል እንጂ።” (ዘፍ 17:15)

ሣካር ~ Sacar: ዋጋ፣ ደሞዝ፣ ምርትማለት ነው።

1. “እግዚአብሔርም ባርኮታልና ዖቤድኤዶም ልጆች ነበሩት በኵሩ ሸማያ ... አራተኛው ሣካር አምስተኛው ናትናኤል፥ (1 ዜና 26:4)

2. የአምና አባት፥ የአሮዳዊው የአራር ልጅ አምናን፥” (1 ዜና

11:35)

ሣጥን ~ Coffer, Coffin: ከፈን፣ መጠቅለያ፣ መሸፈኛ፣ መቅበሪያ ሳጥን... ማለት ነው።

Coffin -‘ከፈነከሚለው ግስ የተገኘ ስም ነው።

       ሣጥን / Coffer: ብር፣ ሽፋን... ማለት ነው። የንዋየ ማስቀመጫ፥የእግዚአብሔርንም ታቦት ወስዳችሁ በሰረገላው ላይ አኑሩት ስለ በደልም መሥዋዕት ያቀረባችሁትን የወርቁን ዕቃ ሣጥን ውስጥ አድርጋችሁ በታቦቱ አጠገብ አኑሩት ...” (1 ሳሙ 6 8 11 15)

       ሣጥን / Coffin: ዮሴፍ በግብፅ በሞተ ጊዜ በድኑ የተቀመጠበት እቃ፥ ዮሴፍም በመቶ አሥር ዓመት ዕድሜው ሞተ በሽቱም አሹት፥ በግብፅ ምድር ሣጥን ውስጥ አኖሩት።” (ዘፍ 5026)

ሤራሕ ~ Serah: ሥራህ፣ ሥራ፣ ድርጊት፣ ክንውን... ማለት ነው። የአሴር ልጅ፥ ሤራሕ (ዘፍ 46:17 1 ዜና 7:30) (ዘኁ 26:46)

ሤባ ~ Shebah: ሰብዓ፣ ሳባ፣ ሰብ፣ ሰው፣ የሰው ልጅ... ማለት ነው። [ተዛማጅ ስሞች- ሰበንያ፣ ሰብታ፣ ሰንበት፣ ሳባ፣ ሳባታይ፣ ሳባጥ፣ ሳቤህ፣ ሳቤዔ፣ ጸባዖት] አንድ ሰውና አንድ ቦታ በዚህ ስም ይታወቃሉ።

. ለስምዖን ልጆች ነገድ እጣ የወጣ የቦታ ስም፥ (ኢያ 19:2)

. የንጉሥ ሰሎሞን አባት፥ ጸሐፊዎቹም ሴባ ልጆች ኤልያፍና ...” (1 ነገ 4:3)

ሤኩ ~ Sechu: ማማ ማለት ነው። በገለዓድና ራማ መካከል የሚገኝ ቦታ፥ የሳኦልም ቍጣ ነደደ፥ እርሱም ደግሞ ወደ አርማቴም መጣ፥ ሤኩ ወዳለው ወደ ታላቁ የውኃ ጕድጓድ ደረሰ ...” (1 ሳሙ 19:22)

ሥትሪ ~ Zithri: አምላክ ይጠብቅ ማለት ነው። የዑዝኤል ልጅ፥ የዑዝኤል ልጆች ሚሳኤል፥ ኤልዳፋን፥ ሥትሪ ናቸው። (ዘጸ 6:22)

ሥዖሪም ~ Seorim: ገብስማለት ነው። ከሃያ አራቱ የካህናት ምድብ፥ የአራተኛው ተራ አለቃ፥ አራተኛው ሥዖሪም አምስተኛው” (1 ዜና 24:9)

ሦራ ~ Sarai: የኔ እመቤት ማለት ነው። የአብርሃም ሚስት፣ የሣራ የቀድሞ ስም፥ ታራም ልጁን አብራምንና የልጅ ልጁን የሐራንን ልጅ ሎጥን የልጁንም የአብራምን ሚስት ምራቱን ሦራ ወሰደ ከእርሱም ጋር ወደካራንም መጡ፥ ከዚያም ተቀመጡ።” (ዘፍ 11:31 17:15)

ሦጋል ~ Shual: የአሴር ወገን፥ የጾፋ ልጅ፥ ሦጋል ቤሪ፥ ይምራ፥ ቤጼር፥ ሆድ፥ ሳማ፥ ሰሊሳ፥ ይትራን፥ ብኤራ ነበሩ። (1 ዜና 7:36)

No comments:

Post a Comment

ማውጫ

    ሀ   ለ   ሐ   መ   ሠ   ረ   ሰ   ሸ   ቀ   በ   ተ   ቸ   ኀ   ነ   ኘ   አ   ከ   ኸ   ወ   ዐ   ዘ   ዠ   የ   ደ   ጀ   ገ   ጠ   ጨ   ጰ   ጸ   ፀ   ፈ   ፐ